💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15.1K subscribers
4.47K photos
2.08K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
ሚስት አለው!
~
→ በህይወት ጉዞ ላይ ልብ ያላሰበውን እንግዳ ያስተናግዳል፤ አንዳንዴም ባልተገባ ስፍራና ባልተፈቀደ ጊዜ ያርፋል። ልክ ለምለም መስክ መስሎት በጨው መሬት ላይ እንደበቀለ ዘር፣ ፍቅርሽ ወይም ፍቅርህ በሌላ ሰው የትዳር ክልል ውስጥ ሲገኝ፣ የነፍስ ጥማት ሳይሆን የህሊና እሳት ይሆናል። አንዳንዴ የራሱን ህይወት እየመራ፣ በራሱ ቃል-ኪዳን ታስሮ ለሚኖር ሰው ልባችሁን ትሰጣላችሁ። ይህ ስሜት፣ እንደማይደርሱበት ኮከብ እያዩ ሌሊቱን በናፍቆት እንደሚያነጋ ተጓዥ፣ መንገዳችሁን አጨልሞ፣ እርምጃችሁን ያግተዋል። ወይ የራሳችሁን ጎጆ አልቀለሳችሁ፣ ወይ ከዚህ የሀሳብ እስር ቤት አልተፈታችሁ። ይህ ስቃይ፣ የብቸኝነት ጩኸት ብቻ ሳይሆን፣ ከባድ የኢማን ፈተና ነው።

• ይህ ስሜት ሲጀምር ንፁህ ሊመስል ይችላል፤ የአንድን ሰው መልካም ስብዕና፣ ፈገግታ፣ ወይም አቀራረብ መውደድ ተፈጥሯዊ ነው። ነገር ግን ይህ መውደድ ድንበሩን አልፎ ያ ሰው የሌላው እንደሆነ እየታወቀ ወደ ጥልቅ ፍቅር ሲቀየር፣ ጦርነቱ ይጀምራል። ይህ ጦርነት በልብህና በአዕምሮህ መካከል የሚደረግ ነው። አዕምሮህ «ይህ አይሆንም፣ ሀራም ነው፣ የሌላ ሰው ንብረት ነው» ሲል፣ ልብህ ደግሞ በስሜት ታውሮ «ግን እወደዋለሁ/እወዳታለሁ» ይላል።

በዚህ የውዥንብር ሰዓት ነው ሸይጣን እንደ ቀበሮ ሾልኮ የሚገባው። ስቃይህን እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ፣ የሀራምን መንገድ በውብ ቃላት ያስውብልሃል። እንዲህ ሲል ይሸነግልሃል፦

• «ምን ችግር አለው? ፍቅርኮ ከፈጣሪ ነው። ስሜትህን መግለፅ አለብህ።»
• «ትዳሩ ደስተኛ ላይሆን ይችላል። አንተ/አንቺ ነህ/ነሽ እውነተኛ ደስታው/ደስታዋ።»
• «በጓደኝነት ስም ቀርበህ/ሽ ቀስ በቀስ የራስህ/ሽን ማድረግ ትችላለህ/ትችያለሽ።»
• «አንድ ጊዜ ብታገኘው/ኚውና ብትነጋገር/ሪ ምንም አያመጣም።»

እነዚህ ሁሉ የሸይጣን ጣፋጭ መርዞች ናቸው። አንዴ ከተቀመሱ፣ ወደ ከፋ የልብ ስብራት፣ የቤተሰብ መፍረስና ከሁሉም በላይ ደግሞ ወደ አላህ ቁጣ የሚወስዱ አደገኛ መንገዶች ናቸው።

