💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የላኢላ_ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➢ክፍል ⓶ ⓶ኛ የቂን፦ ሌላኛዉ የላኢላ ሃኢለሏህ መስፈርት ምንም ሳያወላዉሉ እርግጠኛ ሆኖ መልዕክቷን ማመን ነዉ። በያዘችዉ መልዕክት እርግጠኛ ሆኖ ያላመነ ተጠራጣሪ ነዉ። ➲በልቡ የሚጠራጠር ሰዉ ደግሞ በምላሱ ላኢላ ሃኢለሏህ ማለቱ ፍፁም ፍይዳ የለዉም። በተነፈሰ ቁጥር ላኢላ ሀኢለሏህ ቢልም እንኳን።…
➲የላኢላ_ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫
➛ክፍል⓷

⓸ኛዉ መስፈርት እዉነት ብሎ ማመን፦የላኢላ ሃኢለሏህን መልዕክት እዉነት ብሎ ያላመነ አስተባባይ ነዉ። ላኢላ_ሃኢለሏህ ደግሞ እዉነት ብሎ ለተቀበለ ብቻ ነዉ የምትጠቅመዉ!!

➧ነብዩ ሰለሏህ አለይሒ ወሰለም(አንድ ሰዉ ከልቡ እዉነት ብሎ'ከአሏህ በስተቀር እዉነተኛ አምላክ የለም። ሙሀመድም ባሪያዉና መልዕክተኛዉ ናቸዉ ብሎ የሚመሰክር የለም'በእሳት ላይ እሱን አሏህ እርም የሚያደርገዉ ቢሆንጂ ይላሉ። (ቡኻሪ 128)

⓹ኛዉ መስፈርት ኢኽላስ፦ይሄኛዉ የላኢላ ሀኢለሏህ መስፈርት ደግሞ አምልኮትን አሏህን ብቻ በማሰብ መፈፀምን የሚመለከት ነዉ። አምልኮን ለአሏህ ብቻ ሳያደርግ ለፈጣሪም ለፍጡርም የሚሰጥ አካል ላኢላ ሃኢለሏህ ከነ መሰረቷ ንዷታል። ቀድሞ ነገር ላኢላ ሃኢለሏህ ከማለት ይሄ ይሄ እንጂ ምን ተፈልጎ!? ጌታችን አሏህ እንዲህ ይላል፦

(አላህን ሃይማኖትን ለርሱ ብቻ የሚያጠሩና ቀጥተኞችም ሆነዉ እንዲያመልኩትንጂ አልታዘዙም።)[አልበይናህ፡5]

➲ነብዩ ሰለሏህ አለይሂ ወሰለም እንድህ ይላሉ፦ ላኢላ ሃኢለሏህ ያለን ሰዉ_ይህን ማለቱ (የአሏህን ፊት የሚያስብ ከሆነ አሏህ በእሳት ላይ እርም አድርጎታል) ይላሉ።(ቡኻሪ ፡425 ሙስሊም:1528)

⓺ኛዉ መስፈርት መቀበል፦በተጨማሪ የላኢላ ሃኢለሏህን መልዕክት ያለ ምንም ማመንታት አሚን ብሎ መቀበል ያስፈልጋል። ያለበለዚያ እንቢተኛ ነዉ ማለት ነዉ። መልዕክቷን ያለ መቀበል ፍቃደኛ ያልሆነ እምቢተኛ ትርጉሟን በጥንቃቄ ማወቁና እዉነት እንደሆነም እርግጠኛ ሆኖ መረዳቱ በምንም መልኩ ሊጠቅመዉ አይችልም። አጋሪዎች አስመልክቶ ጌታችን ምን እንደሚል እንመልከት፦(እነሱ 'ከአሏህ ሌላ እዉነተኛ አምላክ የለም'በተባሉ ግዜ ይንጠባረሩ ነበር።''አኛ ለአንድ እብድና ባለቅኔ ብለን አምላኮቻችንን የምንተዉ ሰዎች ነን? ይሉም ነበር [አስሷፍት35_36] እናም የላኢላ ሃኢለሏህ መልዕክት መረዳቱ፣የቂን ብሎ ማወቁ፣ እዉነት ብሎም ማመኑ ቢኖር፤ የያዘችዉን መልዕክት ለመቀበል ዝግጁ እስካልሆነ ድረስ ሰዉየዉ አማኝ አይባልም። አቡ ጧሊብና በርካታ አይሁዳዉያን የሙሐመድ ሰለሏህ አለይሂ ወሰለም እዉነተኛ ነብይነት በተለያዩ አጋጣሚዎች ተናግረዋል። መልዕክቱን ስላልተቀበሉ ግን እንደ ሙስሊም አልታሰቡም።

