💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
✍️አድስ ተከታታይ ፁሁፍ 🖋ያንተ ጓደኛህ ማነዉ ?! ➫➫➫➫➫➫➫➫ ➲ክፍል አምስት ➤በአላህ ፍቃድ ከክፍል 4 የቀጠለው ክፍላችን ይሆናል የመልካምን ጓደኛ ባህሪ እያየን ነበር እንቀጥላለን ኢንሻ አላህ ። ➑➛ሓራም ነገር ላይ ከወደቅክ በቁርአን እና በሓዲስ የሚገስፅህ !! ➲በአሁን ግዜ ኣላህ ያዘነለት ካልሆነ በስተቀር ይህንን ባህሪ ያለው ጓደኛ ያለው በጣም አናሳ እና የተመናመነ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
✍️አድስ ተከታታይ ፁሁፍ

🖋ያንተ ጓደኛህ ማነዉ?!
➬➬➬➬➬➬➬

➲ክፍል ስድስት

➤በአላህ ፍቃድ ባለፉት ክፍሎቻችን ላይ የመልካም ጓደኛን የተወሰኑ ባህሪዎችን ለማየት ሞክረን ነበር ዛሬም የምንቀጥል ይሆናል ኢንሻ አላህ ።

❶❶➛ሚስጥርህን የሚጠብቅ !!

➤ጓደኛ ተብሎ ሚስጥርህን ካልጠበቀ ይሄ ጓደኛ አይባልም ጓደኛ ማለት ከርሱ ጋር ሆንክም ብቻክን ሆንክ ሚስጥርህን የሚጠብቅ ማለት ነው እንጅ ሚስጥህን ካልጠበቀማ ይሄ ጓደኛ ሊባልም አይችልም ወንድሜ።

➲ሚስጥርህን ከንግግርም ሊሆን ይችላል ከሌላም ነገር እንዲሁም ዓይብህን የሚሸፍንልክ መሆን አለበት ያንተን ጉድለትህን እና ሚስጥህን በየአደባባዩ የሚያሰራጭ መሆን የለበትም ።

➤ልብ በል እንዲህ አይነት ጓደኛ የሰይጣን ባልደረባ ነውና ተጠንቀቀው ምን አይነት ካልከኝ ያንተን ሚስጥር የማይጠብቅና ያንተ ዓይብ በየአደባባዩ የሚናገር ስለዝህ ተገንዘብ ጓደኛህ ማነው ??

➲ሰው ጓደኛህ ሁኖ እንደገና እንኳ ብትጋጨው በፍፁም ሚስጥሩን ልታወጣበት አይገባም ያዝለት ዓይቡን ሸፍንለት አላህ ያንተንም በአኼራህ ይሸፍንልካልና ።

⓬➛ከምዕራባዊያን ፋሽን የራቀ !!

➤በተለይ በአሁን ግዜ በምዕራባዊያን ፋሽን ያልተለከፈ ጓደኛ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው አላህ ሲገጥምህ ነውና ይህንን ጓደኛ አጥብቀህ ያዘው የነዝህን ፋሽን የማይከተልም ከሆነ ።

➲የምዕራባዊያንን ፋሽን ተከታይ ከሆነ ለሱና ያለው ቦታ በጣም አናሳ ስለሚሆን እሱ በተለከፈበት በሽታ አንተንም እንዳያስታትምምክ እንዳያጣብቅብክ ራቀው አደገኛ #ቫይረስ ነውና ይህ በሽታ ።

➲ ሱናን ሳይከተል በምዕራባዊያን ፋሽን ተጠምዶ እነዝህን ከተገበረ ፦

➧ ልብሱን ከቦጫጨቀ !
➧ ፁጉሩን እንደ አውራ ዶሮ ከቆለለ !
➧ሱሪዉን ከጎተተ !
➧ ሀፍረተ ገላውን እየገለጠ ከሄደ !
➧ ሴቶችን የሚጨብጥ ከሆነ !
➧ሱና ተከታይ የሆኑ ሰዎች ላይ ካፌዘ !

