💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.67K subscribers
1.29K photos
494 videos
124 files
5.16K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።

👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Download Telegram
☑️ በኢባዳ ላይ የቱንም ያህል ሰነፍ ብትሆን መልካም ስነ ምግባርህ ለጀነት መግቢያ ቁልፍ ሊሆንህ ይችላልና በመልካም ስነ ምግባር ከመታነፅ  እንዳትሰንፍ።
〰〰〰〰〰〰〰
📍የአላህ ደጋግ ባሮች ከወንጀል ነፃ ናቸው ብለህ ታስባለህን!? በፍፁም ነገር ግን ፦ወንጀል ሲፈፅሙ ፦
👉 ወንጀላቸውን ግልፅ ስላላወጡ
👉 በወንጀላቸው ላይ ከመዘውተር   ስለመረጡ
👉 ወንጀል ስለመስራታቸው ምክንያት ከመደርደር ግልፅ ሆነው ጥፋታቸውን ስላመኑና
👉 ወንጀል ከፈፀሙ በኋላ መልካም ስራ ስላስከተሉ
👉ከኔና ካንተ ተሻሉ እንጂ‼️

ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንላቸዉና

ከሰለፎች አንዱን ፦

👉ዲንህ ላይ እንዴት ነህ? ሲሉ ጠየቁት።
እሱም፦
"👉ዲኔን የምሰራቸው ወንጀሎች ይበጣጠሱታል እኔ ደግሞ በኢስቲግፋር እጠጋግነዋለሁ አሏቸው" ይባላል።

ሱብሃነላህ ምን አይነት ያማረ ምላሽ ነው!

https://t.me/https_Asselfya
👉በሶላትህ ውስጥ የምትቾክል ከሆነ
ልብ በል…
ልትደርስበት የምትፈልገውና እንዳያመልጥህ የምትሰጋው ነገር ሁሉ ፊቱ በቆምከው ጌታህ እጅ ነው!

ስለዚህ ረጋ ብለህ ስገድ.
ጌታህን በሶላትህ ካስደሰትከው እርሱም ጉዳይህን በማሳካት ያስደስትካል።

https://t.me/https_Asselfya
➘እህቴ ሆይ ጠንቃቃ ሁኝ ዉድ ነገር ያለቦታዉ ርካሽ ነዉ።

ሁሉም የሚቆርጣት አበባ አትሁኝ

ያያት ሁሉ ሊቆርጣት የሚችል ቀላል ቦታ የበቀለች ርካሽ አበባ አትሁኝ!!

ምክኒያቱም የፈለጋት ሁሉ የሚቆርጣት አበባ ከጊዜ ጋር ነውና ቆሻሻ ቦታ ትጣልና ትሞታለች !!

ያየሽ ሁሉ የሚመኝሽ ዝርክርክ ሴት ሳትሆኝ ለሃላሏ ብቻ የምትታይ ውዲ አበባ ሁኝ!!

ጥንቁቅና ቁጥብ ሁኝ ውድ ትሆኛለሽ!!

https://t.me/https_Asselfya
☑️ በማቅራትህ፣ በማስተማርህና በማሳወቅህ የሰዎችን ሙገሳ፣ ውዳሴና ክብር አትፈልግ። እያስተማርኳችሁ እያልክም አትመፃደቅ። ኩራት አይያዝህ።

📍ሸኽ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና እንዲህ አሉ።

«ከፊሎች ካልተሞገሱ፣ ካልተወደሱና ከልተበረታቱ ዳእዋ ማድረጋቸውን ይተዋሉ። ይህ ሰው ወደ አላህ ይጣራ እንዳልነበረ ማሳያ አይነተኛ ምልክት ነው። ሲጣራ የነበረው ወደ ነፍሱ ነበር ማለት ነው። ሙስሊም የሆነ አካል ለዚህ ነገር ሊነቃ ይገባል። በሚያደርገው ዳእዋ ላይ ፍላጎቱና እሳቦቱ የላቀው የአላህ ፊት ፈልጎና ሰዎችን ለመጥቀም አስቦ መሆን አለበት።»

📚
إعانة المستفيد بشرح كتاب التوحيد (صـ١٤٠).

==
ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَتَطْمَئِنُّ قُلُوبُهُم بِذِكْرِ ٱللَّهِ ۗ أَلَا بِذِكْرِ ٱللَّهِ تَطْمَئِنُّ ٱلْقُلُوبُ

እነዚያ ያመኑ ልቦቻቸውም አላህን በማውሳት የሚረኩ ናቸው፡፡ ንቁ! አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ፡፡

📚(አል -ረዕድ 28
سبحان اللّہ .. الحمد للّہ ..  لا إلّہ إلا اللّہ .. اللّہ أڪبع ..

