💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.6K subscribers
1.29K photos
494 videos
125 files
5.17K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።

👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Download Telegram
ሰኞ ነው የቻለ ይጹም ያልቻለ ያስታውስ ማስታወስ ለሙእሚኖች ይጠቅማልና!!!
የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة
Audio
◾️የእውቀት አስፈላጊነትና ጥቅሙ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

➡️ አዲስ ሙሀደራ
〰〰〰〰〰〰

☑️ እውቀት ብርሀን ነው
☑️ እውቀት የጀነት መንገድ ነው
☑️ እውቀት የነብያቶች ውርስ ነው
☑️ እውቀት የተፈጠርንለት አላማ ነው

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFgdAPPfoRzUemL4vw
سورة هود
أضواء القرآن adwaaalquran
📚ቆንጆ ቲላዋ
⬅️• سورة هود

🎙 القارئ عبدالعزيز الزهراني
-
➡️ ጥያቄዎቻችንን አይመልስልንም ብላችሁ ስሞታ ለምታቀርቡብኝ ወንድም እህቶች

🔘ሀቂቃ የምትጠይቁኝን ጥያቄዎች ሁሉ የምመልስበት አቅምና እውቀት ቢኖረኝ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ጠዋትም ማታ ብመልስላችሁ ደስታዬን አልችለውም ነበር። ግን ያን የማድረግ አቅሙም እውቀቱም የለኝም። እንደናንተው ገና ጅምር ላይ አሉ ከሚባሉ ተማሪዎች ውስጥ አንዱ ነኝ። የቢድአና የጥመት ባለቤቶች ሀቅን ለመቅበር፣ ማህበረሰባችንን በሽርክና በቢድአ ለማጨቃየት ከሚለፋት አንፃር በአቅሜ በምችለው ብንቀሳቀስና ለጥቂቶች እንኳን ቢሆን የኸይር ሰበብ ብሆን ብዬ እንጂ ሌላ የተለየ ነገር ኖሮኝ አይደለም። ይህ ስል እራሴን ለማተናነስና ዝቅ ብሎ መታየትን ፈልጌ እንዳልሆነ በደምብ በደምብ እወቁልኝ። አቅሜን ስለማውቀውና የሚያውቁኝ ሰዎች በደምብ ስለሚረዱኝ ነው። ይህ ማለት ግን የማውቀውን ከሱና ኡለማዎች በትክክል የተረዳሁትን ከዚህ በተሻለ መልኩ አጠናክሬ አቀርባለሁ ኢንሻአላህ። ይህ ነው እውነታው።

ግን እወቁ ቻናል የከፈተ ሁሉ፣ ብዙ ተከታይ ያለው ሁሉ፣ ያወቀውን የሚያሳውቅ ሁሉ ኣሊም ወይም ፈትዋ ሰጪ አድርጋችሁ አታስቡ። በከበደንና በጠናን ጉዳይ እንድንጠይቅ የታዘዝነው (أهل الذكر) ተብለው የተጠሩት የእውቀት ባለቤቶችን ነው። በዚሁ ላይ ለሰለፍይ ወንድም እህቶች የማሳስበው ፈትዋ ስትጠይቁ ሁለት ነጥቦችን በደምብ እንድታስታውሱ ነው።
①) ፈትዋ የምትጠይቁት አካል የእውቀት ባለቤት መሆኑን፣ በአቂዳውና በመንሀጁ የተስተካከለ መሆኑን አረጋግጡ። ሲጨንቃችሁ ላገኛችሁት ሁሉ እየጠየቃችሁ የጠሞ አጥማሚ ትክክል ያልሆነ ፈትዋ ተቀብላችሁ በመያዝ ገደል እንዳትገቡ።

