💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.68K subscribers
1.29K photos
494 videos
124 files
5.16K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።

👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Download Telegram
~አንድ ቀን በእድሜው እጅግ የገፋ፣ሽፋሽፍቱ የወረደ፣ወገቡ የጎበጠ፣ሽማግሌ ዱላውን ተደግፎ እየተጎተተ የአላህ መልእክተኛ(ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) ዘንድ መጣና «የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ትንሽ ትልቅ ሳይል ወንጀልን የተባለን በሙሉ አንድም ሳያስቀር የሠራ ሰው እጣ ፈንታው ምንድነው?» አላቸው፡፡ ቀጠል አደረገና «ወንጀሉ በምድር ላይ ላሉ ሰዎች በሙሉ ቢከፋፈል ሰዎችን የሚያጠፋ ዓይነት የዚህ ዓይነቱ ሰው ተውባ ይኖረዋልን? የአላህንስ ምህረት ያገኛልን?» አላቸው፡፡ ነቢዩም (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ) «ሰልመሃልን?» አሉት፡፡ ሰውየውም «እኔማ ከአላህ በስተቀር በሀቅ የሚመለክ አምላክ የሌለ ስለመሆኑና አንቱም የአላህ መልእክተኛ መሆንዎትን እመሰክራለሁ፡፡» አላቸው፡፡

እርሳቸውም «መልካምን ነገር ትሰራለህ፤ ከመጥፎ ነገር ትርቃለህ፤ በዚህም አላህ ሁሉንም ነገር በመልካም መዝገብ ላይ ይፅፍልሃል፡፡» አሉት፡፡ ሰውየውም «ክህደቴንና ጥመቴን ሁሉ!» አላቸው፡፡ እርሳቸውም «አዎን ክህደትህንና ጥመትህን ሁሉ!» አሉት፡፡ ሰውየው ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስተኛ ሆኖ «አሏሁ አክበር! አሏሁ አክበር!» እያለ ሄደ፡፡ ከርሣቸው ዐይን እስኪሰወር ድረስ ይህንኑ ቃል ይደጋግም ነበር፡፡

•አሁን ጭንቀታችሁ ሲረግብ ይታየኛል፡፡ ኢንሻአላህ ይረግባል፡፡ አላህ ሆይ ጭንቀትን አርቅልን፡፡የደስታ ኑሮም አኑረን!
=
t.me/AbuSufiyan_Albenan
አንዳንድ የ አረቦች ቂቢላ ዘንድ ተለምዶ የሆነ ሰው ሲጠራቸው አቤት ሲሉ " ለቤህ " እሚባል አቤት አባባል አለ

እዚህ ላይ ተጠንቀቁ እህቶች ይህ ለ ሙህሪም እና ሴት ለሴት ብቻ ነው መባባል እሚቻለው

ምክንያቱም የ ውዴታ መግለጫ አቤት አባባል ስለሆነ

ይህን አረቦቹ ያውቁታል ስለዚህ የውጭ ሴቴች ለውጭ ወንዶች አይጠቀሙትም " ሰም ወይም ስሚ " ነው እሚሉት

የኛወቹ እንታረም
قال العلامة مقبل الوادعي ࢪحمه الله :

لو ڪان الطلاق بأيدي بعض النِّساء لطلقت زوجها في اليو۾ عشࢪين مـࢪة.

