💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
04 - شرح أصول السنة
ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ሸይኽ ኣደም
➡️ አዲስ ተከታታይ ትምህርት
  ➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛

📚 أصول السنة للإمام أحمد

☑️ ክፍል 04


➧የኪታብ pdf👇
t.me/https_Asselefya1/7396

🎙በተከበሩ ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ሸይኽ ኣደም ሀፊዘሁሏህ ተዓላ!!!

➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷
@SheikhMuhammedZainAdam
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በ ላኢላህ ኢለላህ መጨፈር
~
የተውሒድን ቃል (ላኢላህ ኢለላህ) ለጭፈራ ማዋል በጣም አስነዋሪ ተግባር ነው። ኢብኑል ጀውዚይ (597 ሂ.)፡-
የሱፍያ ክፍሎችን ተግባር አንስተው ሲያወግዙ እንዲህ ይላሉ:–
“በየምግቡ ላይ ይቀመጣሉ፡፡ ሲጠግቡ ጊዜ ይደንሳሉ፡፡ … ከመዐቶቻቸው ሁሉ የከፋው መዐት ግን ይህንን (ጭፈራ) መቃረቢያ (ዒባዳ) አድርገው መሞገታቸው ነው፡፡ ዳንስን ወደ ላቀው አላህ መቃረቢያ ነው ብሎ የሞገተ ሰው ከኢስላም እንደሚወጣ በርግጥም የዑለማዎች ኢጅማዕ ተቋጥሯል፡፡” [ሶይዱል ኻጢር፡ 168]
በቪዲዮው ላይ የሚታዩት ለመውሊድ የሚጨፍሩ ሱፊዮች ናቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
አርቴፊሻል ጓደኛ

አንዳንድ አርቴፊሻል ጓደኛ እንደተቆርቋሪ ያስወራህና ዞር ብሎ ያመሀል።እንዳታወራ ብለህ የነገርከውን እንደ ሚስጥር ያማከርከውን ያወራል። ንቃ! ጓደኛና ጉደኛን ለይ! ብልህ ፣በሳል፣አስተዋይ፣ነቄ ሁን!ሙእሚን ሁሌም ንቁ ነው ።አጉል ብልጥ ነን ባዮች እንዳያታልሉህ።

@AbuHafsaYimam
👑ኒቃቤ_ነው_ለኔ 👑

ኒቃቤነው ለኔ ጌጥና ማማሬ፣
የሴትነት ወጌ ሀያእ እና ክብሬ፣
የሱሀባን መንገድ በፀና ተግብሬ፣
ሙስሊም ሴት ንፁህነች ቆሻሻ አይነካትም፣
ጅላጅል ሰካራሙም ሞኙም አይደፍራትም፣
ባደባባይ ወታ ክብሯን አትጥልም፣
በዘመን አመጣሽ በፋሺን አልኖርም፣
ኒቃቤ ነው ክብሬ ሂጃቤን አልጥልም፣
ባልማር ይቅርብኝ ከኢስላም አልዞርም፣
አካሌን ገልጬ ስልጣኔ አልሻም፣

ዘመንያልበከላት ሷሊህሴትለመሆን፣
ሂወቴን ላሳልፋት በሱና ብራሀን፣
የዱኒያ ብልጭልጭ ፋሽኑ ሳይስበን፣
ዱኒያን ተረድተናት ለአኼራ ሰርተን፣
ከሸይጧን ጉትጎታ ባሏህ ተጠብቀን፣
ሂጃብን ጠብቀን በኒቃብ ተውበን፣
የዲንን ጥፍጥና በኒቃብ አጣጥመን፣
የድንን ጥፍጥና በሱና አጣጥመን፣
አሏህ ካወሳቸው ሳሊህ ሴት እንሁን፣
ከሙንከር ማራቂያ ኒቃቤነው ለኔ፣
በፋሺን መጃጃል አይስበኝምኔ፣


➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
የምንፈራው ሞት ድንገት መምጣቱ ስለማይቀር እንዘጋጅ!!