➘የማታዚክ እንዳንረሳ
➘ነቢያችን ﷺ ለዓኢሻህ: አንቺኮ ስትቆጪና ስትበሳጪ አውቅብሻለሁ! አሏት። ዓኢሻም እንዴት ታውቁብኛላቹህ ያረሱለሏህ አለቻቸው?፣ ነቢያችን ﷺ እንዲህ አሏት፦
قال : إنكِ إذا كنتِ راضية ، قلتِ : بلى ، ورب محمد ! وإذا كنت ساخطة ؛ قلتِ : لا ، ورب إبراهيم !
‹በኔ› ደስተኛ ስትሆኚ: በሙሐመድ ጌት ይሁንብኝ፣ ስተቆጪ ደግሞ: አይደለም በኢብራሒም ጌታ ይሆንብኝ እያልሽ ትሚያለሽ። ‹አሏት›
[አሲልሲለቱ አሶሒሒያህ 7/887]

የዛሬ ባሎች ሚስቶቻቸውን ልክ እንደረሱላችን ﷺ ቢረዷቸው ትዳራቸው ባስቀና ነበር። "ትዳር ያለፍቅር የሁለት ሰዎች አሰልቺ ስብሰባ ነው!።


መልካም ለይል ..

t.me/https_Asselfya
ሳታረጋግጥ አትቸኩል!
አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
√ ሼር ለማድረግ ለሚቸኩሉ ምክር !!

« ይህ አውቀት ዲንህ ነው
ዲንህ ደሞ ከስጋ ከደምህ በላይ ነውና ከማን እንደምትማርና የማን ፈትዋ እንደምቲዝ ፈትሽ
!!! Âť

【ያነበብከውና የሰማኸው ነገር እውነታ በቁርአን በሀዲስ ሳትመዝን አታሰራጭ !!】

🎙በአቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ

𝐓𝐞 » t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
አቡ-ል-አባስ–ኢብን ተይሚያ‼️
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
✍ከጀግና ቤት የተወለደ ጀግና፣ ከአንበሳ ቤት ያደገ አንበሳ፤ ሸይኹል ኢስላም—አህመድ ኢብኑ ተይሚያ!

ዒልም እየጠባ ያደገ፣ ዒልም እያጣጣመ ወጣትነቱን የተሻገረ፣ በዒልም ያሸበረቀ፣ በዒልም የነጠረ...
:
በተሰማራበት ሁሉ ኮከብ ነበር፣ አብሪ ኮከብ!
ኧረ! የምን ኮከብ የዒልሙ፣ የጂሃዱ ፀዳል የዘመኑ ከዋክብቶችን የዋጠ ደማቅ ፀሐይ ነበር እንጂ!
°
የ ተ ይ ሚ ያ ልጅ ሀ ብ ት የላቸው፣ ን ብ ረ ት የላቸው፣ ሚ ስ ት የላቸው፣ ድ ስ ት የላቸው።
*
ሙሉ ህይወታቸውን ለጌታቸው አሳልፈው የሰጡ ታ ጋ  ይ‼️
(ረህመተን ዋሲዓ!)


http://t.me/https_Asselfya
ስንቶቻችን ነን  ቁርአንን የማንበብ ዕለታዊ ና ቋሚ ልምድ ያለን?

ቀደምቶች በቀን ወይም በሌሊት ቁርአንን የማንበብ ቋሚ የሆነ ዕለታዊ ልምድ ነበራቸው ...  ይሄው ልምዳቸው ደግሞ የማይቀርና  የማይዛነፍ ተደርጎ ይያዝ ነበር ...

ዛሬ ዛሬ  ... አንዳንዶቻችን ቁርአንን ማንበብ ትዝ የሚለን ረመዳን ሲገባ ነው ... ከፊሎቻችን ጁምዓን ብቻ እየጠበቅን እንቀራለን ... ሌሎቹ አልፎ አልፎ በትንሹ ይነካካሉ ... ይሄ ሁሉ የማይመከር ወግ ነው ሊወገድ የሚገባው ልማድ ነው !

ይልቁንም በቀን ቢያንስ  አንድ ጁዝእ .. አለያ ሁለት ... ሦሥት ጁዝእ መቅራትን ልምድ አድርገን ልንይዝ ይገባል ...

ፖለቲካው ፣ የማይረባው ዲስኩር ፣ ከጠላት ከወዳጅ የሚመጣው መልእክት እንኳን ይነበባል - እንኳን የፈጣሪያችን ንግግርና መልእክት የሆነው ቁርአን!