➛ ኢንሻ አሏህ
ይቀጥላል


📚ተውሂድ የሁለት ሀገር ስኬት ቁልፍ ከሚለው ከኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ኪታብ የተወሰደ
✍ام عثيمين

JOIN በማለት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ ተጠቃሚ ይሆናሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የተዘረጋው የአላህ ገመድ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ክፍል ስምንት 〰〰〰〰〰 ➭ልብን “ረቢዓ ቀልቢ” (የልቦናዬ (ለምለም) ጨፌ) በማለት ሲያወሳ ደረትን ደግሞ“ኑረ ሶድሪ” (የደረቴ ብርሃን) በማለት ገለጸው፡፡ ምክንያቱም ደረት ልቦናን ያቀፈ ወይም ያካበበ ነው፡፡ ደረት ሲያበራ በውስጥ ያለው አካል ሁሉ ያንጸባርቃል፡፡ ልብ ለመልካም ነገሮች ከተገጠመች የትሩፋቶች ሁሉ ምንጭ በመሆኗ “ረቢዕ”…
➲የተዘረጋው የአላህ ገመድ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል ዘጠኝ

➽ትክክለኛ የቁርኣን ንባብ በሶስት ነገሮች ካልሆነ ሊሟላ አይችልም
➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬

⓵ቁርኣንን ባማረ ሁኔታ በማንበብ እና በቻለው አቅም በቃሉ በመሸምደድ

⓶ መልዕክቱን በመገንዘብና በመረዳት

كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ إِلَيْكَ مُبَارَكٌ لِّيَدَّبَّرُوا آيَاتِهِ وَلِيَتَذَكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ

“(ይህ) ወደአንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው፡፡ አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው
)፡፡” ሷድ 29

أَفَلَمْ يَدَّبَّرُوا الْقَوْلَ
◆የቁርኣንን ንግግሩንም አያስተነትኑምን?” አል ሙእሚኑን፡68

➢የአንድ ሙስሊም ሐሳብና ጭንቀት ቁርኣንን ማንበቡ ወይም የጀመረውን ምእራፍ መች እንደሚያጠናቅቅ ሳይሆን መቼ ነው የቁርኣንን ጽንሰ ሐሳብ የምገነዘበው? የአላህን ቃል መቼ ነው የምረዳው? መቼ ነው ከልቤ ላይ ሰርጾ የሚገባው? መቼ ነው በቁርኣን የምሰራው? መቼ ነው በቁርኣን እንደተወሱት እውነተኞች የምሆነው? መቼ ነው ከጸጸተኞች ፣ ከተመላሾች ፣ ከአስታዋሾች ፣ ከሰጋጆች ፣ አላህን ከሚታዘዙት ፣ሶደቃ ከሚሰጡት የምሆነው? የሚለው ነው አንድን ሙስሊም ሊያሳስበው የሚገባው፡፡

➧አጁርሪይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-“ንግግሩን የተገነዘበ ጌታውን ፣ የጌታውን ታላቅ ስልጣን እና ችሎታውን ይገነዘባል፡፡በሙእሚኖች ላይ የቸረውን ታላቅ ስጦታ ያውቃል፡፡ በእርሱ ላይ ያለበትን የዒባዳ ግዴታዎች ይርረዳል፡፡

➠ ዋጅብ የሆኑትን ነገሮች በነፍሱ ላይ አጥብቆ ይይዛል ፣ የተከበረው ጌታ ያስጠነቀቀውን ይጠነቀቃል ፣ እርሱ የወደደውን ይወዳል ፡፡ ባህሪው ይህ የሆነ ሰው ቁርኣንን ሲቀራ ከሌሎቹ ሲያደምጥ ለእርሱ ፈውስ ይሆንለታል ፣ ገንዘብ ባይኖረውም በእርሱ ብቻ ይብቃቃል፣ ይረካል ፤ ያለዘመድ ልቅናን ያገኛል ፤ ሌላው ብቸኝነት ሲሰማው እርሱ በሐሴት ይዋጣል፡፡


➧ቁርኣንን ለመቅራት ከፈት ሲያደርገው በምቀራው መች ነው የምገሰጸው? የሚለውን እንጅ መቼ ነው ይህን ቁርኣን የማጠናቅቀው?የሚለው የእርሱ አላማ አይሆንም፡፡ ፍላጎቱ የአላህን ንግግር መቸ ነው የምገነዘበው? በአላህ ንግግር መቸ ነው የምገሰጸው? መቸ ነው የማስተነትነው? የሚለው ይሆናል።ምክንያቱም ቁርኣንን ማንበብ ከአምልኮቶች አንዱ ነው፡፡

