💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
ተቀርተው ያለቁ ደርሶች
ዒልም ፈላጊ.apk
ዒልም ፈላጊ - የሞባይል መተግበሪያ

መተግበሪያው ከያዛቸው በጥቂቱ፦

- ከ40 በላይ የሱና ኡስታዞችን ደርሶች፣
- የዐቂዳ፣ የተውሒድ፣ የመንሀጅ ኪታቦችን፣
- እያንዳንዱ የድምፅ ቅጂ ከሶፍት ኮፒ ጋር

- የቀን እና የማታ ገፅታ ያካተተ፣
- የፅሁፍ መጠን መጨመርና መቀነስ፣
- የጀማሪ ኪታቦችን ለብቻ የሚያሳይ፣

- የደርስ ሰአት እና ቀን አስታዋሽ ያለው፣
- ደርሱን ብናቋርጠው ሌላ ጊዜ ካቆመበት የሚጀምር፣
- አድስ ደርስ ሲጫን መልእክት የሚቀበል ነው።

መተግበሪያውን በሚከተለው ሊንክ ያውርዱ
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.aj.islamic_online_learning
العلم النافع علامة على سعادة العبد

=
قصائد سلفية... 📚
<unknown>
•• قصيدة في نواقض الاسلام...
نظمـ : الشيخ العصيمي حفظه اللّٰه

=
t.me/https_Asselefya1
•• قال محمد بن كعب القرظي :

"من حفظ القـرآن = مُتِـعَ بعقله
وإن بلـغ من العمـر مائتي سنـة!

‏‌‏⤶ ‏البداية والنهاية (٢٧٠/٩)
🫧🫧
t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy
ምክር ስመክርሺ ሙሉ ሰው አድርገሺ አታስቢኝምክር መለገስ የውደታ እንጅ የመብለጥ ምልክት አይደለም ባይጠቅምሺም አይጎዳሺም!!ነይማ ተከተይኝ አንድ ነገር ልገርሺ እህትዬ...!አንች ከሀገርሺ የወጣሺው ደልቶሺ አይደለምአ⁉️
አወ እንደምትይ ተስፋ አደርጋለሁ!!


እራስሺን ቤተሰብሺን  ለመቀየር ነው  ሀገር አቆራርጠሺ ያ በሰማይ የምታይው አውሮፕላን ለዐይንሺ የራቀ በሰማይ ተጣሎ ሲሄድ ብርቅ የሆነብሺ እውስጡ ገብተሺ በጣም የምትወጅውን ያደግሺበትን ሀገርሺን እናት፣ አባት ፣እህት፣ ወንድሞችሺን  ለአንድ ቀን ከቤተሰብ ተለይተሺ ብታድሪ የምታለቅሺ የነበርሺው ሁሉን እርግፍግፍ አድርገሺ  ወደማታቂው ወደበረሀ ሀገር የመጣሺ  ሀሳብሺ እቅድሺ ምን ነበር⁉️ መልሱን ስለምታቂው ለአንችው ትቻለሁ!!

ኢጃዛ ሺርሺር እያልሺ ብርሺን ከምጨርሺ
ብርሺን ዝም ብለሺ ከምትበትኝ save አድርገሺ ሸቅለሺ አላማሺን እቅድሺን አሳኪበት‼️
ብርሺ ላይ በጣም ፎከስ አድርጊ አጥብቂ ግዜው ሀይለኛ እየሆነ ነው  አላህን የማይፈሩ የብር ፍቅር ያሰከራቸው ኑሮ ሲከብዳቸው ትኩረታቸው ሁሉ አረብ ሀገር ሴት ላይ ነው ስለዚህ በጣም ልነቂ ብልጥ ልትሆኝ ይገባል!!

