💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.59K subscribers
1.29K photos
495 videos
125 files
5.17K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።

👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Download Telegram
ሙሐደራ 019 ግንዛቤያችንን በተገቢው መልኩ እናስተካክል!!!
🎙 በወንድም አቡ ዒምራን
ሙሐደራ 019
➩➪➩➪➩➧

↪️ ርዕስ፦ ➘
#ግንዛቤያችንን_በተገቢው
#መልኩ_እናስተካክል!!!

✅ አግባብ ባልሆነ መልኩ የያዝናቸውን እና የተገነዘብናቸውን መርሆዎች ትክክለኛ ወደሆነው ሸሪዓዊ ግንዛቤ መመለስና ማስተካከል ይጠበቅብናል።

🎙 በወንድም አቡ ዒምራን
[ሙሐመድ መኮንን]
https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
▪️💦ጠያቂ፦ አንድን ሰው ለአላህ ብሎ የወደደ ሰው "ለአላህ ብየ እወድሃለሁ" ብሎ ማሳወቅ አለበትን?
🔜🔜🔜🔜🔜🔜🔜🔜🔜🔜🔜
▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ አዎ፡፡ ግን ለአላህ ብሎ መውደድ ዋጋው ከባድ በመሆኑ የሚከፍለው ጥቂት ነው፡፡ ለአላህ ብሎ የመውደድ ዋጋ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? እስኪ ማነው የሚያውቅ መልሱን የሚሰጠን?

▪️💦አንዱ_አድማጭ፦ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡ [ሰባት አይነት ሰዎች አላህ ከሱ ጥላ ውጪ ጥላ በሌለበት (በቂያማ) ቀን ከጥላው ስር ያስጠልላቸዋል፡፡] ከነዚህም ውስጥ [ለአላህ ብለው ተዋደው በዚያም ላይ ተገናኝተው በዚያው ላይ የተለያዩ ናቸው፡፡]

▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ እሱ በራሱ ትክክለኛ ንግግር ነው፡፡ ግን የጥያቄው መልስ አይደለም፡፡ አንተ የጠቀስከው ነገር ሙሉ ለሙሉ ሳይሆን ቀረብ ባለ መልኩ ለአላህ ብሎ መውደድ ምን እንደሆነ የሚገልፅ ነው፡፡ የኔ ጥያቄ ግን "ሁለት ለአላህ ብለው የተዋደዱ ሰዎች አንዱ ለሌላው ሊከፍለው የሚገባው ዋጋ ምንድን ነው?" የሚል ነው፡፡ እንጂ የአኺራ ሽልማቱን (አጅሩን) ማለቴ አይደለም፡፡ ስለዚህ ማለት የፈለግኩት ሁለት ሰዎች እውነት መዋደዳቸው ለአላህ እንደሆነ በተግባር የሚያመላክተው ምንድን ነው የሚል ነው፡፡

▪️💦 ሁለት ሰዎች ሊዋደዱ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውዴታቸው እውነተኛ ያልሆነ እንዲሁ ቅርፃዊ ሊሆን ይችላል፡፡ እውነተኛ እንደሆነ የሚያመላክተው ምንድነው?

▪️💦አንዱ_አድማጭ፦ ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ መውደዱ፡፡

▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ የመውደድ ነፀብራቅ ነው ወይም ከመውደድ ነፀብራቆች አንዱ ነው፡፡

▪️💦አንዱ_አድማጭ፦ የላቀው ጌታችን እንዲህ ብሏል፡ {"አላህን የምትወዱ ከሆናችሁ መልእክተኛውን ተከተሉ፡፡ አላህ ይወዳችኋልና" በላቸው፡፡}

▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ ትክክለኛ መልስ ነው- ግን ለዚህ ሳይሆን ለሌላ ጥያቄ!

▪️💦አንዱ_አድማጭ፦ ምናልባት መልሱ በዚህ ሶሒሕ ሐዲስ ውስጥ ሊሆን ይችላል፡ [ሶስት ነገሮች በውስጡ ያሉበት የኢማን ጥፍጥና አግኝቷል...] ከነዚህ ውስጥ [ለአላህ ብለው የተዋደዱ ናቸው፡፡]

▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ ይሄ ለአላህ ብሎ መውደድ የሚያስከትለው ውጤት ነው- በልቡ የሚያገኘው ጥፍጥና!