✍️ኡስታዝ መሀመድ ሲራጅ
✍️ቁርአን ላይ ሙሀመድ የሚል አራት ቦታላይ አለ፦

➀ ሱረቱል ሙሀመድ
➁ ሱረቱል ፈትህ
➂ሱረቱል አህዛብ
➃ሱረቱል አል ኢምራን

=
ነብይ ብሎ ማለት፦
አላህ ህዝቦችን ከጨለማ ወደብርሀን እንዲየወጣ የተላከ መልእክተኛ ማለት ነዉ።

=
መጀመር የሁሉም ሲሆን መፅናት ግን ለጀግኖች ብቻ የሚሰጥ የክብር ሽልማት ነው። ........

✍️
➰በትዳር ውስጥ ትልቁ ሰኬት !!
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
ባልሽ የሚጠላውን ወይም ሚስትህ የምትጠላውን አለማድረግ/ አለመስራት ለትዳር ትልቅ ሰኬት ነው ! ትልቅ የመተሳሰብ ሂደት ነው። በቃልሺ እወድሀለሁ አንደምትይው ሁሉ የሚጠላውንና የሚያናድደውን ነገር በመራቅ እንደምትወጂው በተግባር አሳይው : አንተም እወድሻለሁ በቃል ብቻ ሳይሆን እሷ የምትጠላውን ነገር በመራቅ በተግባር አሳያት ። 

ይህ ካልሆነ ግን ምንም ያክል ብትዋደዱ የደፈረሰ ትዳር መሆኑ አይቀርምና አንዳቺሁ ለሌላው የሚጠላውን ነገር አይስራ ።

=
https://t.me/https_Asselfya
«⇘የወንዶች ልብ ውስጥ ተቅዋ የሞተ ጊዜ የሴቶችም ሃያእ ያኔ ይጠፋል»‼️

⇘አባት ልጁን ካላደበ፣ወንድም እህቱን ካልመከረ፣ባል ሚስቱን ካልተቆጣጠር ይሄኔ ነው መጥፋቱ

⇘``የሷብቻ መታገል፣ሃያእ ለማድረግ መፈለጓ፣ በሂጃብ መሸፈኗ፣ ጌታዋን ለመፍራት መጣጣሯ መች ከምትፈልገው ያደርሳትና

⇘በአከባቢዋ ያሉ ወንዶች ካልተስተካከሉ ብቻዋን ብትጥር በተኩላዎች መነከሷ እንዴት ይቀርና

⇘ሸይኽ አብድረዛቅ አልበድር  {ሃፊዘሁላህ} እንዲህ ይላሉ፦

⇘ሰንትና ስንት መልካም ሴቶች በመጥፎ ወንዶች ተበላሹ

⇘ስንት ሴቶች ሙኡሚኖች፣ መልካሞች፣ የተሸፈኑ፣ የተከበሩ፣ በትቅዋና፣በኢማን፣በጥሩነት መካከል መልካምነትን የፈለጉ 
 
⇘ተኩላዎች ይገጥሟቸዋል ከተኩሎች የሆኑ ያበላሿቸዋል በምላሳቸው፣ በሰልክ መስመሮች በተለያዩ ኢንተርኔቶች፣ፈታኝ በሆኑ ንግግሮች፣ በተለያዩ አነጋገሮች ያበላሿቸዋል  ክብሯቸውንና ብልጭነታቸው  ይነፍጓቸዋል።

https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
እዉቀትን በተዉከዉ ግዜ ይተዉሀል።


✍️
ሐያእ
___
የሙስሊም ሴት ዘዉድ !!


✍️
ከሀያእ መገለጫዎች ዉስጥ አንዱ፦
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
ሴት ልጅ ወንድን ልጅ በምታናግርበት ግዜ በተቅለሰለሰ ድምጽ አለማናገር ነዉ።

يَٰنِسَآءَ ٱلنَّبِىِّ لَسْتُنَّ كَأَحَدٍۢ مِّنَ ٱلنِّسَآءِ ۚ إِنِ ٱتَّقَيْتُنَّ فَلَا تَخْضَعْنَ بِٱلْقَوْلِ فَيَطْمَعَ ٱلَّذِى فِى قَلْبِهِۦ مَرَضٌۭ وَقُلْنَ قَوْلًۭا مَّعْرُوفًۭا
የነቢዩ ሴቶች ሆይ! ከሴቶች እንደማናቸው አይደላችሁም፡፡ አላህን ብትፈሩ
(ትበልጣላችሁ)፡፡ ያ በልቡ ውስጥ በሽታ ያለበት እንዳይከጅል በንግግር አትለስልሱም፡፡ መልካምንም ንግግር ተናገሩ፡፡

t.me/https_Asselfya
✍️
«(التمييع) ليس مصطلحا علميا»

الشيخ عبدالمحسن بن عبدالله العباد -حفظه الله-
🍃