💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.67K subscribers
1.29K photos
494 videos
124 files
5.16K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።

👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Download Telegram
~ሌሎች መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ።
~አንዳንዱ ሾለ ሌሎች በቂ ማብራሪያ ይሰጣል።ስለ ልሹ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። ምን ማድረግ እንዳለበት ምን ማድረግ እንደለለበት ለይቶ  አያውቅም። ስለሌሎች በማውራት፣በመከታተል እራሱን ዘንግቷል።ለራሱ መሆን ያለበትን ረስቷል።

@AbuHafsaYimam
በድብቅ ሚሰራ ወንጀል
Daru tewhid
ሲያገቡ Sim ሚቀይሩ ወንድምና እህቶች ...?

🎙በኡስታዝ ሳዳት ከማል ሓፊዘሁላህ

         
t.me/Darutewhide
የተዋሉልን ፀጋዎች እና የኛ አያያዝ
~
አላህ ለኛ የዋለልን ፀጋዎች ምን ያህል በሚገባ መልኩ አስተንትነናቸው እናውቃለን? ከዒልም፣ ከሃብት፣ ከጤና፣ ከሰላም፣ ከትዳር፣ ከልጅ፣ ከጓደኛ፣ ከጎረቤት፣ ከብዙ አቅጣጫ ብንመለከት ስንትና ስንት የአላህ ፀጋዎች አሉ?! ሌላው ሁሉ ይቅር። አላህ ኢስላምን ስለሰጠን ብቻ የዋለልንን ውለታ በምን መመለስ ይቻላል?
በህይወታችን ከባድ ፈተና ላይ ወድቀን ከጭንቅ የወጣንባቸውን ጊዜዎች አሉ? እነሱ የአላህ ፀጋዎች ናቸው። ህመም ራሱ የአላህ ፀጋ ነው። በህመም ወንጀል ይረግፋል። ትእቢት ይተነፍሳል። ኣኺራን ማስታወስ ይኖራል። ለተውበት ያዘጋጃል።
መርሳት የአላህ ፀጋ ነው። በህይወታችን ስንት የሚያሸማቅቁ፣ የሚያሳቅቁ፣ የሚያስጨንቁ ነገሮች ይገጥሙናል። ባንረሳቸው ኖሮ ሰላም ይነሱን ነበርኮ። የምንመገበው ምግብ፣ የምንጠጣው ውሃ፣ የምንስበው አየር የአላህ ፀጋዎች አይደሉ? ሰላም ትልቅ የአላህ ፀጋ ነው። ሰላም ሲጠፋ የሰላም ኒዕማ ጎልቶ እየታየ ነው። አካላችን ሁሉ የአላህ ፀጋ ነው። እስኪ ህይወትን ያለ ዐቅላችን፣ ያለ ምላሳችን፣ ያለ አይኖቻችን፣ ያለ ጆሮዎቻችን፣ ያለ እጆቻችን፣ ያለ እግሮቻችን፣ ... እናስበው። ምን ያህል ፈታኝ ነበር?
ጊዜ የአላህ ፀጋ ነው። እንዴት እያሳለፍነው ነው? ወጣትነት የአላህ ፀጋ ነው። ምን ተሰራበት? እድሜ ፀጋ ነው። ምን ተሸመተበት? ሃብት ፀጋ ነው። ሃብታችን ከኣኺራ አንፃር እዳ ነው ወይስ ምንዳ?
ዝናቡ፣ ፀሐዩ፣ ነፋሱ፣ ቀኑ፣ ሌቱ፣ ብርሃኑ፣ ጨለማው፣ እንስሳቱ፣ እፅዋቱ፣ እሳቱ፣ የትኛው ፀጋ ተወስቶ የቱ ይቀራል? እስኪ ህይወትን ያለነዚህ ኒዕማዎች አስቧት። ሱብሓነሏህ! ያለ ምክንያት አይደለም ጌታችን አላህ እንዲህ ማለቱ፦
{وَإِن تَعُدُّوا۟ نِعۡمَةَ ٱللَّهِ لَا تُحۡصُوهَاۤۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَغَفُورࣱ رَّحِیمࣱ}
"የአላህንም ፀጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም። አላህ በእርግጥ መሃሪ አዛኝ ነውና።" [አነሕል፡ 18]
ስለዚህ የጎደለን ላይ ብቻ እያሰብን አናማር። የተሰጠንን እያስተዋልን እናመስግን። ጀሊሉ እንዲህ ብሏል፦
{لَئن شَكَرۡتُمۡ لَأَزِیدَنَّكُمۡۖ وَلَىِٕن كَفَرۡتُمۡ إِنَّ عَذَابِی لَشَدِیدࣱ}
"ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ። ብትክዱም (እቀጣችኋለሁ) ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና።" [ኢብራሂም፡ 7]
ደግሞም ምስጋና ከቃልም ባለፈ በተግባር ይገለፃል። "ምስጋና (ሹክር) ማለት ወንጀልን መራቅ ነው" ይላሉ መኽለድ ብኑ ሑሰይን። ውለታ ቢስ ልንሆን አይገባም። የተሰጡንን ፀጋዎች አላህን ለማመፅ ካዋልናቸው ይሄ ከባድ ውለታ ቢስነት ነው። ስለዚህ የአላህን ፀጋዎች ወደ አላህ መቃረቢያ እንጂ ከሱ ጋር የምንጣላባቸው እንዳይሆኑ እንጠንቀቅ። ሰለማህ ብኑ ዲናር እንዲህ ይላሉ፦
"كل نعمة لا تقرّب من اللَّه فهي بلية"
"ወደ አላህ የማያቃርብ ፀጋ ሁሉ ፈተና ነው።" [አልሒልያ፡ 3/230]
የተሰጠን ፀጋ፣ የተዋለልን ኒዕማ ፈተና እንዳይሆንብን አላህ ይጠብቀን። ኣሚን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
👍2
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
✅ ሞት .....! 🎙ሙሐመድ ሲራጅ ሙ/ኑር https://t.me/Muhammedsirage
ማንም የማይቀርበት = ሞት
ማንንም የማይፈራው = ሞት
የኛ እቅድ ውስጥ ብንረሳውም የአላህ ውሳኔ ውስጥ አለ