➬እናም የመሳሰሉ ባህሪ ካለበት ተወው ወንድሜ ላንተ ምንም አይጠቅምክም ከቻልክ ምክረው ።

❶❸ ➛አርቆ አሳቢ መሆን አለበት !!

➤ይህ ማለት እንዳንድ ሰዎች ለነገ ምን አለኝ የሚለውን እና ለወደፊት ምን ሰርቻለሁ ምን ስንቅ ይዣለሁ የሚለውን ነጥብ እንዳለ የረሱ ብዙ ናቸውና ተንቀቅ በል ለነገ ሀሳቢ መሆን አለበት ወንድሜ።

➲ ለነገ ማሰብ ማለት ያገኘነውን ሁሉንም እናጥፋ እናባክን ለነገ አላህ አለ እያለ ወደ ገንዘብን ማባከን የሚመራህ እናም ከዝህ በከፋ መልኩ ደግሞ ለአኼራው ምን እንዳስቀደመ የማያውቅ ከሆነ ነው ።


▪አላህ እንዲህ ይላል ፦
" እናተ ያመናችሁ ሰዎች አላህ ፍሩ ሁሉም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት " ።

➤ይህ የአምላካችን ቃል ነው እንግዲህ አላህ እንዳለው ያስቀደማችሁትን እዩ እያለን ነውና ለነገ ምን እንዳስቀደምን ካላወቅን አደጋ ነውና ጓደኛ ተብሎ ራሱን ከረሳ ሰውም መሆን አይጠበቅብንም ።

➧ክፍል ሰባት ይቀጥላል ኢንሻ አላህ.........✍️

✍️አብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/abuUseyminabdurehman
https://t.me/https_Asselefya1
የስልክ አጠቃቀማችንን እናሳምር !

ሣይታሰብ ሊመጣ የሚችለውን ሞት እናስታውስ! ነገ ሟቾች ነን!

ጨለማውን ቀብር እናስታውስ !

አጠገባችን ማንም፣ ምንም ሣይኖር አሏህ ፊት መቆም አለ !

የማይቻለው ና ከባድ የሆነው የእሳት ቅጣት አለ !

ከዚህም ጋር ፣ ሐራም ነገርን በመመልከትና በመስማት ደስተኛ ህይወትን መግፋት በፍፁም አይታሰብም ! በአምላክህ ላይ አመፀኛ እየሆንክ ደስታን እጎናፀፋለሁ ማለት ቂልነት ነው!


አሏህን እንፍራ !

ስልኮቻችን የተከለከሉ ነገሮችን መስሚያ ና መመልከቻ ከሚሆኑ ከነ አካቴው አለመጠቀሙ ይሻላል !


https://t.me/Muhammedsirage
➲እውቀት ፈላጊዋ እህቴ!
➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱

ቢስሚላሂ ብየ ልጀምር ፅሁፌን
በረካ ፈልጌ ከዚያም ለማመስገን
ለትልቁ ጌታ ለአርሹ ባለቤት
በሙሉ ጌታየ ጉድለት ለሌለበት
አንቺ ውድ እህቴ ኢልም ፈላጊዋ
የጀነቷ ጓደ አንቺ ከርታታዋ።


ወደድኩሺ ወደድኩሺ በጣምም ወደድኩሺ
ኢልም ፈላጊዋ ለእኔ ልዩኮ ነሺ
እውቀት ለማገኘት ቤተሰብ ርቀሺ
አቂዳን ለመማር ከሀገርሺ ወተሺ
ይገርመኝ ነበረ በጣሙን ባልወድሺ
ትንሹን ልገርሺ ትንሹን ላስታውስሺ
ከእሙ ሀብለና ከደካማዋ እህትሺ።


በኢልም ላይ ሆነሺ ፈተናሺ ቢበዛም
ቢርብሺ ቢጠማም ብርዱ ቢበረታም
ኢንሻአላህ ታገሺ ያልፋል እህት አለም
አንችኮ ታላቅ ነሺ አላህ የመረጠሺ
ቁረአንና ሱናን ያደረግሺ መመሪያሺ