ዝቅ ብለሺ አድበሺ ስሪ ወጣ ወጣ አታብዢ አላማሺ ይሳካ ዘንድአላማሺን የወጣሺለትን እቅድ ሳታሳኪ ሀገር እዳትገቢ  በዚህ ኑሮ ውድነት ሀገር ገብተሺ ያለሺን ጨርሰሺ ነው የምትመለሺ እድሜሺን እንደ ውሀ ቀዢ ስትመላለሺ እዳትጨርሺ‼️

ጓደኞችሺን እያቸው ትናት የሸኘሻቸው እየተመለሱ ነው ለምን ይመስልሻል!? ላችው ትቻለሁ!!ስለዚህ እህቴ አንደዬ ከሀገርሺ ወተሻል ሀገር ሂደሺ ለመመለስ ለመመለስ አትሂጅ እዚሁ ጠንክረሺ ስሪ እቅድሺን እስከምታሳኪ ወጥረሺ ስሪ!! ጨርሻለሁ።

ያኢላሂ እኔንም እህቶቸንም የወጣንለትን አላማ አሳካልን ወደ ሀገራችንም ከገባን በኋላ በሀገራችን ሪዝቃችንን ከፍተህ በድናችን በመንሀጃችን በኒቃባችን ፀንተን  እስከ ሞት ፍፃሜአችን እንድንኖር   ሶብሩን፣ ፅናቱን ፣ ብርታቱን ወፍቀን አሚን!!

=
https://t.me/+6MI0Mn_JmaY5MDNk
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🛑👉ሰዎችን መልካም ነገር አመላክት....

•• دُل النَاسَ علی الخَیّر !

الشيخ عَبْد السّلام الشُويِعر وَفقه الله
=
http://t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
☞የላኢላ ሀኢለሏህ መስፈርቶች....!

شُروطُ لا إلـٰه إلاّ اللّٰه!
=
http://t.me/https_Asselefya1
↱ከረመዷን በፊት ሽርክን ተጠንቀቅ↲
አቡ ረይስ ሙሐመድ ኢማም
ቆየት ካሉ የጁሙዐ ኹጥባ

↶⊱ احْذَرْ الشِّرْكَ قَبْلَ رَمَضَانَ

⊰ከረመዷን በፊት ሺርክን ተጠንቀቅ !!

🕌 ደሴ አል አዝሓር መስጂድ

[شعبان/٢٠ /١٤٤٢]

🎙በአቡ ረይስ ሙሐመድ ኢማም

=
t.me/abu_reyyis_arreyyis/9172
t.me/abu_reyyis_arreyyis/9172
የባሏ እጅ ከእጇ የእግር ጫማ ከጫማዉ አጋጥማ ትቀርፀና ከዛ የኔ ባል እንድህ ነዉ የኔ ባልዋ ልዬ የኔ ባልዋ....... እያለች ጥሩነቱ ሙሉ ሚድያ ትፀፍ ትፀፍና ከዛ አንዷ ሄዳ ስትነጥቃት ባሌ ተቀማሁ ዉሪሪ ብላ ሚድያ ለቅሶ ቤት ታስመስላለች እቱዬ አንቺዉ እኮ ነሺ ቀድመሺ ያስማማሸዉ እ! ታድያ ለቅሶ ምን በሉኝ ነዉ ደግ አደረገችሽ እሰይ ደግ ሆንሺ የምልሽ !!ማን አስማሚ አለሺ ቀድመሺ !?

=
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
⭞ዉርጃ እና ኒፋስ ∼∼∼∼∼∼∼ 【ክፍል ⓶⓵】     ⬌⬌⬌⬌⬌ ☞ተፈጥሯዊ በሆነ መልኩም ይሁን በሰው ሰራሽ ምክንያት አራት ወር የሞላውን (ነፍስ የተዘራበትን) ጽንስ ያስወረደች ሴት የሚፈሳት ደም የኒፋስ ደም ተደርጎ እንደሚወሰድ ሁሉም ዑለማኦች ተስማምተዋል፡፡ አራት ወር ባይሞላውም ያስወረደችው ጽንስ የሰው ቅርጽ (እጅ፣ እግር፣ጭንቅላት... } ☞ከተፈጠረለት በኋላ (81 ቀን) ያለፈው ከሆነም የኒፋስ…
የሀይድ እና የኒፍስ አስተጣጠብ
∽∼∽∼∽∼∽∼∽∼∽∼∽