②) ፈትዋ ስትጠይቁ ይቻላል ወይም አይቻልም ስትባሉ መረጃው በቁርአን በሀዲስ የተደገፈና መሆኑን አረጋግጡ። ሌላው ቢቀር ለዚህ ፈትዋ መረጃው ምንድ ነው ብላችሁ ጠይቁ። አንዳንዱ በመሰለኝ ከኪሱ በመምዘዝ ፈትዋ የሚሰጥ አይጠፋምና ጥንቃቄ አድርጉ። ስለዚህ ሁለት ነገር ላይ ትኩረት ይደረግ
👁‍🗨ፈትዋ ስትጠይቁ ለእውቀት ባለቤት ጠይቁ
👁‍🗨ለተሰጣችሁ ፈትዋ መረጃው ምንድ ነው በማለት አረጋግጡ።
Audio
የአላህ ባህሪዎችን በተመለከተ የኢማሞ አትቲርሚዚ እና የሌሎች አኢማዎች አቌም ...

https://t.me/Muhammedsirage
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
➲መንዙማ እውነታው፣ አደጋዎችና መዘዞቹ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➻ክፍል አራት ➧በሌላ ጎኑ ድል ለአሏህ፣ ለመልክተኛው እና ለአማኛች ነውና አሏህ ለነብዩሏህ ኑሕን (አለይሂ_ሰላም) በጣም ጥቂት ከሆኑ ተከታዮቻቸው ጋር ከእንስሳት ጥንድ ጥንድ በመሆን እዛች መርከብ ላይ ተጭነው በዚህ ምድራዊ ህይወት ከመስመጥ ተጠበቁ። በአላህ ፍቃድ የሚቀጥለው አለም ላይ ካለው አሳማሚ ቅጣት ተጠብቀው…
➲መንዙማ
➬➬➬➬➬

➢ክፍል አምስት

➧ልብ በሉ በዚህ ግዜ አማልክት ተብለውም አልተጠሩም። ሸይጧን ግቡን
ለማሳካት ሩቅ ነው የሚያልመው።ከዚያም ይህ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ሲተካና፣እውቀትም ሲጠፋ “አባቶቻችሁ ዝናብ ሲቸግራቸው እነሱን ነበር የሚጠይቁት” ብሎ ታላቁ ወጥመዱ ውስጥ ከተታቸው። ከዚያም ተቀበሉት። በዚህም ምክንያት አላህ ለምድር ህዝቦች የመጀመርያውን መልክተኛ ኑሕን (ዐለይሂ-ስሰላም)
ላከ።

➲ታላቁ መልክተኛ ኑሕ በቀንም በማታም፣ በድብቅም በግልፅም፣ በተለያየ ስልት ህዝባቸውን “ህዝቦቼ ሆይ! አላህን በብቸኝነት አምልኩት ከእርሱ ውጭ በሃቅ የሚመለክ የለምና” በማለት 950 አመት ተጣሩ። በጣም ጥቂቶች እንጂ ለጥሪያቸው መልካምን
መልስ አልሰጡም።


➠ነብየላህ ኑሕ 950 አመት ህዝቦቹን በቀንም በማታም በድብቅም በግልጽም ካስጠነቀቁ በኋላ የህዝቦቹ መልስ የሚከተለው ነበር

◀وَقَالُوا لَا تَذَرُنَّ آلِهَتَكُمْ وَلَا تَذَرُنَّ وَدًّا وَلَا سُوَاعًا وَلَا يَغُوثَ وَيَعُوقَ وَنَسْرًا

አሉም “አምላኮቻችሁን አትተዉ።ወድንም፣ ሱዋዕንም፣የጉሥንም፣የዑቅንም ነስርንም አትተው።” [ኑሕ፡ 23]

➧ይህን ጉድ ተመልከቱ። ብቸኛው ፈጣሪ፣ የሁሉ ቀላቢ፣ የፍጡራኑ ሁሉ መጠጊያ፣ ብቸኛ አምላክ አላህ በድንበር አላፊዎች እና የተፈጠሩለትን አላማ በረሱ ህዝቦች
“አማልክት” በተባሉ ፍጡራን ተተካ። የአላህ መብት ተቆርሶ የተሰጣቸው አምስቱ ሰዎች ወድ፣ ሱዋዕ፣ የጉሥ፣ የዑቅ እና ነስር በመባል ይታወቃሉ።