ሁላችንም ሞትን እንፈራለን። ወደሞት ከሚያደርሱን ማንኛቸውም ነገሮች በቻልነው አቅም በመጠንቀቅ ከሞት እንሸሻለን። ግን የተጠነቀቅነውን ያክል ብንጠነቀቅ የቻልነውን ያክልም ከሞት ብንሸሽ አንድ ቀን የምንፈራው ሞት በእኛ ላይ መምጣቱ ምንም ጥርጥር የለውም። አላህ እንድህ ይላል:-

{ قُلْ إِنَّ الْمَوْتَ الَّذِي تَفِرُّونَ مِنْهُ فَإِنَّهُ مُلَاقِيكُمْ ۖ ثُمَّ تُرَدُّونَ إِلَىٰ عَالِمِ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ فَيُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ }

«ያ ከእርሱ የምትሸሹት ሞት እርሱ በእርግጥ አግኛችሁ ነው (ያገኛችሗል) ።
ከዚያም ሩቁን እና ቅርቡን ዐዋቂ ወደ ኾነው ጌታ ትመለሳላችሁ፡፡ ትሠሩትም የነበራችሁትን ሁሉ ይነግራችኋል» በላቸው፡፡ [ጁሙዐ (8)]

አንድ ነገር ልብ እንበል:- መሞታችን ምንም ቅሮት ከሌላው አንድ ቀን እችን ዱኒያ መሰናበታችን ጥርጥር ከሌለው ለሞት ከወዲሁ እንዘጋጅ አንዘናጋ!!
ሞት አማክሮ አይመጣም ድንገት ነው የሚከሰተው ስለዚህ መፀፀት በማይጠቅምበት ጊዜ ከመፀፀት በስተፊት በተሰጠን የዱኒያ ጊዜ ለአኼራችን እንዘጋጅ
የተሰጠን እድል ከማለፉ በስተፊት ከሞት በሗላ ላለው ሒወታችን እንስራ!!

ኢብኑ ሙሐመድዘይን
​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•
t.me/IbnuMuhammedzeyn
Audio
🔊 አድስ የኪታብ ቂርአት


▪️ክፍል  (⓹)

➧ማህበረሰብን በማስተካከልና በማነፅ ላይ የሴቶች የጎላ ሚና በተመለከተ የሚዳስስ!!

🎙በአቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ


https://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru

➲የኪታቡን pdf ለማግኘት👇
➧t.me/https_Asselefya1/6385
Audio
☑️ አዲስ የቂርአት ፕሮግራም!!


♦️የኪታቡ ርዕስ
➫➫➫➫➫➫

🌐«የነብዩ ልደት (መውሊድ) በተመለከተ።»

↪️ (ክፍል  ➅)


🎙በአቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru

የኪታቡ PDF ለማግኘት⤵️
https://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/8307
እህቶቻችን ወደ ዲን ሲቀርቡ፣ ኒቃብ ሲለብሱ፣ ቁርኣት ላይ ሲያተኩሩ አቅማቸውን የሚፈታተኑ ብዙ ፈተናዎችን ያስተናግዳሉ። ይበልጥ የሚያመው ደግሞ ከውጪው በበለጠ በቅርብ ሰው የሚመጣው ፈተና ነው። ከዚህም ይበልጥ የሚያመው ወደ ዲን ከቀረበው፣ ሰበብ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ከሚጣልበት ወንድም የሚታየው ነገር ይበልጥ ሞራልን የሚያቀዘቅዝ፣ ስሜትን የሚጎዳ መሆኑ ነው። ቀጥሎ የማሰፍረው ከአንዲት እህት የደረሰኝ መልእክት ነው። መቼም የሁላችንም ልብ አንድ አይደለም። ምናልባት ቆም ብለን እናስብ ዘንድ በአላህ ፈቃድ የሆነ ያክል እገዛ ይኖረው ይሆናል።
اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎
አንዳንዴ ነገሩ ይከብዳል...
ብዙ እህቶች የሚወድቁበት የሆነ ብዙ ከባድ ፈተና አለ። በጣም ጠንካራ የሆኑት እንጂ የማይቋቋሙት። ደግሞ ሴቶች ደካማ እንደሆኑ ታውቃለህ። የታላቁ ጌታ በፍፁም ከኔ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ የሚል የተስፋ ቃል ባልነበረ ብዙ እህቶች ተስፋ በቆረጡ ነበር....

