💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
ወንድ ልጂ ከምንም በላይ በችግሩ ግዜ ከጎኑ የምትቆም ሴት እጂጉን አብዝቶ ይወዳል!!

🎈
ኡኽታ እኔና አንቺስ በችግሩም በደስታውም ጊዜ አብረነው ነን

https://t.me/SileTidarEnmekaker
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
እህቴ ⓼ ➭➭➭➭ ⇘የጀነት ሰዎች ነፍሳቸዉ ከፍጥረቱ ዉዴታ ተሳንፋ ወደ ፍጥረቱ ፈጣሪ የተጠናከረች ናት። ጌታቸዉ ከንብረታቸዉ፣ ከቤተሰባቸዉ፣ ከነፍሳቸዉ በላይ እነሱ ዘንድ ተወዳጅ ነዉ። ⇘ምናልባትም በሌሊት ተነስተዉ ለሱ አንሾካሽከዋል፣ ቀንም በሱ ፍራቻ አንብተዋል፣ ዐይናቸዉ እሱ ማየትን ናፍቀዋል፣ ልባቸዉ በሱ ዉዴታ ረፍት አግኝተዋል። ⇘በዱንያ ላይ ልባቸዉ እሱን ማየትን ናፈቀችና አላህም በዚያኛዉ…
እህቴ
➭➭➭➭

ዛሬ የእዝነትና የፍቅር የአታክልት ስፍራ በሆነዉ (በአቡ ደህዳህ) የአታክልት ስፍራ ዉስጥ ቆይታ እናረጋለን። ያቺ የአታክልት ስፍራ ልብን በሀሴት ምትሞላ፣ ደስታ የምትሰጥ፣ ሰላማዊ አየር ያላት ዉብ የአታክልት ስፍራ ናት። ያየዉን ሰዉ ድንገት ሳያስተዉል ‛ሱብሀነላህ!’ እንዲል ታስገድዳለች። የመዲና ሰዎች አዉርተዉላት የማያበቁ እጅግ ዉብና ምርጥ የአታክልት ስፍራ ነበር።

ከዕለታት በአንዱ ቀን የምድር ሰዎችን እንዳስገረመዉ ሁሉ የሰማይ መልዕክተኞችን አጀብ ማሰኘት የሚችል የሚገርም ክስተት ተከሰተ። ንፁህ ዐይኖችን በእንባ ያጠበ፣ እዚያ የነበሩትን ብቻ ሳይሆን ታሪካቸዉን የሰማዉን ሰዉ በእንባ ያራጨ ገራሚ ክስተት ተከሰተ።

ክስትቱ ወዲህ ነዉ.. አንድ ቀን (አቡ ደህዳህ) በነቢያችን አጠገብ ሲያልፍ የአንድን ታዳጊ ልጅ ለቅሶ ይሰማል። ልጁ የቲም መሆኑን ሲያዉቅ አዘነለትና ቆሞ የልጁን ጉዳይ መስማት ፈለገ። ልጁም ሀዘን በጎዳዉ አንደበት እንባዉ እየቀደመዉ ረሱሉን እንዲህ አላቸዉ..

«አንቱ የአላህ መልዕክተኛ! በአታክልት ስፍራዬ ዙሪያ ግንብ እየሰራሁ እያለ (ግንዱ) የጎረቤቴን አንዲት የተምር ዛፍን ቆረጠበት። እንዲተዉልኝ ወይም እንዲሸጥልኝ ጠየኩት። እሱ ግን እምቢ አለ።»

ረሱሉም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሰሀቦችን ያን ጎረቤቱን እንዲጠሩት አዘዙትና መጣ። ረሱሉም ልጁ የቲም ስለሆነ እንዲሰጠዉ ሌላዉ ቢቀር እንዲሸጥለት ጠየቁት። እሱ ግን እንደማያረገዉ ተናገረ።

ረሱሉም በጣም የሚገርምን ንግድ አመላከቱት.. «ሽጥለት! ለአንተ ደግሞ በምትኩ መቶ የተምር ግንዶች ጀነት ዉስጥ አሉልህ!» አሉት። (ዐዉ ከማ ቃለ)