[ ڪتاب غاࢪة الأشࢪطة ٢/ ٢١٨].🌱
~የማይጠቅሙሸ ነገሮቾ ላይ ትኩረት ስታደርጊ ላንች ይበልጥ አስፈላጊ የሆኑትን ታጫለሸ

~ስለዚህ በሚጠቅምሽ ላይ ትኩረት አድርጊ

~
t.me/https_Asselfya
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Photo
📍የሒጃብ ጥፍጥና⁾
                { እና }
ስለሒጃብ የተሣሣቱ ግንዛቤወች

👉🔖ክፍል ሁለት

▪️ስለሒጃብ በሁለተኛ ሚሰነዘር የተሣሣተ ግንዛቤ

ሌለኛዋ እህት ደግሞ ፦ "ለምን ነገሮችን  እናከባብዳቸዋለን ኢስላም ገር የሆነ ሀይማኖት ነው {ነአም ገር ነው } ። ታዲያ ሰወች ለምን አስቸጋሪ እንዲሆን ያደርጉታል ? ሂጃብ ሴትን ልጅ ከሚያስጨንቋት ነገሮች አንዱ በመሆኑ  ለምን እንድትቸገር ይደረጋል? 
ጌታችን (ሱብሀነሁ ወተዓላ) እንድህ ሲል በቁርአኑ ተናግሮ የለምን ? "አላህ በናተ ላይ ገሩን ነገር ይሻል በእናተም ችግር እንድገጥማችሁ አይሻም ..." ትላለችም !

እንግድህ እዲ አይነት ሃሳቦች በስብእናሽ ላይ ለተንሰራፋብሽ እህቴ ሚኖረኝ ምላሽ ፦ ውድ እህቴ ! ሀያሉ ፈጣሪያችን አንችን ሂጃብ እንድታደርጊ ሲያዝሽ ህይወትሽ ቀላልና ያልተጨናነቀ #እንድሆን ፈልጎ ነው ፤ እርሱ በእውቀቱ ምሉዕ በመሆኑ የባሮቹን ሁኔታ ጠንቅቆ ያውቃልና ።

ሂጃብ ማለት ፦ለመተግበር በጣም ቀላልና ከብዙ ነገሮች የሚጠብቅሽ ነው። አወ! ሂጃብ እንደምታስቢው ከባድ ሳይሆን የማያጨናንቅ ነው ፤ ምክንያቱም በሂጃብ ያማረ ገላሽን መሰተር የቻልሽ ጊዜ ሰወች በሂጃብሽ ውስጥ ያለውን ክቡር ገላሽን ልክ ጌጣጌጥ ማስቀመጫ ሙዳይ እንደተቀመጠ የከበረ ሉል ወይም እንቁ መቁጠር ይጀምራሉና ነው ፤  ይህም ክቡር ሰውነትሽ ለአንድ እምነቱ የፀና እንድሁም የሚያፈቅርሽን ሚንከባከብሽ ወንድ ( ባልሽ) ተቆጥቦ የተቀመጠ እንደመሆኑ ገልጦ እንድመለከተው የሚፈቀድለት ለእርሱ ብቻ ነው ።

ሂጃብ አላህ ላገራለት ቀላልና የማያጨናንቅ ነው ፤ ሂጃብ መልበስሽ የአላህን ውደታ የሚያስገኝልሽ ሲሆን የመልእክተኛውን (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) የባልደረቦቻቸውን ቀኑን መንገድ የተከተሉን የሰማእታትን ጉርብትና በመጨው ዓለም ያገናፅፍሻል ።
አላህ እንድህ ይላል ፦
▪️وَمَن يُطِعِ ٱللَّهَ وَٱلرَّسُولَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ مَعَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمَ ٱللَّهُ عَلَيْهِم مِّنَ ٱلنَّبِيِّـۧنَ وَٱلصِّدِّيقِينَ وَٱلشُّهَدَآءِ وَٱلصَّٰلِحِينَ ۚ وَحَسُنَ أُو۟لَٰٓئِكَ رَفِيقًۭا
~አላህንና መልክተኛውንም የሚታዘዝ ሰው እነዚያ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይኾናሉ፡፡ የእነዚያም ጓደኝነት አማረ፡፡
(
አኒሳእ 69)