🛑👉ክፍል  ⓶⓶«የመጨረሻ»
━━━━━━━━━━━

የመታጠብ ግዴታነት የሚጸናው በደም ፍሰትነው። ደም ያላጋጠማት ሴት እንዲትታጠብ አትገደድም። ትጥበቱ ተቀባይነት ይኖረው ዘንድ ደግሞ የደሙ ማቆም ቅድመ ሁኔታ ተደርጎ ይወሰዳል። ደሙ ሳይቆም የታጠበች ሴት አልነጻችም ማለት ነው። ከሀይድ ወይም ከኒፋስደም ለመጽዳት መታጠብ ራሱን የቻለ አምልኮትነው፡፡ስለሆነም ኒይያ ያስፈልገዋል፡፡ከሀይድ መንጻትን ሳታስብ ብትታጠብ ከሀይድ እንደጸዳች አይቆጠርላትም።

عن عمر رضي الله عنه  انه سمع رسو ل الله يقول " إنما الأعمال بالنيات وإنما لكل إمرء ما نوى " متفق عليه


ሀይድ ወይም ኒፋስ ላይያለች ሴት መላ አካሏን የመታጠብ ግዴታ አለባት፡፡ ምንም አይነት ዉጫዊ የሰውነት ክፍል አይታለፍም፡፡ አንድት ሴት ጁኑብን በምትታጠብበት ወቅት ጸጉሯን መፍታት አይጠበቅባትም፡፡ ለሀይድና ለኒፋስ ትጥበት ግን ጸጉሯን በመፍታት ማዳረስ ግድ ይላታል ይላሉ ጥቂት ምሁራኖች፡፡ በትክክለኛ ሃዲሶች ጸጉሯን በጣም አድርጋ እንድታሸውና ራሷንበሙሉ እንድታዳርስ ተነግሯል፡፡ በዚህ ላይ ተመስርተው አብዛኛዎቹ ምሁራኖች ጸጉርን መፍታት የሚወደድ ተግባር እንጂ ግዴታ እንዳልሆ ነያምናሉ የተሻለውም አቋምይህነው፡፡ ምክንያቱም የሀይድ እና የጁኑብ ትጥበት ሁለቱም በትጥበት ደረጃ የሚያለያያቸው ትልቅ ነጥብ የለም፡፡ በትጥበቱ ዙሪያ የተቀመጠው ወሳኝ ቁምነገር ራሷ (ጭንቅላቷ) ሙሉ በሙሉ በዉሀ እንድዳረስ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ለጥንቃቄ ሲባል ግን ጸጉሯንም ሁሉ ማዳረስ ተገቢ ነው፡


عن أسماء انها سألت النبي صلى الله عليه وسلم  عن غسل  المحيض  فقال...ثم تصب على رأسها  فتدلكه  دلكا شديدا  حتى  تبلغ شؤون رأسها ثم  تصب عليه الماء...رواه مسليم

عن عائشة  قالت : كنا نغتسل وعلينا الضماد ، ونحن مع رسو ل الله محلات  ومحرمات. رواه ابو داود


ሀይድን ወይም ኒፋስን ለማስወገድ በማሰብ መላ ሰውነቷን ራሷንም ጭምር በዉሃ ያዳረሰች ሴት ከሀይድ ወይም ከኒፋስ ነጽታለች። ይህ ግዴታ የሆነው አስተጣጠብ ነው።👉ሱንናዊአስተጣጠብ ግን መጀመሪያ ኢስቲንጃእ ታደርጋለች፡፡ ከዚያም በሳሙና ወይም በሌላ ነገር እጆቿንታጸዳለች፡፡ ከዚያም ሀይድን ለማስወገድ በመነየት ዉዱእ ታደርጋለች፡፡ እግሮቿን ከፈለገች መጨረሻ ላይ ከፈለገች ደግሞ ዉዱእ በምታደርግበት ጊዜ መታጠብ ትችላለች፡፡ ዉዱእ ስታደርግ ያጠበቻቸውን የሰውነት ክፍሎች ቀሪ አካሏን ስትታጠብ ዳግም መታጠብ አይጠበቅባትም፡፡