ስለዚህ ከሚዘነጉ ሰዎች አትሁን፡፡ ለዚህም መልካም ተግባር የሚገጥምህ አላህ መሆኑን ተገንዘብ፡፡
” አኽላቁ ሃመለቲ አል ቁርኣን ሊል አጁሪ፡ ገፅ10

➳ይህን ለማረጋገጥ ቁርኣንን በደንብ ያነባል ፣ ነፍሱን ይታገላል፡፡

➧ይህን አስመልክቶ ኢብን አል'ቀይም - ረሂመሁሏህ - “ሚፍታሁ ዳሪ አስ’ሰዓዳ”
በተባለው ኪታባቸው የሚከተለውን ተናግረዋል፡-“የቁርኣንን አንቀጽ በማስተንተንና በመገንዘብ ማንበብ ፣ ያለምንም መገንዘብና መረዳት አጠናቆ ከማንበብ የበለጠና የተሻለ ነው፡፡ ለልቦና በጣም ጠቃሚ ፣ ኢማን ለማግኘት ቀስቃሽ ፣ የቁርኣንን ጣፋጭነት ለመቅመስ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያለው ነው፡፡” ሚፍታሁ ዳሪ አስ ሰዓዳ፡1/172

➛ኢንሻአላህ ይቀጥላል◉◉◉◉◉◉✍

📚አንብብ ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋልና

https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️ተከታታይ የቂርአት ፕሮግራም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➡️ ሸርህ አቂደቱል ዋሲጥያ የፈውዛን

☑️ አህለሱናዎች
▪️ቀደርዮች
▪️ኸዋሪጆች
▪️ሙርጂአዎች
▪️አህባሾች
☑️ ብዙ የቢድአ ቡድኖች ተወስቶበታል

➰ክፍል ⑧➰
〰〰〰〰

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የላኢላ_ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➛ክፍል⓷ ⓸ኛዉ መስፈርት እዉነት ብሎ ማመን፦የላኢላ ሃኢለሏህን መልዕክት እዉነት ብሎ ያላመነ አስተባባይ ነዉ። ላኢላ_ሃኢለሏህ ደግሞ እዉነት ብሎ ለተቀበለ ብቻ ነዉ የምትጠቅመዉ!! ➧ነብዩ ሰለሏህ አለይሒ ወሰለም(አንድ ሰዉ ከልቡ እዉነት ብሎ'ከአሏህ በስተቀር እዉነተኛ አምላክ የለም። ሙሀመድም…
➲የላኢላ ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➳ ክፍል⓸

⓻ኛዉ መስፈርትመዉደድ፦ ሌላኛዉ መስፈርት ደግሞ ላኢላ ሃኢለሏህን ፣መልዕክቷን እንድሁም እሷን የተሸከሙ ሰዎችን መዉደድ ነዉ።

➠ላኢላ ሃኢለሏህ የሚል ሰዉ ከምንም በላይ አሏህን ይወዳል።

➠ከሰዎችም ከአሏህ ሌላ ባላጣዎችን የሚይዝ አለ።ልክ አሏህን እንደሚወዱት ይወዷቸዋል። እነዚያ ያመኑት ግን አሏህን በመዉደድ(ከእነርሱ)ይበልጥ የበረቱ ናቸዉ።
{አልበቀራህ፡165}

➧ከምንም በላይ አሏህን የወደደ ሰዉ ደግሞ እሱ ወዶና መርጦ የላካቸዉን ነብይ የሂወቱ መመሪያ አድርጎ ይከተላል።(''አሏህን የምትወዱ ከሆነ ተከተሉኝ አላህ ይወዳችኋዋልና'' በላቸዉ።(አል ኢምራን:31)

➻አላህ የሚወደዉን መዉደድ እንዲሁም የአሏህ ደጋግ ባሪያዎችን መዉደዲም ላኢላ ሃኢለሏህ ከሚል ሰዉ የሚጠበቁ ነገሮች ናቸዉ።

➧ነብዩም ሰለሏህ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፦(ሶስት ነገሮች በዉስጡ ያሉበት ሰዉ የኢማንን ጥፍጥና አጣጥሟል ፦