ሂጃብ ማድረግሽን ወደ ጎን ማለትሽ በራስሽ ላይ ብዙ ችግሮችን መጋበዝሽ እንደሆነ ልትረጅው ይገባል ፤እንድሁም ሂጃብ እንዳትለብሽ የሚገፋፉሽ ሀይሎች በአንቺ ላይ ብዙ መዘዞችና መጥፎ ሁኔታወች እንድፈጠሩብሽ እያደረጉ መሆናቸውን አስተውይ ። ይህን በተለመለከተ አላህ ሱብሀነሁ ተአላ እንድህ በማለት በቁርአን ይገልፃል !
▪️وَٱللَّهُ يُرِيدُ أَن يَتُوبَ عَلَيْكُمْ وَيُرِيدُ ٱلَّذِينَ يَتَّبِعُونَ ٱلشَّهَوَٰتِ أَن تَمِيلُوا۟ مَيْلًا عَظِيمًۭا
አላህም በእናንተ ላይ ጸጸትን ሊቀበል ይሻል፡፡ እነዚያም ፍላጎታቸውን የሚከተሉት (ከውነት) ትልቅን መዘንበል እንድትዘነበሉ ይፈልጋሉ፡፡
▪️يُرِيدُ ٱللَّهُ أَن يُخَفِّفَ عَنكُمْ ۚ وَخُلِقَ ٱلْإِنسَٰنُ ضَعِيفًۭا
አላህ ከእናንተ ሊያቃልልላችሁ ይሻል፡፡ ሰውም ደካማ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
(
አል ኒሳእ 27~28)

ከላይ የተጠቀሰው የቁርአን አንቀፅ ጉዳዪን ከሸሪአ አንፃር ነው የሚዳስሰው ፤ ማንኛውም ወንድና ሴት አማኞች ይህን ሀቅ ያለማስታረቅ ይቀበላሉ 

ይህን ታላቅ የሆነ ጉዳይ ከአለማዌ የአኗኗር ስረአት ጋር ብናነፃፅረው ምን ይህል ጊዜ ጉልበትና ገንዘብ ለመገላለጥና ለእርቃናዌነት ትዕይንት (ተበሩጅ) እንደሚባክን ሁላችንም አናውቅም ? መልሱ ግልፅ ነውቀላሉ መንገድ የትኛው እንደሆነ ተለይቷልሆኖም ሰወች በራሳቸው ላይ ፍትሀዌ ብያኔን የመስጠት የሞራል ብቃት የላቸውም ።
منقول
📝ይ.ቀ.ጥ.ላ.ል.......
𝐓𝐞»t.me/https_Asselfya
ለጮኸዉ  ሁሉ  ምላሽ  ከሰጠሽ  ያወራን  ሁሉ  ካዳመጥሽ  እመኝኝ  የህይወትሽን  ትርጉም አታዉቂዉም!

ራሥሽን ሁኚ
ለጮኸ ሁሉ አይመለስም  መናገርሽ ለዉጥ ካላመጣ  ዝምታ ጌጥ ነዉ

ያወሩሽን ሁሉ አትቋጥሪ
አይቶ ማለፍ ሰምቶ  ማፍሰስ  ይልመድብሽ  በጆሮሽ  እንጂ በልብ ጆሮሽ  አትስሚያቸዉ።
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Photo
ዉዶች እስከመጨረሻ እልከዉናበ pdf መልኩ ላዘጋጀዉ ፈልጌ ነዉ ኢንሻአላህ

~
⭕️👉ስ ለ ሻዕባን ወር አጫጭር ጥቆማዎች 


በሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን

«ሙስሊሞች ሆይ ያለነው በሻዕባን ወር ላይ ነውና በዚህ ወር ዙርያ አንድ ስድስት ነጥቦችን በማውሳት ልንከተለው ስለሚገባን ግዴታችን እናብራራለን።