የአላህ ቃል የሆነው ቁርአን፣ ለዚህ ችግራችን ፍቱን መድኃኒት የሆነ ታሪክን ይተርክልናል። የነብዩላህ ዩሱፍ እና የዙለይኻ ታሪክ። ዙለይኻ ባለትዳር ሆና ሳለ፣ በቤቷ በሚሰራው በዩሱፍ ፍቅር ከቁጥጥሯ ውጭ እስክትሆን ድረስ ተይዛ ነበር። ፍቅሯ አይኗን አሳውሮ፣ ሀፍረቷን ገፎ፣ የተከለከለውን ነገር ለመፈፀም እስከመዘጋጀት አድርሷታል። ክፍሏን ዘጋግታ "ና" ባለችው ጊዜ፣ የነብዩላህ ዩሱፍ ምላሽ ለሁላችንም እስከ እለተ-ቂያማ ድረስ የሚደወል የኢማን ደወል ነው፦ (በአላህ እጠበቃለሁ!) ነበር ያሉት።

እርሱ የመረጠው ጊዜያዊ ደስታን ሳይሆን፣ የጌታውን ውዴታ ነበር። የዙለይኻን ውበትና ግፊት ከመከተል ይልቅ፣ የአላህን ፍራቻ አስበለጠ። በዚህም ምክንያት ለዓመታት በእስር ቤት መከራን ተቀበለ። ነገር ግን ለአላህ ብሎ በመታገሱ፣ አላህ ከእስር አውጥቶ የግብፅ ገዥ አደረገው፤ ክብርንና ጥበብን ሰጠው። ይህ የሚያሳየን ታላቅ እውነት አለ፦ "ለአላህ ብለህ አንድን ነገር የተውክ እንደሆነ፣ አላህ ከዚያ የተሻለውን ይተካልሃል።" የሚለው የውዱ የነብያችን ሐድስ።

ይህንን የልብ ምርኮኝነት አሸንፎ ወደ ነፃነት ለመውጣት፣ ልክ እንደ ነብዩሏህ ዩሱፍ በአላህ መታገዝ ያስፈልጋል።  ከዚህ አይነት መጥፎ ስሜት ከምንወጣባቸው ነገሮች መካከል፦

① ዱዓ፦ ልቦች በአላህ እጅ ናቸው፤ እርሱ እንደፈለገ ይገለባብጣቸዋል። በእኩለ ሌሊት ተነስተሽ፣ በሱጁድ ላይ ወድቀሽ «ያ ሙቀሊበል ቁሉብ፣ ሰቢት ቀልቢ ዐላ ዲኒክ» (አንተ የልቦች ገላባጭ ሆይ! ልቤን በዲንህ ላይ አፅናልኝ) በማለት ዱዓ አድርጊ።
«ጌታዬ ሆይ! ይህንን ከልቤ አውጣልኝ፤ በምትኩም አንተን የምወድበትንና አንተን ለሚወድ ሰው የሚኖረኝን ሀላል ፍቅር ለግሰኝ» ብለሽ አልቅሺ።

② ሁሉንም የግንኙነት በሮች ዝጊ፦
ቁስል እንዲድን ከተፈለገ መንካትን ማቆም ግድ ነው። የዚያን ሰው ፎቶ ማየት፣ በማህበራዊ ሚዲያ መከታተል፣ ዜናውን መስማት፣ አልፎም ሊገኝበት በሚችልበት ቦታ መገኘት፣ እሳቱን እንደማራገብ ነው። ስልኩን ማጥፋት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ ማገድን ጨምሮ ሁሉንም የግንኙነት መስመሮች ሙሉ በሙሉ መቁረጥ የመጀመሪያውና ዋነኛው የመድኃኒቱ አካል ነው።

③ ለአላህ ብለሽ ተይው!፦ ይህንን ስሜት የምትተይው "ስለማይረባ" ወይም "ስለማያምር" ሳይሆን፣ ለአላህ ብለሽ መሆን አለበት። ይህ ውሳኔ በራሱ ዒባዳ ነው። ወሏሂ!ይህንን ውሳኔ ስታደርጊ፣ አላህ በልብሽ ውስጥ ልዩ የሆነ የኢማን ጥፍጥናን፣ እርካታንና መረጋጋትን (ሰኪናን) ይሰጥሃሻል ። የሀራምን ደስታ ለአላህ ብሎ የተወ፣ አላህ የሀላልን ጣፋጭነት ያቀምሰዋል።