⓵ኛው እሱ ዘንድ አሏህና መልዕክተኛዉ ከነሱ ዉጭ ካሉ ሁሉ ይበልጥ የተወደዱ ሊሆኑ ነዉ።

⓶ኛው አንድን ሰዉ ለአሏህ ሲል ብቻ ሊወዲ ነዉ።

⓷ኛው አላህ ከሱን ከክህደት ካተረፈዉ ቡሀላ ወደ ክህዴት መመለስን ልክ ከእሳት ዉስጥ መወርወርን የሚጠላዉን ያክል ሊጠላ ነዉ
።(ቡኻሪ 16፣ሙስሊም፣174)

➧ስለዚህ አሏህን የሚወድ ሰዉ ከምንም በላይ የአሏህን ፍላጎት ያስቀድማል።

➧አሏህ የሚወደዉን ይወዳል፣ የሚጠላዉንም ይጠላል።

➲የላኢላ ሃኢለሏህ አንኳር መልዕክት የሆነዉን ተዉሒድና የተዉሒድ ሰዎች እየጠሉ በምላስ ላኢላ ሃኢለሏህ ማስተጋባቱ ይጠቅማል ብሎ ማሰብ ዘበት ነዉ።

📚ተዉሒዲ የሁለት ሀገር የስኬት ቁልፍ ከኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁሏህ መፀሃፍ የተወሰዴ!!

✍أم عثيمين

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
↪️አቢ ሙሳ አላህመልካም ስራውን ይውደድለትና እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ እንድህ ብለዋል

➡️ሶስት አይነት ሰዎች ጀነት አይገቡም!!
▪️አስካሪ መጠጥ አዘውታሪ
▪️ዝምድና ቆራጭ
▪️ሲህር እውነት ነው ባይ

📚رواه أحمد وٱبْنُ حِبّٓان في صحيحه
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲መንዙማ ➬➬➬➬➬ ➢ክፍል አምስት ➧ልብ በሉ በዚህ ግዜ አማልክት ተብለውም አልተጠሩም። ሸይጧን ግቡን ለማሳካት ሩቅ ነው የሚያልመው።ከዚያም ይህ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ሲተካና፣እውቀትም ሲጠፋ “አባቶቻችሁ ዝናብ ሲቸግራቸው እነሱን ነበር የሚጠይቁት” ብሎ ታላቁ ወጥመዱ ውስጥ ከተታቸው። ከዚያም ተቀበሉት። በዚህም ምክንያት አላህ ለምድር ህዝቦች የመጀመርያውን መልክተኛ ኑሕን (ዐለይሂ…
➲መንዙማ
➫➫➫➫➫➫

➛ክፍል ስድስት


➧ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ወደ ምን አይነት ሰዎች ነበር የተላኩት?
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰


➲ሁሉም ነብይ ወደ የህዝቡ ሲላክ ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ግን ባጠቃላይ ለአለማት እዝነት ተደርገው ነው የተላኩት።ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ለምን አይነት ህዝቦች እንደተላኩ ማወቃችን ወሳኝ ነጥብ ነው።
ምክንያቱም ዛሬ አብዛኞች የነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ተከታዮች ነን እያሉ በተግባር ግን ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (የተዋጓቸውን የነ አቡ ጀህልን መንገድ ሲከተሉ ይታያሉና።

➧ከላይ “የሰው ልጆች እንዴት አላህ ላይ ማጋራት ጀመሩ” የሚለውን ዋና ነጥብ
አይተን ነበር። በነጥቡ ላይ የሺርክን አደገኝነት እና የመጀመርያው ሺርክ በምን ምክንያት እና በማን ሰባኪነት እንደተፈጸመ አይተናል። አሁን ደግሞ ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ለምን አይነት ሰዎች ተልከው እንደነበር ማወቃችን የሺርክ አደገኝነት አውቀን በአላህ ፍቃድ ከባድ ጥንቃቄ እንድናደርግ ያግዘናል፣ ይረዳናል።


➧ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (የተላኩባቸው ህዝቦች ሐጅ የሚፈጽሙ፣ ምጽዋት የሚለግሱ እና ሌሎችንም ስራዎች የሚተገብሩ ነበሩ። ግና ይህ ተግባራቸው እስልምና ውስጥ አላስገባቸውም። ምክንያቱም አምልኮ ሲፈጽሙ በአላህ ላይ አጋርን ይጨምሩ ነበርና። በዚህም ነው ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (የተጋደሏቸው።

ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (የተላኩባቸው ህዝቦች አላህ ብቸኛው የሁሉ ፈጣሪ፣ ሁሉን አስተናባሪ፣ ሲሳይ ሰጪ መሆኑን ያምኑ ነበር። ለዚህም የሚከተሉት የቁርኣን አንቀጾች ግለጽ ማስረጃ ናቸው።

وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَسَخَّرَ الشَّمْسَ وَالْقَمَرَ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۖ فَأَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ

ከሰማይም ውሃን ያወረደና በእርሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ሕያው ያደረጋት ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው “አላህ ነው” ይሉሃል። “ምስጋና ለአላህ ነው” በላቸው። ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም። አንከቦት 61

وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَهُمْ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۖ فَأَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ

ማን እንደፈጠራቸውም ብትጠይቃቸው “በእርግጥ አላህ ነው” ይላሉ። ታዲያ (ከእምነት) ወዴት ይዞራሉ?አዙህሩፍ 87

قُل لِّمَنِ الْأَرْضُ وَمَن فِيهَا إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ●قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ السَّبْعِ وَرَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَتَّقُونَ●قُلْ مَن بِيَدِهِ مَلَكُوتُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ يُجِيرُ وَلَا يُجَارُ عَلَيْهِ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ●سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ فَأَنَّىٰ تُسْحَرُونَ
“ምድርና በውስጥዋ ያለው ሁሉ የማን ነው? የምታውቁ ብትሆኑ (ንገሩኝ)” በላቸው።“በእርግጥ የአላህ ነው” ይሉሃል። “ታዲያ አትገሰጹምን?”በላቸው። “የሰባቱ ሰማያት ጌታና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን ነው?” በላቸው። “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል። “እንግዲያ አትፈሩትምን?” በላቸው። የነገሩ ሁሉ ግዛት በእጁ የሆነ እርሱ የሚጠብቅ በእርሱ ላይ የማይጠበቅ ማን ነው? የምታውቁ እንደሆናችሁ (መልሱልኝ)” በላቸው። “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል። “ታዲያ እንዴት ትታለላላችሁ?” በላቸው። [አልሙእሚኑን፡ 84-89]

📚መንዙማ ከሚለው ከኡስታዝ ሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል◉◉◉

ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️ተከታታይ የቂርአት ፕሮግራም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➡️ ሸርህ አቂደቱል ዋሲጥያ የፈውዛን

☑️ የኢማን ትርጉም
☑️ አርካኑል ኢማን

➰ክፍል ⑨➰
〰〰〰〰

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የተዘረጋው የአላህ ገመድ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➧ክፍል ዘጠኝ ➽ትክክለኛ የቁርኣን ንባብ በሶስት ነገሮች ካልሆነ ሊሟላ አይችልም ➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬➬ ⓵ቁርኣንን ባማረ ሁኔታ በማንበብ እና በቻለው አቅም በቃሉ በመሸምደድ ⓶ መልዕክቱን በመገንዘብና በመረዳት كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ إِلَيْكَ مُبَارَكٌ لِّيَدَّبَّرُوا آيَاتِهِ وَلِيَتَذَكَّرَ…
➽የተዘረጋው የአላህ ገመድ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል አስር

➲ቁርኣንን በፍጥነት አንብቦ ከመጨረስ ነፍስህን በእርሷ የምትፈውስበት ፣ አስተንትነህ ትርጉሟን በደንብ ተገንዝበህ የምታነባት አንዲት አንቀጽ በላጭና በጣም ጠቃሚ ናት፡፡ለዚህ ነው ሰለፎቹ ወይም ቀደምት ደጋጎች በአንዲት አንቀጽ ቆመው ሌሊቱን የሚያነጉት፡፡

ነብዩ صلى الله عليه وسلم በሚከተለው አንድ አንቀጽ ቆመው ሌሊቱን አንግተዋል፡

إِن تُعَذِّبْهُمْ فَإِنَّهُمْ عِبَادُكَ ۖ وَإِن تَغْفِرْ لَهُمْ فَإِنَّكَ أَنتَ الْعَزِيزُ الْحَكِيمُ

“ብትቀጣቸው እነርሱ ባሮችህ ናቸው፡፡ ለነርሱ ብትምርም አንተ አሸናፊው
ጥበበኛው ነህ” (ይላል)
አል ማኢዳህ፡118” አህመድ፡ 21328 አን ነሳኢይ፡1010 ኢብኑ ማጀህ፡1350

➢በትክክለኛ ሐዲስ አቡ ሰዒድ አል'ኹድርይ ረድየሏህ አንሁ የሚከተለውን አስተላልፈዋል፡-አንድ ሶሃባ አንድን ግለሰብ “ቁልሁወሏሁ አሀድን” ደጋግሞ ሲቀራ አደመጠው፡፡ነገሩን እንደቀላል በመመልከት ከነጋ በኋላ ወደረሡል صلى الله عليه وسلم መጣና ነገራቸው፡፡ የአላህ መልክተኛ صلى الله عليه وسلم ግን የሚከተለውን ተናገሩ፡-