▪️💦አንዱ_አድማጭ፦ የላቀው ጌታችን እንዲህ ብሏል፡ {በዘመን እምላለሁ! በእርግጥ ሰው ሁሉ በክስረት ውስጥ ነው፡፡ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሰሩት፤ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡}

▪️💦ሸይኹል_አልባኒ፦ በጣም ጥሩ ብለሃል! ይህ ነው ትክክለኛው መልስ!! ይህም ሲብራራ እኔ አንተን እውነት ለአላህ ብየ የምወድህ ከሆነ በምክር ልከተልህ ይገባል፡፡ አንተም እንደዚያው፡፡ ለዚህም ነው "ለአላህ ብለን እንዋደዳለን" በሚሉ ሰዎች ዘንድ ይሄ አንዱ ሌላውን በምክር መከተል በጣም ውስን የሆነው፡፡ ምናልባት መዋደዳቸው ከፊል እውነት ሊኖረው ይችላል፡፡ ግን ሙሉእ አይደለም፡፡ ለምን ቢባል አንዳቸው የሌላውን ስሜት ይጠብቃልና፡፡ "እውነቱን ስነግረው ቢቆጣስ፣ ቢሸሽስ፣... ወዘተ" እያለ ሐቅን ሳያስተላልፍ ይቀራል፡፡

▪️💦 ስለዚህ ለአላህ ብሎ መውደድ ዋጋው አንዳችን ለሌላው በምክር ኢኽላስ ሊኖረው ነው- እውነተኛ መካሪ ሊሆን፡፡ ሁሌም በመልካም ሊያዘው ከመጥፎም ሊከለክለው ይገባል፡፡ ወዳጅ ለሚወደው ከጥላው የበለጠ በምክር የሚከተለው ሊሆን ይገባል ማለት ነው፡፡ ሶሐቦች ተገናኝተው ሲለያዩ አንዱ ለሌላው ይችን ምእራፍ ይቀሩ እንደነበር የሚያመላክተው ሶሒሕ ማስረጃ ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡

(አልሓዊ ሚን ፈተወል አልባኒ፡ 165-166)
https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
➲ይችን አያ የሚያስተነትን አዕምሮ ያለው ሰው እንደት አላህን ያመፃል?


كَيْفَ تَكْفُرُونَ بِاللَّهِ وَكُنتُمْ أَمْوَاتًا فَأَحْيَاكُمْ ۖ ثُمَّ يُمِيتُكُمْ ثُمَّ يُحْيِيكُمْ ثُمَّ إِلَيْهِ تُرْجَعُونَ

ሙታን የነበራችሁ ስትኾኑ ሕያው ያደረጋችሁ ከዚያም የሚገድላችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ሲኾን ከዚያም ወደርሱ የምትመለሱ ስትኾኑ በአላህ እንዴት ትክዳለችሁ!

➛አላህ ባማረውና ውብ በሆነው ቃሉ ልባችንን ያርጥብልን! የእኛ ነገር ያሳዝናል
↩️عن Ř­ŮŘ°ŮŽŮŠŮ’فٮةُ ﺭﺿ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ سَمِعْتُ النَّبِيَّ  يَقُولُ : [ لَا يَدْخُلُ الْجَنَّةَ Ů‚ŮŽŘŞŮ‘ŮŽŘ§ŘŞŮŒ]
(رواه البخاري وغيره)

▪️ሁዘይፋ(ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁኝ (ወሬ አመላላሽ ጀነትን አይገባም)

(ቡኻሪና ሌሎችም ዘግበውታል)


↩️ﻗﺎﻝ ﺭﺟﻞ ﻟﻮﻫﺐ ﺑﻦ ﻣﻨﺒﻪ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ: ﺇﻥ ﻓﻼﻧﺎ ﺷﺘﻤﻚ .. ﻗﺎﻝ:ﺃﻣﺎ ﻭﺟﺪ ﺍﻟﺸﻴﻄﺎﻥ ﺭﺳﻮﻻ ﻏﻴﺮﻙ ]

▪️አንድ ሰው ወህብ ኢብኑ ሙነቢህ ዘንድ መጣና፦
እከሌ ሰድቦሀል አለው… ሸይጧን ካንተ ውጭ ሌላ የሚልከው መልእክተኛ አጣእንዴ አለው።)