አሏህ ካዘነላቸው የሱና ወንድሞች ዉጪ ነገሩ እንዲህ ሆኗል ከዲን ይልቅ መልክ እድሜ ላይ በርትተዋል። መስፈርቶቹ ከአንድ ሰው ነው የሚላኩት ተብሎ እስኪጠረጠር ድረስ እንድ አይነት በመልክ ወላ በእድሜ ቀይ ቆንጆ እድሜዋ ከዚህ በታች ብዙ ኪታብ የቀራች የተማረች...ብዙ ብዙ ደግሞ እሱ ጋር ኖሮ ቢሆን እሺ።

ሁሉም ሴቶች ቀይ ናቸውን??
እሺ አንድ ሴት ቢያንስ መልኩንና ቂርዓቱን ብታሟላ እንዴት የተማረችና እድሜዋ ከዚህ በታች እንዴት ሊሆን ይችላል??
Maybe ሊኖር ይችላል ግን እጅግ ጥቂት ነው።

የምር እስኪ አንድ ወንድ ሱኒይ ሲሆን ወደ ሱና ሲጠጋ ፂሙን ይለቃል ልብሱን ከፍ ያደርጋል እና ሌሎችንም ነገሮች ይፈፅማል። የታዘዘውን ይሄን በማድረጉ ወሀቢይ ሊባል ይችላል እና ሌላም ፈተና ሊደርስበት ይችላል። ግን ሀቂቃ እንደ ሴቷ አይፈተንም። ሴቷ ኒቃብ ስትለብስ ሙተበሪጅ ሆና ዝም ያሏት ቤተሰቦቿ ሙተሀጂብ የሆነች ቀን ከገዛ ቤተሰቦቿ ፊትናው ይጀምራል። ከዛን ስራዋን ታጣለች። ሌላ ስራ ለማግኝትም ትቸገራለች። እቤት በገባች በወጣች ቁጥር አዛ ትደረጋለች። "እኔ ያስተማርኩሽ ለዚ አይደለም፣ እንደሷ አመድ አፋሽ ሆነሽ እንዳትቀሪ" እየተባለ ምሳሌ ይሰጥባታል። ሀታ በገዛ ቤቷ ባዳ የሆነች ያክል እስኪሰማት ድረስ። ታውቀዋለህ ግን ይሄ ስሜት ምን ያክል እንደሚያም?!! እኔ ግን በጭራሽ አመድ አፋሽ አልሆንኩም። እንዲያውም የጌታዬን እዝነትና ዉዴታን ነው ያፈስኩት። ከዚያም ደርስ ትከለከላለች። ግን የሚገርመው ደርስ ልትሄድ ልትቀራ "የትራንስፖርት አልሰጥም" ያለ ቤተሰብ ለዱንያዊ ትምህርት በሺዎች አውጥቶ ያስተምራል!!

ትራንስፖርት አጥታ በእግርም ቢሆን እየሄድኩ ቂርዓቴን እቀራለሁ ብላ በህመም ምክንያት ያቆመች እህት እንዳለችስ...??

ከዚህ ሁሉ መውጫ ዲኗንም ለመማር ያላት አማራጭ ኒካህ ማሰር እንደሆነ ታስባለች። በቤተሰቦቿ ቤት እንዳትቀራ ተከልክላለችና። ግን ለኒካህ የሚመጡ ወደ ሱና ተጠግተዋል የሚባሉ ወንዶች ይሄ ነው መስፈርታቸው አላህ ካዘነለት ውጪ። ቢያንስ ዲንን አስቀድመው ቢሆን፣ ዲን የላትም ብሎ ቢሆን የሚተዋት በጣም ደስ ይል ነበር።
እስኪ እናንተ የሱና ወንድሞች ካላዘናችሁልን ማን ያዝንልናል? ኢኽዋኑ!? አህባሹ!? በጭራሽ እነሱማ ሂጃባችንንም አቂዳችንንም ሊያጠፉ ነው ሚፈልጉት።