➧አርእስቱን ስናጠቃልል የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ፍጡራንን ማንም ይሁን ማን መላኢካም ይሁን ነብይ አላህ ከሰጠው ደረጃ በላይ ከፍ ማድረግ አላህ ለጠላው ሺርክ ይዳርጋል። ፍጡራን ፍጡር ናቸው። ምንም ይሁኑ ማን ጉዳትን ከራሳቸው ላይ መከላከል አይችሉም። መጥቀምም መጉዳትም የሚችለው የፍጡራን ሁሉ መጠጊያ የሆነው አንድ አላህ ብቻ ነው ።

➳ እዚህ መጸሀፍ ላይ የምናየው የሺርክ ስንኞች አብዛኛዎቹ በነብዩ (صلى الله عليه وسلم(፣በወሊዮች እና ወልይ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሰዎች ላይ ድንበር በማለፍ የተፈፀሙ ናቸው።
◉

◉
◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

➽መንዙማ ከሚለው ከሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

📚አንብብ! ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል

ወደ ግሩፓችን ይቀላቀሉ ተጠቃሚ ይሆናሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
• كيف كان النبي صلى الله عليه وسلم يقرأ القرآن ؟.
https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
﴿ يَا رَبِّ إِنَّ قَوْمِي اتَّخَذُوا هَٰذَا الْقُرْآنَ مَهْجُورًا ﴾.
﴿ وَنُنَزِّلُ مِنَ الْقُرْآنِ مَا هُوَ شِفَاءٌ وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ ﴾.
▪️اَللَّهُمَّ إِنِّيْ أَسْأَلُكَ عِلْمًا نَافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلاً مُتَقَبَّلاً. (إذا أصبح)

‹‹ኣላህ ሆይ! ጠቃሚ እውቀትን, መልካም የሆነ ሲሳይን, ተቀባይነት ያለውን ተግባርን እጠይቅሃለው፡፡››-
✍️አድስ _ተከታታይ ፁሁፍ !
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
✅የመንሃጅ ግልፅነት
እና
ደዕዋን ለማስፋፋት ያለው አስተዋፅኦ

✍️በኡስታዝ ሙሀመድ አህመድ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁሏህ
የተዘጋጀውን ፁሁፍ ኢንሻ አላህ በዚህ ቻናል በተከታታይ የምንለቅላችሁ መሆኑን እናበስራለን ።

ተቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/abumahi13
↪️አቢ ሙሳ አላህመልካም ስራውን ይውደድለትና እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ እንድህ ብለዋል

➡️ሶስት አይነት ሰዎች ጀነት አይገቡም!!
▪️አስካሪ መጠጥ አዘውታሪ
▪️ዝምድና ቆራጭ
▪️ሲህር እውነት ነው ባይ

📚رواه أحمد وٱبْنُ حِبّٓان في صحيحه
سورة الزمر
أضواء القرآن adwaaalquran
• 🔹 تلاوة من سورة الزمر

📚 القارئ عبدالمجيد الأركاني
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
➲መንዙማ ➬➬➬➬➬ ➢ክፍል አምስት ➧ልብ በሉ በዚህ ግዜ አማልክት ተብለውም አልተጠሩም። ሸይጧን ግቡን ለማሳካት ሩቅ ነው የሚያልመው።ከዚያም ይህ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ሲተካና፣እውቀትም ሲጠፋ “አባቶቻችሁ ዝናብ ሲቸግራቸው እነሱን ነበር የሚጠይቁት” ብሎ ታላቁ ወጥመዱ ውስጥ ከተታቸው። ከዚያም ተቀበሉት። በዚህም ምክንያት አላህ ለምድር ህዝቦች የመጀመርያውን መልክተኛ ኑሕን (ዐለይሂ…
➲መንዙማ
➫➫➫➫➫➫

➛ክፍል ስድስት


➧ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ወደ ምን አይነት ሰዎች ነበር የተላኩት?
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➲ሁሉም ነብይ ወደ የህዝቡ ሲላክ ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ግን ባጠቃላይ ለአለማት እዝነት ተደርገው ነው የተላኩት።ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ለምን አይነት ህዝቦች እንደተላኩ ማወቃችን ወሳኝ ነጥብ ነው።
ምክንያቱም ዛሬ አብዛኞች የነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ተከታዮች ነን እያሉ በተግባር ግን ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (የተዋጓቸውን የነ አቡ ጀህልን መንገድ ሲከተሉ ይታያሉና።