④ ልብህን በበጎ ነገር ሙላው!፦ ልብ እንደ ባዶ እቃ ነው። በበጎ ነገር ካልተሞላ፣ በክፉ ነገር መሞላቱ አይቀርም። ጊዜህን ዒባዳ ላይ አውለው። ሰላትን በወቅቱና በኹሹዕ  ስገድ። ቁርአንን በተደቡር አንብብ። ዚክር አብዛ። የነብያቶችን ታሪክ አጥና። ልብህ በአላህ ፍቅር ሲሞላ፣ የሌላ ፍቅር ቦታ ያጣል።

⑤ የራስህን ህይወት ጀምር!፦ አላህ ትዳርን ትልቅ ተቋም ያደረገው እርጋታን፣ ፍቅርንና ምህረትን እንድናገኝበት ነው።አይንህን ወደ ሀላሉ በማዞር፣ ለአንተ ወደ ተፈቀደው የሕይወት አጋርህ ዞር በል። ይህንን የሀሳብ እስረኛነት ሰብረህ ስትወጣ አላህ ላንተ ያዘጋጀው የተሻለና የተባረከ የህይወት አጋር እንዳለ እመን።

በመጨረሻም ወዳጆቼ! ይህ ስሜት ሊያጠፋችሁ ሳይሆን፣ ሊያንፃችሁና ወደ ጌታችሁ ሊያቀርባችሁ የመጣ ፈተና መሆኑን ተረዱ።ማዕበሉ አልፎ የኢማናችሁ ፅናት ሲፈተን፣ ይበልጥ ጠንካሮችና ወደ አላህ የቀረባችሁ ሆናችሁ ትወጣላችሁ። የተሰበረ ልባችሁን ይዛችሁ ወደ እርሱ ተመለሱ፤ ጌታችሁ ከምንም በላይ ለተሰበሩ ልቦች ቅርብ ነውና።
📝𝐀𝐛𝐮 𝐒𝐮𝐟𝐲𝐚𝐧
|•|t.me/AbuSufiyan_Albenan
~ ንቀት ከበዛበት ወዳጅነት
ክብር ያለዉ «ብቸኚነት» ይሻላል።


=
∙ አንዳንድ ጊዜ ....

መጨረሻ ነዉ  ብለን እናስባለን  ነገር ግን በድንገት «አላህ ሁሉንም ነገር»ያስተካክላል።

=
t.me/https_Asselefya1
እያስተዋላቹህ!!


ልታገባው ነበር ነገር ግን "ከታማኝ ምንጭ" ባገኘችው መረጃ ሰውዬው በገንዘቡም በጤናውም ሆነ በፀባዩ ለትዳር አይሆንም ። ከዚያም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሰውየው ማግባቱን ሰማች ።

ማግባቱ አይገርምም ነገሩ ግን ወዲህ ነው ። ሰውየው ያገባው "ታማኝ ምንጯን" ነው
 የሶብር አይነቶች
Ibnu Munewor
የሶብር አይነቶች!

- የአላህን ትእዛዝ በመፈፀም ላይ መታገስ
- የአላህ ክልከላዎች በመራቅ ላይ መታገስ
-አሳማሚ በሆኑ የአላህ ዉሳኔዎች ላይ መታገስ

╭┈──── ••⇣⇣
╰┈➢ t.me/https_Asselefya1
የነገረኛ ሰው ጥፋት
ኢብኑ ሙነወር
በትዳርም ሆነ በጓደኝነት መካከል እየገባችሁ የምታራርቁ ምቀኛ፣ሸረኛ፣ተንኮለኛ ሰወች ተገሰፁበት ከክፉ ስራችሁ ተቆጠቡ ምንም አታተርፉበትም።

t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi
❝አንበሳ እና ነብሩ❞
🎙በኑረዲን አል-ዓረብ
👉ለሸይኽ አወል እና ለዑስታዝ ኸድር ከሚሴ ሀፊዞሁሙሏህ

«አንበሳ እና ነብሩ»
----------------------
ፈጥነው እንደ ሌሎች ክፉ አይናገሩም ፡
የኔን ብቻ የሚል ሙሪድ አያፈሩም፡
ዕውቀት ፍለጋ እንጅ ከቶ ፊትና አይመሩም፡
በማንም ላይ ቢሆን በደልን አይሰሩም፡
የፊትና አራጋቢ ውርጋጥ አይቀጥሩም፡