↩️[ﺟﺎﺀ ﺭﺟﻞ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺸﺎﻓﻌﻲ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ: ﻓﻘﺎﻝ ﻟﻪ ﻓﻼﻥ ﻳﺬﻛﺮﻙ ﺑﺴﻮﺀ .. ﻓﺄﺟﺎﺑﻪ: ﺇﺫﺍ ﺻﺪﻗﺖ ﻓﺄﻧﺖ ﻧﻤﺎﻡ ، ﻭﺇﺫﺍ ﻛﺬﺑﺖ ﻓﺄﻧﺖﻓﺎﺳﻖ . ﻓﺨﺠﻞ ﻭﺍﻧﺼﺮﻑ ]

▪️አንድ ሰው ኢማም አሻፊኢ ዘንድ መጣና እከሌ በመጥፎ ያነሳሀል አላቸው…እውነትህን ከሆነ አንተ ወሬ አመላላሽነህ ዋሽተህ ከሆነ ፋሲቅ ነህ አሉት። ሰውየውም አፍሮ ሄደ።
https://t.me/https_Asselfya
▪️ሱፍያን አስሰውርይ አላህ ይዘንለትና እንዲህ አለ።

✅ ውስጥህን (ቀልብህን) አስተካክል አላህ ውጭህ ያስተካክለዋል። አደራህ ንግግር አታብዛ። ንግግር መቀነስ ቀልብ እንዲረጥብ ያደርጋል።
📚 حلية الأولياء (٨٢/٧)
💦የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ።

◾️ከዚክሮች ሁሉ በላጩ 👉 لا إله إلا الله ነው
◾️ከዱአዎች ሁሉ በላጩ 👉 الحمد لله ነው

📚(ቲርሚዚ ዘግቦታል)
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌۭ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍۢ ۖ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ خَبِيرٌۢ بِمَا تَعْمَلُونَ
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡
================================
وَلَا تَكُونُوا۟ كَٱلَّذِينَ نَسُوا۟ ٱللَّهَ فَأَنسَىٰهُمْ أَنفُسَهُمْ ۚ أُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْفَٰسِقُونَ
እንደነዚያም አላህን እንደረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው (ሰዎች) አትኹኑ፡፡ እነዚያ እነርሱ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
================================
ኢኽላስ ኒያ
አንድ ሰው በምንም ሁኔታው ውስጥ ሳለ በስራው ላይ ፈጣሪን እንጂ ፍጡርን መመልከት የለበትም፤ ሰዎች ከአላህ በላይ በአንዲትም ነገር አያብቃቁለትምና፡፡

 á‰á‹°á‹­áˆ ኢብኑ ዒያድ እንዲህ ይላል፡ â€šâ€š ለሰዎች ብሎ መስራት በአላህ ላይ ማጋራት (ሽርክ)  áŠá‹áĄáĄ ለሰዎች ብሎ መስራትን መተው ታይታ (ሪያእ) ነው፡፡ ከሁለቱ መዳን ደግሞ ኢኽላስ ነው፡፡››

https://t.me/abumahi13
https://t.me/abumahi13
إنزال المرأة الى قبرها من قبل غير المحرم - العلامة صالح الفوزان…
➡️ ሴት ልጅ ከሞተች በኋላ ስትቀበር ወደ ለህድ የሚያስገባት አካል አጅነብይ ቢሆንም ችግር የለውም።

🎙العلاَّمة صَالِح الفَوْزَان حَفِظَهُ الله
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
↪️አኢሻ - ረዲዬሏሁ ዓንሃ - እንድህ ብላለች “የአላህ መልክተኛ የሰኞን እና የሐሙስን ጾም (ለመጾም በጉጉት) ይጠባበቁ ነበር፡፡”
📚 (ቲርሚዚይ: 745)

✅ሙእሚኖች ለመልካም ነገሮች ጉጉቱ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ሰኞ እና ሐሙስን መጾም፤ በየወሩ አስራ ሶስት፣ አስራ አራት እና አስራአምስተኛው ቀን መጾም፤ ዚክር (ተስቢህ ተህሊል ተህሚድ ማብዛት) ፤ ቁርአን መቅራት ፤ በሽተኛን መጠየቅ ፤ ወደተውሂድ ጥሪ ማድረግ ፤ ሰዎችን መልካም ነገር ማስተማር፤ በመልካም ማዘዝ፤ ከመጥፎ መከልከል የዘወትር ተግባራችን ሊሆን ይገባል፡፡

🔻ሙእሚን አጋጣሚዎችን ይጠቀማል ፤ ጊዜውን ሳያባክን አላህ ለሚወደውና ወደርሱ ለሚያቃርበው ተግባር ይጠቀማል ፤ በቤቱም፤ በመንገዱም፤ በመስጅዱም ፤ በሁሉም ቦታ በሚሰራቸው ስራዎች ሁሉ የአላህን ሰዋብ (ምንዳ) ተስፋ ያደርጋል ፤ የአላህን ቅጣት ይፈራል፡፡
https://t.me/joinchat/1dRtOLUW8mpkYzFk
በስጁድ መካከል የሚባል ዚክር
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
رَبِّ اغْفِرْ لِيْ رَبِّ اغْفِرْ لِيْ.