ከዚያምበጸጉሯ ላይ ሶስት ጊዜ ሶስት እፍኝ ዉሃን እያፈሰሰች በደንብ ታሸዋለች፡፡ ራሷ በደንብ ሲረጥብ ተጨማሪ ዉሃ በማፍሰስ መላ ራሷን ታዳርሳለች፡፡ መጀመሪያ ቀኝ የራስ ክፍሏን ቀጥላም ግራውን ክፍል በማስከተልም መሀል ክፍሉን መታጠቧም ሱንና ነው፡፡ ራሷን አዳርሳ ከታጠበች በኋላ ቀኝ የገላዋን ክፍል ትታጠባለች፡፡ ቀሪውን የግራ ጎኗን አስከትላ ከታጠበች በኋላ መጨረሻ ላይ ሚስክ የተደረገበት ጥጥ ወይም ሽቶ የተደረገበትን ፎጣ በመጠቀም ደም የሚያገኘውን አካሏን በማደራረቅ ታጠናቅቃለች፡፡ ሰውነቷን ከመታጠቧ በፊት ዉዱእ አደረገችም አላደረገችም ሀይድን ወይም ኒፋስን ለማስወገድ አስባ እስከታጠበች ድረስ ኋላ ላይ ዉዱእ ማድረግ አይጠበቅባትም፡፡ ትልቁን ሀደስ ለማስወገድየሚደረገው ኒይያ ትንሹን ሀደስምያካተተ ነው፡፡ ስለዚህ ዉዱእም እንዳደረገች ነው የሚቆጠረው ማለት ነው፡፡ ነብዩም ሰውነታቸውን ከታጠቡ በኋላ ዉዱእ ማድረጋቸውን የሚጠቁም አንድም መረጃ የለም። ይህም የማሊኪያዎች፣ የሻፍዒያዎችና የሀነፊያዎች ምርጫ ነው።

قال النبي  للرجل بعدما أعطاه  الماء ليغتسل به من الجنابة : خذ هذا فأفر غه  عليك، رواه البخاري

قال ابن عبدالبر: الله عزوجل إنما فرض على الجنب  الغسل دون الوضوء ..وهذا إجماع لا خلاف فيه بين العلماء"


የሀይድና ኒፋስ ትጥበት ግዴታነቱ ወዲያዉኑ ደሙ እንዳቆመ የሚጸና አይደለም፡፡ ሀይዷ ወይም ኒፋሷ ሙሉ በሙሉ ማቆሙን እንዳረጋገጠች ባስቸኳይ የምትፈጽመው ግዴታ የሆነ ተግባር ካለ ግን ቶሎ መታጠብ ግዴታ ይሆንባታል፡፡ ለምሳሌ ከሀይድ የነጻችው ጸሀይ ልትጠልቅ አካባቢ ከሆነ ዐስርን መስገዷግዴታ ስለሆነ ወዲያዉኑ መታጠብ ግዴታ ይሆንባታል፡፡ ነገር ግን ሀይዷ ያቆመው ዐስር እንደገባ ከሆነ ሰፊ ጊዜ ስላላት ዘግየት አድርጋ መታጠብ ትችላለች፡፡ ወዲያውኑ መታጠቡ የሚወደድ ተግባር መሆኑ ግን መዘንጋት የለበትም። የሀይድና የኒፋስ ደም ነጃሳ ነው፡፡

قال الله عزوجل  {"وَیَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلۡمَحِیضِۖ قُلۡ هُوَ أَذࣰى "  البقرة :٢٢٢}
ولقول النبي  لفاطمة  بنت أبي حبيش ...فاغسلي عنك الدم ...رواه البخاري
قال الشوكاني : واعلم ان دم الحيض نجس بإجماع المسلمين " نيل الأوطار : ١/٥٧