📍የመጀመርያው ነጥብ
የሻዕባን ወር ከሌሎች ወራት በተለየ ሁኔታ በፆም ይለያልን? አዎን ይለያል ። ምክንያቱም ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] «በዚህ ወር ፆም ያበዛሉ። ከወሩ ጥቂት ቀናት እስኪቀራቸው ወሩን ይፆሙት ነበርና።»
በዚህም ሱና መሰረት የአላህ መልእክተኛን [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] በመከተል በዚህ በሻዕባን ወር ፆም ማብዛት አለብን።

📍ሁለተኛው ነጥብ
የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ፆምን የተመለከተው ነው። ይህንን ቀን ለይቶ መፆምን የሚመለከቱ ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኙና ትክክለኛ ያልሆኑ ደካማ ሀዲሶች ተነግረዋል። በነዚህ ተመርኩዞ ይህንን ዒባዳ መፈፀም ደግሞ አይቻልም። ከነቢዩ ለመተላለፉ ባልተረጋገጠ ማንኛውም ነገር አላህን ማምለክ አይፈቀድም። በመሆኑም የሻዕባን አስራ አምስተኛው ቀንን ለይቶ መፆም የሌለ ነገር ነው። ከመልእክተኛው ለመገኘቱ መረጃ ከሌለ ደግሞ ቢደዐ ነው።

📍ሶስተኛው ነጥብ፤ የሻዕባን ወር አስራ አምስተኛው ቀን ሌሊት ትሩፋትን ይመለከታል።
ልክ ቀኑን መፆም የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለው ሁሉ ለሌሊቱም ከሌሎች ሌሊቶች በላጭ ነው ተብለው የተነገሩት ሀዲሶች ከነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለመነገራቸው ትክክለኛ መረጃ የሌላቸው ደካማዎች ናቸው።
ስለሆነም የሻእባን አጋማሽ ሌሊት ልክ እንደ ረቢዕ ወር ሌሊት፣ እንደ ረጀብ ወር ሌሊት እንጂ የተለየ ነገር የለውም። ተነገረ የተባለውም መረጃ ቀድሜ እንደገለፅኩት ደካማዎች ናቸው።

📍አራተኛው ነጥብ
ይህችን የአስራ አምስተኛዋን ሌሊት ለየት አድርጎ ዝግጅት ፈጥሮ ማሳለፍ ቢደዐ ነው። ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለየት አድርገው ያሳዩን፣ ሌሊቱን የሚሰገድ አምልኮትም ዝግጅትም የለምና። ስለዚህ ምሽቷ ልክ እንደ ሌሎች ምሽት ናት። አንድ ሰው ከዚያች ሌሊት በፊትም የለይል ሰላት መስገድ ልምዱ ከነበረ በዚያች ሌሊትም ተነስቶ መስገዱ ልክ እንደበፊቱ ነውና ችግር የለውም። ካልሆነና በፊት የማይሰግድ ከነበረ ዛሬ በሻዕባን "ለይለቱ ኒስፍን" ለየት አድርጎ መስገድ የለበትም። ምክንያቱም ከአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኘ ተግባር ነውና። ከዚህም የከፋው ደግሞ አንዳንዱ ሰው የሆነ ያህል ረከዓ በዚህ ምሽት ይሰገዳል በሚል ለየት ያደርገዋል። ይሁንና ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይህንን ምሽት ነጥሎ ለየት ማድረግ ስላልተገኘ ይህችን ምሽት በሰላት ልዩ አናደርግም።

📍አምስተኛው ነጥብ
የአላህ ሱብሃነሁ ለነገሮች የሚያደርገው ውሳኔ በሻዕባን አስራ አምስተኛዋ (አጋማሽ) ምሽት ነውን

ምላሹም አይደለም ሲሆን፤ ምሽቷም የመወሰኛይቱ ሌሊት [ለይለቱል ቀድር] አይደለችምና ነው። ምክንያቱም "ለይለቱል ቀድር" በረመዳን ውስጥ የምትገኝ ምሽት ናት። ሃያሉ አላህ እንዳለው፤
”إنا انزلناه“
"እኛ አወረድነው" ማለትም ቁርኣንን ለመጀመርያ ግዜ ያወረድነው ማለቱ ነው። ይህም ሙሉ ምዕራፉ ሲነበብ እንዲህ ይላል፤

إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ ﴿١﴾ وَمَا أَدْرَاكَ مَا لَيْلَةُ الْقَدْرِ ﴿٢﴾ لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٍ ﴿٣﴾ تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِم مِّن كُلِّ أَمْرٍ ﴿٤﴾ سَلَامٌ هِيَ حَتَّىٰ مَطْلَعِ الْفَجْرِ ﴿٥﴾
Al-Qadr☞ القدر:- [1-5]

[እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡፡ (1)መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ? (2)መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡ (3) በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡ (4) እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡፡(5)]
ይህ ክስተትና ምሽቱም መቼ እንደሆነ ሲገልፅ እንዲህ ይላል፤

(شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ ۖوَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۗ يُرِيدُ اللَّـهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّـهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ) البقرة:- 185

[(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡ አላህ በእናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፡፡ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡ (185)]

በዚህም መረጃ መሰረት ለይለቱል ቀድር ማለትም ፈጣሪያችን አላህ ለማንኛውም ነገር ሁሉ አመታዊ ውሳኔ የሚሰጥበት ምሽት በረመዳን ወር ውስጥ የምትገኝ አንዲት ሌሊት መሆኗን እንረዳለን። ምክንያቱም ሌሊቷ ቁርኣን የወረደባት ሌሊት ነች ። ቁርኣን ደግሞ የወረደው በረመዳን ወር ነውና የመወሰኛይቱ ምሽትም የምትገኘው በረመዳን እንጂ በሌላ ወር አይደለም። ስለሆነም የሻዕባን አጋማሽ ሌሊት  "ለይለቱል ቀድር" የመወሰኛይቱ ምሽት አይደለችም። በዚያች ሌሊትም ለአመቱ የሚሆን ምንም የሚወሰን ነገር የለም።

📍ስድስተኛው ነጥብ፦
የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ላይ አንዳንዶች ምግብ አዘጋጅተው ለድሆች በሚል የሚያከፋፍሉትና የእናት እራት፣ የአባት እራት ወይም የወላጆች እራት የሚሉት [እንዲሁም ባገራችን የእህል ዘሮችን ባንድ ላይ ሰብስቦ በመቀቀልና ከዚያም መጀመርያ ግቢ ውስጥና ውጪም በመበተን አመቱ የጥጋብ የርጋታ ይሁንልን የሚሉት] ሁሉ ከነቢዩ ያልተላለፈልን ከሰሃቦችም ሪድዋኑላሂ አለይሂም ያልተገኘ መጤ የሆነ ቢድዐ ነው።

👆 እነዚህን ስድስት ነጥቦች ጠቅሼ ብቆጥራቸውም ሌሎች ላብራራቸው የሚገቡ ሆነው ያለፍኳቸው እንዳሉ ግልፅ ነው።  አላህ እኛንም እናንተንም ሱናን የሚያሰራጩ፣ ቢድዐን የሚያስጠነቅቁና ተመርተው የሚመሩ (ቅን ሆነው የሚያቀኑ) ያድርገን። ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በጁምዓ ኩጥባቸው ወቅት እንደገለፁት ከምሪቶች ሁሉ በላጩ የሳቸው ምሪት ነውና ቅኑን መንገድ የሚከተሉ፣ በሳቸው አመራርም የሚመሩ ያድርገን። «በማስከተል፤ ከንግግሮች ሁሉ በላጩ የአላህ ኪታብ ነው። ከአመራሮች ሁሉ በላጩም የሙሀመድ ምሪት ነው። መጥፎ ጉዳይ ማለት መጤዎቹ ናቸው። ሁሉም ፈጠራዎች ጥመት ናቸውና።»ብለዋል።

منقول
➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
t.me/https_Asselfya