ጌታዬ ሆይ! ማረኝ፣ ጌታዬ ሆይ! ማረኝ፡፡ .’

اَللَّهُمَّ اغْفِرْ لِيْ وَارْحَمْنِيْ وَاهْدِنِيْ وَاجْبُرْنِيْ وَعَافِنِيْ وَارْزُقْنِيْ وَارْفَعْنِي.

አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ትክክለኛውን ጐዳና ምራኝ፤ ጠግነኝ፤ ሲሳይን ለግሰኝ፤ የላቀ ደረጃን አጐናፅፈኝ፡፡.’
ማንኛውም በዱንያ ላይ ለሚደርስብን መከራ፣ ስቃይ፣ ችግር፣ ሙሲባና ስብራት መጠገኛውና መካሻው ጀነት ውስጥ ነው። ብቻ በሶብር ላይ እንበርታ!
▪️በማንኛውም ነገር ላይ ታገስ!

🛍« አንዳንዴ ኡስታዝ ላይመጣ ይችላል ፣ አንዳንዴ ልትታመም ትችላለህ ፣ አንዳንዴ ቤተሰብ ሊርቁህ ይችላሉ ፣ ይህ ሁሉ መከራ እየመጣብህ ያን ሁሉ እያለፍክ ኢልም ላይ መማርህን መፅናት አለብህ። ወደ መስጅድ መሄድህን መፅናት አለብህ ፣ ቁርአን መቅራት ላይ መፅናት አለብክ ፣ ዛሬ ኡስታዝህ ተናዱ በጥፊ ስለመታህ ቁርአን መቅራትን ማቆም የለብህም ፣ ደጋግመህ ሰብረህ ፣ በዛው መቀጠል አለብህ ሰብር (ትግስት) አስፈላጊ ነው!።»
Audio
➲አላህን ማውሳትና የሚወሳበት ቦታ የመገኘት ትሩፋት

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
Audio
➲ከቁርአን አንዲትን ፊደል ማንበብ ያለው የላቀ ምንዳና ትሩፋት

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFgdAPPfoRzUemL4vw
ምሽት (መግሪብ ወቅት) ላይ ልጆቻችሁን ወደቤት ውስጥ አስገቡ፡፡ ወደ ውጭ እንዳይወጡ ከልክሏቸው፡፡ ሸይጧን በዚያ ወቅት ይሰራጫልና፡፡ ይህ ወቅት ካለፈ በኋላ ግን ቢንቀሳቀሱ ችግር የልውም፡፡ በራፎቻችሁንም ዝጉ፡፡
✅የአላህ መልእክተኛصلى الله عليه وسلمእንድህ አሉ፣

▪️የመጨረሻ ሶላታችሁን በለሊት ዊትር አድርጉ !
📚ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል}}
Muhammad al Muqit سورة الدخان - محمد المقيط | AD-DUKHAN (THE SMOKE)…
Quran Cure for the Hearts
➧ትልቅ ቅጣት ማለት ባንተና በቁርአን መረዳት መካከል እገዳ መኖር ነው!

﴿وَجَعَلْنَا عَلَى قُلُوبِهِمْ أَكِنَّةً أَنْ يَفْقَهُوهُ وَفِي آذَانِهِمْ وَقْراً﴾

" በልቦቻቸውም ላይ እንዳያውቁት ሺፋኖችን በጆሮዎቻቸውም ላይ ድንቁርናን አደረግን ፡፡"
[አንዓም 25]

➧ቁርአንን ልክ ንፁህ ያልሆነ ሰው
እንደማይነካው


➮ንፁህ ልብ የሌለውም የቁርአንን መረዳትና ጥፍጥናውን አያገኝም

➮የምንሰራቸው ወንጀሎች ከቁርአን እያራቁንና ልቦቻችንን አድርቀው
እያቆሸሹብን ይገኛሉ
ኢስቲግፋር ወደ አላህ መመለስ እናብዛ አላህ ወደርሱ ይመልሰን ።

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w