"والذي نفسي بيده إنها لتعدل ثلث القرآن"
➧“ነፍሴ በእጁ በሆነው ጌታ እምላለሁ፡፡ እንሆ እርሷ የቁርኣንን አንድ ሶስተኛ
ትመዝናለች
፡፡” ቡኻሪ፡5013

➢ቁርኣንን ያለምንም መገንዘብና ማስተንተን እንዲሁ በስድ ከምታነብ ፣ አንዲትን አንቀጽ በደንብ እያስተነተንክ እና እያስተዋልክ ካነበብክ ነፍስህን እየፈወስክ ፣የልብህን በሽታ እያከምክ ፣ እምነትህን እና ተወኩልህን እያጠናከርክ ፣ ከአላህ ጋር ያለውን እውነተኛነትህንና የጠበቀ ግንኙነትህን በማደስ ከእርሷ ጋር ብቻህን በደስታ ማሳለፍህ የተሻለና በላጭ ነው፡፡

⓷ኛው በተከበረው ቁርኣን መስራት
ሀሰን አል'በስርይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
"أنزل القرآن ليعمل به ، ..."

➧“ቁርኣን የወረደው በእርሱ ሊሰሩበት ነው፤ …” ሚፍታሁ ዳሪ አስ ሳዓዳህ፡1/187

➠ቁርኣን የወረደው ልንሰራበት ፣ ከቁርኣን ባለቤቶች እንድንሆን ነው፡፡ አንድ ሰው
ሀርፉን ፣ አንቀጾችን ፣ ምዕራፎችን በማንበብና በመሀፈዝ ብቻ የቁርኣን ባለቤት ሊሆን አይችልም፡፡ ይልቁንም ትርጉሙን በመረዳትና በመገንዘብ በታላቁ ቁርኣን መስራት ይኖርበታ
ል፡፡

➭ከሶሃቦች ዘመን ቀጥሎ ከሚገኙት ታላላቅ ታብዒዮች መካከል አንዱ የሆኑት ኢማም ሀሰን አል'በስርይ - ረሂመሁሏህ - የዘመኑ ቁራኦችን (ቁርኣን አንባቢዎች) አስመልክቶ የሚከተለውን ተናግረዋል፡፡

➤“አንድ ሰው አንድንም ሐርፍ ሳልጥል ቁርኣንን አንብቤ አጠናቀቅሁ ይላል፡፡ይህን ሲናገር የእርሱ አላማ ሒፍዙንም ተጅዊዱንም አጥርቸና አረጋግጨ አነበብኩት ለማለት ፈልጎ ነው፡፡ ነገር ግን በአላህ ምዬ የምናገረው ሁሉንም ጥሎታል፡፡

ቁርኣን ላይ ያሉ ስነ-ምግባሮችና ተግባሮች ከእርሱ ላይ አይታዩም፡፡ አንዳንዶች በአንድ ትንፋሽ የቁርኣንን ምእራፎች አጠናቅቄ አነበብሁ ይላሉ፡፡ ወሏሂ እነዚህ ቁራኦች አይደሉም የቁርኣንን ህግ በተግባር የሚያውሉም ጥበበኞችም ፣ አላህን ፈሪዎችም አይደሉም፡፡ መቸ ነው እንደነዚህ አይነተ ሰዎች ቁራእ የሆኑት? እንደነዚህ አይነት ሰዎችን አላህ በሰዎች መካከል ቁጥራቸውን አያብዛው!” አዝ ዙህድ ሊብን አል ሙባረክ 793

➤ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የላኢላ ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➳ ክፍል⓸ ⓻ኛዉ መስፈርትመዉደድ፦ ሌላኛዉ መስፈርት ደግሞ ላኢላ ሃኢለሏህን ፣መልዕክቷን እንድሁም እሷን የተሸከሙ ሰዎችን መዉደድ ነዉ። ➠ላኢላ ሃኢለሏህ የሚል ሰዉ ከምንም በላይ አሏህን ይወዳል። ➠ከሰዎችም ከአሏህ ሌላ ባላጣዎችን የሚይዝ አለ።ልክ አሏህን እንደሚወዱት ይወዷቸዋል። እነዚያ ያመኑት…
➲የላኢላ_ሃኢለሏህ መስፈርቶች ሰባት ናቸዉ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል ⓹

➠7ኛው መስፈርት መዉደድ ከትላቱ የቀጠለ፦

ስለዚህ መስፈርቶች ስናወራ ዋናዉ የሚፈለገዉ ነገር በተጨባጭ መልዕክታቸዉን ማስገኛት እንጂ እንዲሁ በጭንቅላት ሸምዲዶ በምላስ መዘርዘሩ አይደለም። ስንት መስፈርቶቿን መቁጠር ሳይችል ላኢላ ሀኢለሏህን በሚገባ የሚያስገኝ አለ?!