አልገጠመህምን አልሰማህምን ሱኒይ ሆና ኢኽዋኒ አገባች ሲባል?! አንድ የሱና እህት ከዚህ ሁሉ በቃ አስተካክለዋለሁ ብላ ኢኽዋን አግብታ በዛው የቀረች የተገለበጠች። ግን አንዳንዷ ደግሞ የሱና ጀግና እንጂ አይሆንም ብላ ትንሽ እድሜዋ ከፍ ካለ......የሱና ወንድ የሚባሉት ደግም የሚፈልጉት በእድሜ ትንሿን ነው። ሁሉንም እየወቀስኩ አይደለም። ደግሞ የፈለጉትን መሰፈርት ማውጣት መብታቸው ነው።
ማንም የፈለገውን መስፈርት ማድረግ መብቱ ነው ግን...???

አላህ ለነሱ ያለውን ሪዝቅ ማንም አይወስደውም ሶብር ማድረግ ነው አላህ የተሻለውን ምርጡን ያመጣል ግን ያው ሴቶች ደካማ አይደለን
አንዳንዴ ያቅታል። ህመማችን እንዲገባችሁ ነው ይህን የምለው።

ምን እንደምፈራ ግን ታውቃለህ? በፊት ኒቃብ ስለብስ ኡሚ አሪፍ ስራ ነው ያለሽ (የመንግስት ስራ ነበር የምሰራው) "ይሄን ስራ አትተይው። ሌላው ቢቀር ቢያንስ ኒካህ እስከምታስሪ ቆይ። እንዲህ ኒቃብ ከለበሽ ባል አታገኚም። ማን ያይሻል?" ብላኝ ነበር። እኔ ግን ለነፍሴ: "በጭራሽ አላህን በመታዘዝሽ ሪዝቅሽ ቢሰፋ እንጂ አይጠብም። እንዲያውም አላህን መታዘዝ ሪዝቅ ለመምጣት ሰበብ ነው" እያልኩ አበረታት ነበር የመንግስቱን ስራም ተውኩት፣ በኒቃብ መስራት አይቻልምና።
አሁን ግን ድሮም ነግሬሽ ነበር
እኔ ያልኩሽን ብትሰሚ ኖሮ ... መባሉ ያስፈራኛል።
እሷን ደስ ይበላት ብዬ የምወደውን ቂርዓት ትቼ እሷ ደስ የሚያሰኛትን ነገር እየሰራሁ ነው አላህ ነገሮቼን እስከሚያስተካክልልኝ ድረስ።

ኒቃብ ስለለበስኩ ኡሚ ለወራቶች ነው ያኮረፈችኝ። አብረን አንድ ቤት ውስጥ ሆነን ትናፍቀኝ ነበር። ሀቂቃ በጣም የሚያሳምም ነው ስሜቱ። ግን መፀናኛዬ ጌታዬ ነበር። እሱ ቅርብ የሆነ ሁሉን ነገር እያየልኝ እየሰማ ስለሆነ ደስ ይለኝ ነበር። ወሏሂ በጣም የሚያስከፋ ነገር ገጥሞኝ እኔ ግን ጌታዬን እያሰብኩ እስቅ ነበር። ሶብር በማድረጌ ከእሱ የማገኝውን አጅር እያሰብኩ እፅናና ነበር። አልሀምዱሊላህ በፊትም አሁንም በቃላትም በንግግርም ልገልፀው የማልችለው ሰላምና መረጋጋት ደስታ በውስጤ አለ።