ሑስነል ኺታም ስጠን ።
👍1
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

ከማንኛዉም ግሩፕ እያወጡ ዉስጥ ለዉስጥ እየሄዱ ቂርአት እናቅራችሁ የሚለዉ በዝቷልና ጥንቃቄ አድርጉ። መንሀጃቸዉን አጣሩ ዝም ብላችሁ ንክር እንዳትሉ !!

~
👍6
﴿وَالْبَاقِيَاتُ الصَّالِحَاتُ خَيْرٌ عِندَ رَبِّكَ ثَوَابًا وَخَيْرٌ مَّرَدًّا﴾

«سُبْحَانَ اللهِ ، وَالحَمْدُ للهِ ، وَلَا إلَهَ إلَّا اللهُ ، وَاللهُ أكْبَرُ ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إلَّا بِاللهِ» .
👑 ከሴቶች ዲን ያላት ከሌሎች ይልቅ ብልጫ አላት!

ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦

﴿تُنْكَحُ Ř§Ů„Ů…ŮŽŘąŮ’ŘŁŮŽŘŠŮ Ů„ŘŁŘąŮ’Ř¨ŮŽŘšŮ: لِمالِها، ولِحَسَبِها، وجَمالِها، ولِدِينِها، فاظْفَرْ بذاتِ الدِّينِ، تَرِبَتْ يَداكَ﴾

“ሴት ልጅ ለአራት ነገሮች ሲባል ትገባለች። ለገንዘቧ፣ ለዘሯ፣ ለመልኳ፣ ለዲኗ ሲባል። ዲን ያላትን ምረጥ። ይህን ካለደረክ ‘ዲን ያላትን ካልመረጥክ’ እጅህ አመድ አፋሽ ይሁን።”