➧ስንት በምላሱ እየዘረዘረ መሠረታዊ ነጥቦቿን የሚያጓዲል አለ?!


➠በጥቅሉ ከነዚህ መስፈርቶች የምንረዳዉ ከአስፈላጊ መስፈርቶች የተራቆተ ባዶ ላኢላ ሃኢለሏህ ዋጋ የሌለዉ መሆኑ ነዉ።

➧ታላቁ አሊም ኢብኑ_ ረጀብ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ፦ ''በምላሱ ላኢላ ሃኢለሏህ እያለ ከዚያም አላህን በማመፀና ሸይጧንንና ስሜቱን የሚከተለዉማ በርግጥም ተግባሩ ንግግሩን አስተባብሎታል። ሸይጧንና ስሜቱን በመታዘዝ አሏህን ባመፀዉ ልክ የተዉሒዱን ሙላት አጓዲሎታል ። (ከአላህም የሆነ መመሪያ ሳይኖረዉ ስሜቱን ከተከተለ ሰዉ ይበልጥ የጠመመዉ ማነዉ?!)/ከሊመቱል ኢኽላስ፡28/

➧ሰዎች ለነዚህ መስፈርቶች ከሚኖራቸዉ አያያዝ አንፃር የተዉሒድ ጥንካሬቸዉ ይለያያል።

➩ኢብኑል ቀይም ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ፦ ስለሆነም በተጨባጭ በሆነ መልኩ ከአሏህ በስተቀር እዉነተኛ አምላክ እንዴሌለ የመሠከረን አሏህ በእሳት ላይ እርም አድርጎታል። የዚችን ምስክርነት እዉነታ በሚገባ ያረጋገጠና በተግባር ያስገኛ ሰዉ እሳት ይገባል ማለት ዘበት ነዉ። የላቀዉ አላህም(እነዚያ በምስክርነታቸዉ የፀኑ ናቸዉ)ይላል።እናም ምስክርነት በይፍም፣በስዉርም፣ በልቡ በዉጩም የፀና ይሆናል ማለት ነዉ። ምክንያቱም ከሰዎች ዉስጥ ምስክርነቱ ሸሃዳዉ የሞተ የሆ አለ። ከነሱ ዉስጥ ደግሞ ምስክርነቱ የተኛ አለ_ሲቀሰቀስ የሚነቃ። ከዉስጣቸዉም የተጋደመ አለ። ከዉስጣቸዉም ለመቆም የቀረበ አለ።

➧ባጭሩ የላኢላ ሃኢለሏህ ምስክርነት ከቀልብ ዉስጥ፣ልክሩህ ከአካል ዉስጥ እዳላት ሁኔታነዉ። የሞተ ሩህ አለ።የታመመሩህ አለ። ወደ ሞት የቀረበ አለ። ወደ ህይወት የቀረበ አለ። ሌላ ደግሞ ለአካል ጥቅምና ደህንነት የሚተጋ ሩህ አለ።(አድዳኡ_ወድደዋእ፡302)

➧ከዚህ በመነሳት ህዝባችን በተጨባጭ ያለበት እዉነታ ስንቃኝ የሚታየዉ ነገር አሰፈሪ ነዉ።

➤ኢንሻአላህ ይቀጥላል◉◉◉◉◉◉✍

✅ተዉሒዲ የሁለት ሃገር ስኬት ከሚለዉ ከኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁሏህ መፀሃፍ የተወሰዴ

✍️أم عثيمين
➢ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይቀላቀሉ ይጠቀማሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️ወሳኝ ጥንቃቄ ለዲን ተማሪዎች
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

✅ የምትማርበትን ኡስታዝ፦
☑️ አቂዳውንና
☑️ መንሀጁን ጠንቅቀህ እወቅ


➡️ ይህ እውቀት ስጋህ፣ ደምህና ህይወትህ ነውና ከማን እንደምትወስደው በትኩረት አጢን

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFgdAPPfoRzUemL4vw
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲መንዙማ ➫➫➫➫➫➫ ➛ክፍል ስድስት ➧ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ወደ ምን አይነት ሰዎች ነበር የተላኩት? 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ➲ሁሉም ነብይ ወደ የህዝቡ ሲላክ ነብዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ግን ባጠቃላይ ለአለማት እዝነት ተደርገው ነው የተላኩት።ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ለምን አይነት ህዝቦች እንደተላኩ ማወቃችን ወሳኝ ነጥብ ነው። ምክንያቱም…
➲መንዙማ
➫➫➫➫➫
እውነታው:አደጋዎቹና መዘዞቹ