ሌሎችም ኒቃባቸውን ቤተሰብ የሚያቃጥልባቸው በጣም ከባድ ፊትና የሚገጥማቸው ብዙ እህቶች አሉ። ከኔም የባሰ ብዙ አለና አብዝቼ ጌታዬን አመሰግነዋል ሁሌም። ኒቃቤ ለኔ ክብሬ ውበቴ ነው ከአጉል እይታ የሚከላከለኝ በጌታዬ ፍቃድ መጠበቂያዬም ጭምር። አላህ ከፊትና ይጠብቀንና የሞትኩ ቀን ቢሆን እንጂ አይወልቅም ኢንሻ አላህ። ዱንያ ላይ ያለውን ነገር ሁሉ እንስጥሽ ቢሉኝ እንኳን ወላሂ ሱመ ወላሂ እኔ በኒቃቤ አልደራደርም። ከፍ ያለው አላህ ለሁላችንም እስቲቃማውን ይስጠን።
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
እህቶቻችን ወደ ዲን ሲቀርቡ፣ ኒቃብ ሲለብሱ፣ ቁርኣት ላይ ሲያተኩሩ አቅማቸውን የሚፈታተኑ ብዙ ፈተናዎችን ያስተናግዳሉ። ይበልጥ የሚያመው ደግሞ ከውጪው በበለጠ በቅርብ ሰው የሚመጣው ፈተና ነው። ከዚህም ይበልጥ የሚያመው ወደ ዲን ከቀረበው፣ ሰበብ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ከሚጣልበት ወንድም የሚታየው ነገር ይበልጥ ሞራልን የሚያቀዘቅዝ፣ ስሜትን የሚጎዳ መሆኑ ነው። ቀጥሎ የማሰፍረው ከአንዲት እህት የደረሰኝ መልእክት…
ምንም ለማለት ቃላቶች አጠሩኝ!!!

ሀቂቀትን ሀገራችን ላይ ያለው ተጨባጭ ይሄ ነው! የቤተሰብ ግፊት በጣም ከባድ ነው ከቤተሰብ እገዛ ኑሮ ከውጭ መገፋት ይሻላል ብያለሁ!!

ውድ የሱና እህቶቸ አውቃለሁ ፈተናው በጣም ብዙ ነው ግን አላህ ጥንካሬውን እንድሰጠን የሁል ጊዜም ዱአየ ነው! ቤተሰቦች የሱና ተከታይ ካልሆኑ ሙሉ ቤተሰቦቻችን አጠገባችን ሁነው ብቻችንን ማንም እንደሌለን የሚሰማውስ ነገር ያአላህ አዛኙ ጌታችን የሱን ባሪያዎች መቸም አይረሳቸውም ጌታችን ከእኛ ጋር ነው ሁል ጊዜም አልሃምዱሊላህ!

ከችግር በኃላ ድሎት አለ የአላህን ራህመት በትዕግስት እንጠብቃለን!!
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➭የመልካም ሚስት ስብዕና ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➧የባሏን ውለታ የማትክድ ▰▱▰▱▰▱▰▱ ➝የአላህ መልዕክተኛصَلَى اْللّٰهُ عَلَيْه وَسَلَم ሆይ"በጎ የዋሉልንን መካድ ምን ማለት ነው? አልኳቸው እርሳቸውም እንድህ አሉ፦ 🔃"لعلَّ إحداكنَّ تطول أيْمَتها من أبويها ،ثم يرزقها اللّٰه زوجََا ويرزقها منه ولدًا فتغضبُ الغضبة…
የመልካም ሚስት ስብዕና
➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱

ባሏን የምታከብርና ሐቁን የምትጠብቅ
➪➪➪➪➪➪➪➪➪➪➪➪➪➪

በተለይ ደግሞ ባልየው የመልካም ስብዕና ባለቤት፣ አላህን ፈሪ፣ በዲኑ ፅናት ያለው፣ አምልኮውን በአግባቡ የሚያከናውንና የአላህን ትዕዛዝ የሚጠብቅ ከሆነ ሐቁ የዛኑ ያክል እጥፍ ድርብ ይሆናልኢማሙ ቲርሚዚይ እና ኢብኑ ማጃህ ከሙአዝ ቢን ጀበል እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ صَلَى اْللّٰهُ عَلَيْه وَسَلَم እንድህ ብለዋል