📚 ቡኻሪ (5090) ሙስሊም (1466) ዘግበውታል

📣በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦

💬፦ https://bit.ly/4ayf0xJ

💬፦ https://bit.ly/486xnrS

💬፦ https://bit.ly/41zEZkk

📷፦ https://bit.ly/4arMbTx

💬፦ https://bit.ly/41tIUPv

📺፦ https://bit.ly/3UTTSwh
👍2
ራስህን ሁን!
የተቀበለ ይቀበልህ
ያልተቀበለህ ይሂድ።
~
t.me/https_Asselfya
~እንደነዚያ አላህን እንደረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው ሰዎች አትኹኑ፡፡ እነዚህ አካላቶች አመጸኞች ናቸው፡፡

~
t.me/https_Asselfya
~እውነተኛ ፍቅር ...

ሱጁድህ ላይ ሆነህ ከአላህ ዘንድ ምትፈልገው  ...
ፊት ለፊት ተቀምጠህ ደግሞ ከአባቷ ምትፈለገው እንጂ..

በስልክህ በኩል ወይም ገለል ባለ ቦታ ላይ ይዘህ ምታገኘው አይደለም። .
 
                                         Ů…Ů†Ů‚ŮˆŮ„
👍1
~ብዙ ግዜ ስለ'ዛ አባት አስባለሁ…ሱብሒ ወጥቶ ሲደክም ዉሎ አምሽቶ ስለሚገባው አባት፤ ልጆቼን እንዴት ላሳድግ ብሎ በሀሳብ እየተብሰለሰለ ያለ እንቅልፍ ስለሚያድረው አባት፣ በባስ እየሄደ በታክሲ ልጁን ስለሚልከው አባት፣ ጫማ ሳይቀይር ልጁን ስለሚያስዘንጠው አባት፣ ባገኘ ጊዜ በሰባት እጆቹ አስቤዛ ሰብስቦ ስለሚገባው አባት፣ ባጣ ጊዜ ሐዘን ፊቱን ስለሚያጠቁረው አባት፣ በዱንያ ፈተናዎች ላለመዋጥ ስለሚታገለው አባት፣ ሀሳብ ጭንቀቱ ሁሉ ስለ ልጆቹ የወደፊት ዕጣፈንታ ስለሆነው አባት፣ በዕዉን በህልሙ ልጆቼን! የሚል ቃል ከአፉ ስለማይጠፋው አባት፡፡

ድሮ ያኔ አባትነት ሲባል ቀላል ነገር ይመስለኝ ነበር፤ እሱ ልጆቼን! ሲል አፉ ስለለመደበት ብቻ ይመስለኝ ነበር፡፡ ልጁ ሲወድቅ እኔን ድፍት ያድርገኝ ሲል ልቡ የሚሰነጠቅ፣ አንጀቱ የሚተረተር አይመስለኝም ነበር፡፡

አባት .... ሾፌር ሲሆን ልጁ ይደቀንበታል፣ ስልክ ሲደወል ልጄ ምን ሆና ይሆን? የሚል ሀሳብ ቀድሞ ጭንቅላቱ ላይ ይመጣበታል፤ መንገደኛ ሲሆን መንገዱ በረዘመ ቁጥር የልጆቹ ናፍቆት ይጠናበታል፡፡

አባትህ እንዴት እንዳሳደገህ ብታውቅ ኖሮ ባንተ ላይ ያለው ሐቅ እንጂ በሱ ላይ ያለህ ሐቅ ትዝ አይልህም ነበር፡፡

ጌታዬ ሆይ ባለፈው ዕድሜያችን ከወላጆቻችን አንፃር ያጎደልነዉን ሁሉ ይቅር በለን፤ በተቀረው ዕድሜያችን የምንኻድማቸው አድርገን፡፡ 
=t.me/AbuSufiyan_Albenan
👍3