እኔን ተከተሉኝ ብለው አይደነፉም፡
ከዕውቀት ገበታ ጧትም ማታ አይጠፉም፡
መጓዝ የፈለገን አያወላከፉም፡
እኔን ምሰል ብለው ማንንም አይለክፉም፡

የሰለፍያ ልጅ ውድ የተውሒድ ፈርጦች
የወሎ ላይ ተክል የከሚሴ ምርጦች፡
ፈጥኖ የገባቸው የሰውነት ክብሩ፡
ጀግኖቻችን ናቸው አንበሳና ነብሩ፡

...በኑረዲን አል-ዓረብ

t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi
"ወንድሜ"

«ላታገባት ባዶ ተስፋ አትስጣት
«ላታገባት አለሁሽ አትበላት
«ላታገባት አትዋሻት
«ላታገባት እንደ ምርጫ አትጠቀማት

እህት አለህ አይደል በእህትህ ላይ እንደርስ የማትፈልገውን አንተ በሰው እህት ላይ አታድርስ።

«ላታገባት አትዋሻት  የቃላት ድርደራ በመሀላ ብዛት አታሳምናት አላህን ፍራ ውሸት አኗኗርን ቀርቶ አሟሟትን ያበላሻል እባክህ ወንድሜ በሴት ልጅ እድሜ አትጫዎት ነገ ሴት ልጅ ትወልዳለህ በቃ እውነቱን ንገራት አማራጭ አታድርጋት እባክህ አላህን አፍራ !! ነገ አላህ ፊት እራቁት መቅረብ አለና አስተውል በቃ አትዋሽ !

منقول
=
t.me/https_Asselefya1
«በትግስት___ጠብቃት!

የ
ህልም ንግስትህን እንዲህ ስትናፍቃት
የተፃፈዉ ደርሶ እስከ ምታገኛት

አደብ በልና በሰብር ጠብቃት
ዉስጥህን አዘጋጅ ዉድዬ እስክትመጣ
መሸከም እንድትችል የትዳርን ጣጣ

እስከዛዉ ግን ታገስ
የትም አትልከስከስ

የሰዉ ልብ አታውልቅ
አላማህን እወቅ

የዲን እህትህን ጊዜም አትሻማ
ላትሆንህ ላትሆናት መንፈሷን አታድማ

ያችንም ያችንም ላይሆን ቃል አትግባ !
ላንተም ደግ አይደለም የእህቶችህ እንባ!

ሰላምክን ታጣለህ ትዳር ስትገነባ!
የተለያየ ሴት ፀባይ መልክ ማየቱ

ቤትህን ይንደዋል ከነ መሰረቱ
ስለዚህ ወንድሜ የሰዉ ጊዜ አትግደል!
የተበዳይ ዱዐ እንዳይሰድህ ገደል!

አላህ ያለው ደርሶ እስከ ምታገኛት!
ኢማንህን ሰንቀህ በትግስት ጠብቃት!
አላህ ያለው ደርሰ እስከ ምታገኛት!


منقول
╭┈──── ••⇣⇣
╰┈➢
t.me/https_Asselefya1
አሁን ያለበት ገፀታ ሀገራችን ማለቴ ታች አንባ ☘

=
√ መጠለል እየቻሉ ግን ከናንተ ጋር ዝናብ ላይ የቆዩትን «ሰዎች» ምረጡ።

=
t.me/https_Asselefya1
النِّساءُ السَّلَفِيَّات أَغلَى مِنَ الذَّهَبِ الأَحمَر
Voice message
ወንዶቻችንን አታበላሹ ሰርተዉ እንዳይበሉ ወንድነት አታሳንሷቸዉ እረፉ በቃ! ጎበዝ ከሆንሽ ለቤትሽ ደጉሚ ግን ሙሉ አንች የሱ ቦታ አትያዥ አሃ¡¿ ለሁሉም ቦታ አለዉ ቦታሺ ላይ ተቀመጭ!