🔃قال رَسُوْل صَلَى اْللّٰهُ عَلَيْه وَسَلَم :، "لَا تُؤْذِي امْرَأَةٌ زَوْجُهَا فِي الدُّنْيَا إلَّا قَالَتْ زَوْجَتُهُ مِنَ الْحُورِ العِينِ ; لَا تُؤْذِيهِ قَاتَلَكِ اللّٰهُ.، فَإِنَّمَا هُوَعِنْدَكِ دَخِيلٌ يُوشِكُ أَنْ يُفَارِقَكِ إِلَيْنَا"

➪"ዱኒያ ላይ አንድት ሴት ባሏን የምታስቸግር ከሆነ ፤በተቃራኒው ጀነት ያለችው ሚስቱ (አልሑሪል ዒይን) አታስቸግሪው! አላህ ይርገምሺና! እርሱ እኮ ልክ አንቺ ዘንድ እንዳለ እንግዳ ነው፤ አንቺን ተለይቶ ወደኛ መምጣቱ አይቀርም። "ትላለች።

የዕውቀት ባለቤቶች (ዑለማዎች) ይህን ሀድስ አስመልክተው እንዲህ ብለዋል፦ ይህ ሀድስ ባሎቻቸውን ለሚያስቸግሩ ሴቶች ከባድ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው!

በልጆቿ መሀል ፍትሀዊ የሆነች
➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻

ከመልካም ሚስት መገለጫ ባህሪያት መካከል አላህ የልጅ ፀጋን ከለገሳትና ክብርንም ካጎናፀፋት በመካከላቸው ፍትሃዊ ትሆናለች።

የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንድህ ብለዋል

🔃قال عَلَيْهِ الْصَّلَاةُ وَالسَّلَامُ " اعْدِلُوا بَيْنَ أَوْلَادِكُمْ ،اعْدِلُوا بَيْنَ أَوْلَادِكُمْ

በልጆቻችሁ መካከል ፍትሀዊ ሁኑ! በልጆቻችሁ መካከል ፍትሀዊ ሁኑ
!
ይህ ሀድስ በሱነን አቢ ዳውድ የተዘገበ ሲሆን። በዚህ አይነት መልዕክት ያላቸው ብዛት ያላቸው ሐድሶች ከነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ተወርተዋል።

ቤቷ ውስጥ የምትረጋጋ!
➩➩➩➩➩➩➩➩➩➩➩

ከመልካም ሚስት መገለጫ ባህሪያት መካከል ቤቷ ውስጥ ረግታ የምትቀመጥና ወጣ ገባ ያማታበዛ መሆኗ ነው! ከቤት ከወጣችም ለጉዳይ ካልሆነ በቀር አትወጣም። እንድሁም ከቤቷ ተገላልጣና ተራቁታ አትወጣም! ዓይኗንም (በሸሪአ የተከለከለ ነገር ከመመልከት) ትጠብቃለች! ሰበር ታደርጋለች ብልቷንም (ከሀራም) ትጠብቃለች

ይህንን በተመለከተ የተወሰኑ የቁረአንና ሀድስ አስረጂዎች ከፊት አሳልፈናል ከእነዚህም መካከል ኢማሙ አጠበራኒ "አል አውሰጥ"በተሰኜ ኪታባቸው ሳሊም ቢን አብዲላህ ቢን ኡመር ከአባታቸው እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንድህ ብለዋል ፦

🔃المَرْأَةُ عورةٌ خرجتِ استشرفها الشَّيطان ، وإِنَّها لاتكونُ أقرْبَ إلى اللّٰهِ منها فِي قَعْرِبيتها.

ሴት ልጅ " ዐውራህ" ናት ከቤት ከወጣች ሸይጣን
ያሱባታል (የአላማው መምቻ) ያደርጋታል፤ ወደ አላህ የበለጠ ቅርብ የምትሆነው ቤቷ (ጓዳዋ)ውስጥ ስትሆን ነው



✍️ኢንሻአላህ ይቀጥላል

የመልካም ሚስት ስብዕና ከሚለው ከአብዱረዛቅ ቢን ዐብዱልሙሕሲን አልበድር ኪታብ የተወሰደች!

የፋሩቅ እናት

📚አንብብ! ከማንበብ ብዙ እውቀት ይገኛል

ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1