➧ክፍል ሰባት


➠ልብ በሉ የአላህ ባሪያዎች እነዚህ አጋሪያን የአላህን ጌትነት ማመናቸው ወደ ነብያት ሁሉ ሀይማኖት ኢስላም አላስገባቸውም። ይህም የሆነው አምልኮን በጠቅላላ ለአንድ አላህ ብቻ ስላልፈጸሙ እና አላህንም ከእርሱ ውጭ ያሉትንም ያመልኩ ስለ ነበር ነው።

«ከአጋሪያን ተግባር ውስጥ የሚጠቃለለው ለእርሱ ብቻ የሚገባውን አምልኮ በእርሱ ላይ ሌላን ምንንም ማድረግ የማይችሉ፣ የማይጠቅሙ፣ የማይጎዱ፣ ጥቅምን ለራሳቸው ማምጣት የማይችሉ፣ እራሳቸውን ከጉዳት መከላከል የማይችሉትን ፍጡራን መገዛታቸው ነው። ለዚህም ማስረጃው የሚከተለው አንቀጽ ነው።

وَمَا يُؤْمِنُ أَكْثَرُهُم بِاللَّهِ إِلَّا وَهُم مُّشْرِكُونَ

➧አብዛኞቻቸውም፤ እነሱ (በአምልኮ የተውሒድ ክፍል) አጋሪዎች ሆነው እንጂ በአላህ ጌትነት አያምኑም።” [ዩሱፍ፡ 106]

የዚህ አንቀጽ ትንታኔ እንደሚያሳየው አብዛኛዎቹ አጋሪዎች የአላህን ጌትነት፣ ፈጣሪነት፣ ሲሳይን ለጋሽነት እና አስተናባሪነት ያጸድቁ እንደነበር ነው።

➲ግና አላህን በጌትነቱ እንደነጠሉት በአምላክነቱ አልነጠሉትም። ለብቸኛው ፈጣሪ የሚገባውን አምልኮ ከእርሱ ውጭ ለሆኑ ፉጡራን በማካፈል ነበር አምልኮ የሚፈጽሙት። የአላህን ጌትነት አምነው ተቀብለው በአምላክነቱ ላይ በማጋራታቸው ደግሞ “አማኝ” አላስባላቸውም።

«ለዚህች አንቀጽ ቁርኣን ተርጓሚ የሆኑትን ሶሐባዎች እና ታቢዒዮች የሰጡትን ትርጉም እንመልከት፡-

ኢብን ዐባስ (ረድየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ ይላሉ፡- “ከኢማናቸው ውስጥ ሰማይን ማን ፈጠረው? ምድርን ማን ፈጠረው? ተራራን ማን ፈጠረው? (ተብለው) ከተጠየቁ አላህ ብለው ይመልሳሉ፣ እነሱ ግን አጋሪ ናቸው።

➲ኢክሪማ ደግሞ እንዲህ አሉ፡ “ማን ፈጠራችሁ፣ ሰማያትና ምድርን ማን ፈጠረ ብለህ ትጠይቃቸዋለህ? የእነሱም መልስ አላህ ይሆናል። ይህም ነው በአላህ ላይ ያላቸው እምነት። ከእርሱ (ከአላህ) ውጭ ግን ያመልካሉ።

➧ሙጃሂድ ደግሞ እንዲህ ይላሉ፡- “እምነታቸው አላህ ፈጠረን፣ ሲሳይ ይለግሰናል፣ ይገድለናል ብለው መናገራቸው ነው። ይህ ነው እምነታቸው ከእርሱ ውጭ እያመለኩ.....”

➲ዐብዱረሕማን ኢብን ዘይድ ኢብን አስለም ደግሞ “በአላህ ላይ አንድም የሚያጋራ የለም አላህ ጌታው፣ አላህ ፈጣሪው እና ሲሳይ ሰጪው መሆኑን እያወቀ እና እያመነ ቢሆን እንጂ።
◉
◉

◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📘ዝግጅት መንዙማ ከሚለው ከኡስታዝ ሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ።

✏️መጻፍ ካልቻልክ አንብብብ!!ማንበብ የተሻለ ሰው ያድርጋል።


ጆ ይ ን በ ማ ለ ት ተ ጠ ቃ ሚ ይ ሁኑ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1