➧ከላይ “የሰው ልጆች እንዴት አላህ ላይ ማጋራት ጀመሩ” የሚለውን ዋና ነጥብ
አይተን ነበር። በነጥቡ ላይ የሺርክን አደገኝነት እና የመጀመርያው ሺርክ በምን ምክንያት እና በማን ሰባኪነት እንደተፈጸመ አይተናል። አሁን ደግሞ ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ለምን አይነት ሰዎች ተልከው እንደነበር ማወቃችን የሺርክ አደገኝነት አውቀን በአላህ ፍቃድ ከባድ ጥንቃቄ እንድናደርግ ያግዘናል፣ ይረዳናል።

➧ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (የተላኩባቸው ህዝቦች ሐጅ የሚፈጽሙ፣ ምጽዋት የሚለግሱ እና ሌሎችንም ስራዎች የሚተገብሩ ነበሩ። ግና ይህ ተግባራቸው እስልምና ውስጥ አላስገባቸውም። ምክንያቱም አምልኮ ሲፈጽሙ በአላህ ላይ አጋርን ይጨምሩ ነበርና። በዚህም ነው ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (የተጋደሏቸው።

ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (የተላኩባቸው ህዝቦች አላህ ብቸኛው የሁሉ ፈጣሪ፣ ሁሉን አስተናባሪ፣ ሲሳይ ሰጪ መሆኑን ያምኑ ነበር። ለዚህም የሚከተሉት የቁርኣን አንቀጾች ግለጽ ማስረጃ ናቸው።

وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَسَخَّرَ الشَّمْسَ وَالْقَمَرَ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۖ فَأَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ

ከሰማይም ውሃን ያወረደና በእርሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ሕያው ያደረጋት ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው “አላህ ነው” ይሉሃል። “ምስጋና ለአላህ ነው” በላቸው። ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም። አንከቦት 61

وَلَئِن
سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَهُمْ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۖ فَأَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ

ማን እንደፈጠራቸውም ብትጠይቃቸው “በእርግጥ አላህ ነው” ይላሉ። ታዲያ (ከእምነት) ወዴት ይዞራሉ?አዙህሩፍ 87

قُل لِّمَنِ الْأَرْضُ وَمَن فِيهَا إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ●قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ السَّبْعِ وَرَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَتَّقُونَ●قُلْ مَن بِيَدِهِ مَلَكُوتُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ يُجِيرُ وَلَا يُجَارُ عَلَيْهِ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ فَأَنَّىٰ تُسْحَرُونَ
“ምድርና በውስጥዋ ያለው ሁሉ የማን ነው? የምታውቁ ብትሆኑ (ንገሩኝ)” በላቸው።“በእርግጥ የአላህ ነው” ይሉሃል። “ታዲያ አትገሰጹምን?”በላቸው። “የሰባቱ ሰማያት ጌታና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን ነው?” በላቸው። “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል። “እንግዲያ አትፈሩትምን?” በላቸው። የነገሩ ሁሉ ግዛት በእጁ የሆነ እርሱ የሚጠብቅ በእርሱ ላይ የማይጠበቅ ማን ነው? የምታውቁ እንደሆናችሁ (መልሱልኝ)” በላቸው። “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል። “ታዲያ እንዴት ትታለላላችሁ?” በላቸው። [አልሙእሚኑን፡ 84-89]

📚መንዙማ ከሚለው ከኡስታዝ ሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል◉◉◉

ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselfya
https://t.me/https_Asselfya
◾️‏قال الإمام ابن القيم رحمه الله :
💦ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።

【"من طلب العلم ليحيى به الاسلام فهو من الصديقين ودرجته بعد درجة النبوة"】
✅ እስልምናን ህያውና የበላይ ለማድረግ አስቦ እውቀትን የሚፈልግ ሰው እውነተኞች ተብለው ከተመሰከረላቸው ባሮቹ ይመደባል። ጀረጃውም ከነብይነት በኋላ ያለው የሱ ይሆናል።

📚مفتاح دار السعادة (1/ 121)