ስለሆነም ይህ ደም የነካውን ልብስ ማጠብ ግድ ይላል፡፡ ለማጠብም ሳሙናና መሰል ማጽጃዎችን መጠቀም ይበረታታል፡፡ ሳሙናና መሰል ማጽጃዎችን ለመጠቀም አቅም የሌላት ከሆነ በዉሃ ብቻ ማጠብ ይኖርበታል፡፡ በዉሃ ካጠበችው በኋላበልብሱ ላይ የደሙ ተጽእኖቢቀር በነጃሳነት አይወሰድም፡፡ የደሙ አሻራ አይጎዳም ተብሏል፡፡

قال النبي صلى الله عليه وسلم  لخولة بنت يسار: يكفيك  غسل الدم ولا يضرك  أثره،،  رواه أبو داود وصححه الألباني


ከሀይድም ይሁን ከኒፋስ ለመንጻት ዉሃ መጠቀም እስከተቻለ ድረስ ከዉሃ ዉጭ ያሉ መጸዳጃዎችን መጠቀም አይቻልም። ሀዲሱም ይሄንኑ ያስረዳል፡፡

قال النبي صلى الله  عليه وسلم  لخولة بنت يسار :يكفيك الماء ...رواه أحمد  وصححه أحمد شاكر


የሀይድ ደም ማቆሙን ካረጋገጠች በኋላ ሰውነቷን ለመታጠብ ዉሀያላገኘች ወይም ዉሃው ቢገኝም መጠቀም ያልቻለች ሴት ተየሙምታደርጋለች። ከዚያም የጸዳች ሴት የምታደርጋቸውን ማንኛውም ተግባራቶች መፈጸም ይኖርባታል፡፡

"فَلَمۡ تَجِدُوا۟ مَاۤءࣰ فَتَیَمَّمُوا۟ صَعِیدࣰا "  النساء ٤٣

«ተጠናቀቀ አላህ ባነበብነዉ ተጠቃሚዎች ያድርገን ....!! »

«ለአስተያየት እርምት በዚህ ያቀብሉኝ፦     @Ass_Selefyaa1bot 


──────⊹⊱✫⊰⊹──────
الحمدُ للهِ الَّذي بِنعمَتِه تَتمُّ الصَّالحاتُ .

አልሐምዱሊላህ!
በፀጋው መልካም ነገሮች ሁሉ ይሳካሉ፡፡


──────⊹⊱✫⊰⊹──────
http://t.me/https_Asselefya1
http://t.me/https_Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
⭞የሀይድ እና የኒፍስ አስተጣጠብ ∽∼∽∼∽∼∽∼∽∼∽∼∽ 🛑👉ክፍል  ⓶⓶«የመጨረሻ» ━━━━━━━━━━━ ☞የመታጠብ ግዴታነት የሚጸናው በደም ፍሰትነው። ደም ያላጋጠማት ሴት እንዲትታጠብ አትገደድም። ትጥበቱ ተቀባይነት ይኖረው ዘንድ ደግሞ የደሙ ማቆም ቅድመ ሁኔታ ተደርጎ ይወሰዳል። ደሙ ሳይቆም የታጠበች ሴት አልነጻችም ማለት ነው። ከሀይድ ወይም ከኒፋስደም ለመጽዳት መታጠብ ራሱን የቻለ አምልኮትነው፡፡ስለሆነም…
ይሄ የመጨረሻ ነዉ ተከታታይ ፁሁፋችን ማቆሚያ ነዉ። ከረመዷን በኋላ አላህ እድሜ ከሰጠን ሌሎች ተከታታይ ፁሁፍ እንቀጥላለን !

በእስተዛሬ ቆይታችን ብዙ ነገሮች በአላህ እገዛ አስተላልፈናል አላህ ይቀበለን!! ስለ ቻናላችን ዛሬ አስተያየት ሀሳባችሁ አቀብሉኝ እኔ ልቀበላችሁ በሉ ምክርም ሌላም ሀሳብ ካላችሁ ጣል ጣል አድርጉብኝ እጠብቃለሁ መስመር ላይ ነኝ👇👇👇👇

@Ass_Selefyaa1bot
@Ass_Selefyaa1bot

እህታችሁ B.A ነኝ ከባህር ማዶ

✍️