➷አረ አንቺ ልዩ ነሺ
እህት አለም አይተሻቸዋል ግን
በየ መጠጥ ቤቶች የሚጃጃሉትን
በቁርአን በሀድስ የሚያላግጡትን
ኒቃብን ረግጠው እርቃን የወጡትን
አጅነብይ ወንድ ጋር የሚማግጡትን
።

➷አስቢ እንጂ ውዴ
ታዳ ከእነዚህ ጋር በምን ተገናኝተሺ
ሰላም መረጋጋት ኢማንን አድሎሺ
አላህ በትዕዛዙ ከመጥፎ ጠብቆሺ
ምስጋና አቅርቢ እንጂ ለታላቁ ጌታሺ
የሴቶች አለቃ የምርጥ ምርጥ ነሺ


➷አህባሺ ቢውተረተር ክብርሺን ለማጉደል
ኢልም እንዳታገኚ ኢኽዋን ቢታገል
ከእነሱ ፈተና እራስሺን አግለሺ
ኢልምን ለመፈለግ መንገድሺን ጀመርሺ
በሰለፍያ ላይ መጓዝን ከፈለግሺ
አልጋ በአልጋ አይሆንም ይበዛል ፈተናሺ
እይ እስኪ ቀደምቶች እንደት እንደለፉ
በስቆቃ እንግልት ሂወትን ያለፉ
ሰዎችን ለማቅናት በጣሙን ቢለፉ
ታሰሩ ተመቱ በጣም ተገላቱ

ህይወትንም አጡ በእየ እስር ቤቱ።

ለድናቸው ሲሉ ይሄን ካሳለፉ
ታድያ ለምንድን ነው ያንቺ መርበትበቱ

👉እህቴ ልገርሺ

ዛሬ በኢልም ላይ ትንሹን ካልታገልሺ
መሆንሺ አይቀርም ውዳቂና እርካሺ
ስለዚህ ታገሺ የዛሬን ፈተና
ጀሊሉ እንድሰጥሺ በአኼራ ላይ ጀና
መታገሉ አይከፋም ዛሬ በዱኒያ
ለቤተሰቦችሺ እንድትሆኚ መመሪያ
አላህ ይወፍቅሺ ኢልም በኢልም ላይ
የበላይ ያድርግሺ ነገም በጀነት ላይ።


✍ከእሙ ሃብለና ከአል ኢህሳን ተማሪ
➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
متن أصول الثلاثة ٦
Abu Useymin
ተከታታይ የኪታብ ደርስ
➖➖➖➖➖➖➖

📚ኪታብ ኡሱሉ ሰላሳ

            ➧ክፍል 
❻

🎙በአብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1

@abuUseyminabdurehman
~አትንኩት ወንድሜን ህመሙ ያመኛል!
~ጊዜውን ሰውቶ ለድኑ ሚለፋ ከቶ የት ይገኛል!!

~ተው አትንኩብኝ ሰለፍይ ወንድሜን!
~የዱኒያ መካሪ አኼራ አሰታዎሸን !!

~ተውሒድ አሥተማሪ  ከሸርክ!
~ አሰጠንቃቂ  ግማሸ አካላቴን!! 

~ህመሙ ያመኛል ሱና ሲያዋድደን!
~ተውሒድ አንድ አርጎናል ኢስላምም ፈቅዶልን!!

~ስለዚ ተፋቱት ስራውን ይስራበት !
~ሀቅ አይጥሜ ሁላ ዛቻክን አንሳላት!
~ነገሩ ልፋጅ እሱ አይበገርም ዋሂዱ እያለለት!!

~አሏህዬ የሀቅ ሰወችን ለሀቅ የሚለፉትን አንተ ጠብቃቸው አንተ ደስታን ለግሳቸው አሚን!!

https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
➧ሁለቴ የሚወዱን ሰዎች በርግጥም እውነትም እውነትም ይወዱናል።

አንደኛው
- ሳያዩን እንዲሁ ሲስሉን

ሁለተኛው
- በአካል ሲያዩንና ሲያገኙን
Audio
☞አዲስ ሙሐደራ

የልብ ድርቀት እና ስልክ

በሙሐመድ ሲራጅ መ/ኑር

ሙሉ እና አጠር ያለ ሙሐደራ
https://t.me/Muhammedsirage
➧ቆጨኝ አሁን አሁን!!

ቆጨኝ አሁንማ እውቀት እየራበኝ
የለጋነት እድሜ ሣላቀው አለፈኝ
ሸሪአን ዘንግቼ ሡናን እረስቼ
እስከዛሬ ኖርኩት እንዲህ ተሳስቼ
ከእኔ የባሱ ያሉኝ ጒደኞቼ
ምንም ሣናጠና በአጉል ፈተና

ዲንን ችላ በለን ሳይኮ ስናጠና
አልመልሠው ነገር አሁን ቆጨኛና
ፊዚክስ ኬሚስትሪ እያልን ሂስትሪ
ዘንግተን ሣናቀው የተውሂድን ጥሪ
አቤት ጭንቀት ያኔ ልናልፍ ሚንስትሪ
ቀን ማታ በጥናት ሆነንም አዳሪ
የኢስላም መሠረት የኢማን ግንባታ

የለም እኛ ጋራ በሌላ ጨዋታ
ምላሳችን ብቻ ናት ሙሲሊመኛ
ተግባራችን ደሞ ለልብ መዝናኛ
ስሜትን ተከታይ ለዲን ቸልተኛ
አሁን በጭንቀቴ እንዴትስ ልተኛ
ምደርስም አይመስለኝ የጊዜ እራብተኛ
ሁሉም ግልፅ ሲሆን ሰአት ጠበበኛ
!!

➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
በዚህ ፊትና በበዛበት ዘመን
በኒቃብ ላይ ጠንካራ አቋም ያለዉ
ጀግና ወንድ መኖሩ እጂጉን ያኮራል!


➘በኒቃብ ላይ ጠንካራ አቋም ያላችሁ ወንድሞች አላህዬ ይጠብቃችሁ ፀናቱ ይስጣችሁ!

➘ሓቂቃኮ ስንት ደዩስ አለ አላህ ረድቷት ለብሳ
እሱ ግን የሚያስወልቃት ደነዝ ወንድ አለ እህ!

➘አላህ ሆይ ለእህቶቼ በኒቃብ ጠንካራ የሆነ በሁሉም ነገር ብርቱ ጀግና ወፍቅልኝ!
!
➷➷የሱብሒን ሶላት ለመስገድ በሌሊት ጨለማ ወደ መስጂድ የሚሄድ ሰው ፡ የቂያማ ቀን ኑር (ብርሃን) ለብሶ ከአላህ ጋር ይገናኛል።

ረሱል ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም
ምንጭ፦ ሶሒሁ ተርጊብ ወት ተርሒብ (1/171)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
➲ጣፍጭ  ቲላዋ  ግብዣ!

➧ቁረአን የልብ ብረሀን የዱኒያ የአሄራን ሂወት የሚያቀና ውብ የአላህ ቃል የማይጠገብ!

https://t.me/https_Asselefya1
متن أصول الثلاثة ۷
Abu Useymin
ተከታታይ የኪታብ ደርስ
➖➖➖➖➖➖➖

📚ኪታብ ኡሱሉ ሰላሳ

            ➧ክፍል 
❼

🎙በአብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1

@abuUseyminabdurehman
📲 ተንቀሳቃሽ ስልክ እና አደቦቹ
አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
📱خُطْبَةُ الْجُمُعَةِ
📱የጁሙዓ ኹጥባ

📲 الهاتف النقال وآدابه
📲 ተንቀሳቃሽ ስልክ እና አደቦቹ

🕌 ደሴ አል-አዝሐር መስጂድ

📅محرم/28/ 1444

🎙አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
      ↓↓↓
t.me/abu_reyyis_arreyyis/6281
t.me/abu_reyyis_arreyyis/6281
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ حَقَّ تُقَاتِهِ وَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ

• { سورة آل عمران } •