ሁሉም ሰሀባ በድንጋጤ ክዉ አሉይሄን የመሰለ ግብይት ወደ ቀረበለት ሰዉ ጆሮዎች ዞሩ። እንደሚቀበል ማንም ሸክ አልነበረዉም

እሱ ግን እምቢ አለ።የቲሙም ልጅ እንባ በእንባ ሆነ። የሰሀቦች ዐይንም ወደ ሰዉዬዉ በግርምት ማየት ጀመሩ። እሱ ግን ምንም አቋሙን አልቀየረም ነበር።

ይሄኔ ነዉ (የአቡ ደህዳህ) ታሪክ ሚጀምረዉ። አቡ ደህዳህ ይሄንን ምልልስ ከሰማ ብኃላ ነፍሱ ወደ ጀነት ናፈቀች። ረሱልንም እንዲህ ሲል ጠየቀ..

«አንቱ የአላህ መልዕክተኛ! የአታክልት ስፍራዬ ሽጬ ለልጁ የተምር ግንዱን ባስመልስለት በጀነት ዉስጥ የተምር ዛፍ አገኛለሁ?»

ረሱሉም ደስታ ፊታቸዉን አፈካዉ። «አዎ!» አሉት። አቡ ደህዳህም ወደ ሰዉዬዉ ዞረና «የአታክልት ስፍራዬን ታዉቀዋለህ?!» አለዉ። ሰዉዬዉም «አዎ!» አለ።

አቡ ደህዳህም «የተምር ግንድህን በአታክልት ስፍራዬ ሽጥልኝ!» አለዉ። ተስማማ ንግዱ ተፈፀመ። (ሱብሀነላህ!)

የልቡ ምት የእግሩን ፍጥነቶች እየቀደመ ወደ አታክልት ስፍራዉ ሮጠ። የመዲና ቤቶች በመላለሱት በተቆራረጠ ድምፅ..
«ኡመ ደህዳህ!..
» ብሎ ሚስቱን ተጣራ።

«ከአታክልት ስፍራዉ ዉጪ! እሱ ለአላህ!» አላት። የደህዳህ እናትም ወዲያዉ ከግዛቷ ተነሳች። እጆቿን ከፍራፍሬዎቹ ላይ አነሳች። በልጆቿ እጅ ላይ የቀሩትን ፍራፍሬ ሳይቀር ቀማቻቸዉና አማና ነዉና አስቀመጠችዉ። የባሏን ትዕዛዝ ከመፈፀሟ በፊት የአላህን ትዕዛዝ «ለበይክ!» አለች። ምንም ሳትጠይቅ፣ ምንም ሳታጣራ በንፁህ ልብ ዉሳኔዉን ተቀበለች። አንድ ነገር ብቻ ነዉ ምታቀዉ። «ለአላህ!» መሆኑን።

ከዚያም ወደ ባሏ ዞረችና.. «ትርፋማ ንግድ ነዉ አቡ ደህዳህ! ትርፋማ ንግድ ነዉ።» አለች።

እቺ እህትሽም የጀነትን ፀጋ በማሠብ ከዱንያዊዉ የአታክልት ስፍራ ወጣች።

ምን አይነት ሚገራርሙ ባልና ሚስት ናቸዉ?!

ልቧ በአታክልት ስፍራዉ ላይ የተንጠለጠለ ቢሆንም ያለ አንዳች ኪላፍና ሙሉ በሆነ ዉዴታ የባሏን ትዕዛዝ አከበረች። ወደደች።

ዛሬ እኔ ምንም አላወራም። ታሪኩ ብቻዉን ለሚገሰፁት በቂ ትምህርት ነዉ።

እህቴ! የፈለገዉን ያህል ፈታኝ ቢሆንም ከዱንያ የአታክልት ስፍራሽ ዉጪና ለአላህ መንገድ ደስ ከሚልሽ ነገር ላይ ለግሺ! ከንብረትሽ፣ ከወቅትሽ፣ ከእድሜሽ ለዚህ ዲን መፅዉቺ!! የአላህን ዉዴታና የጀነቱን የአታክልት ስፍራ በማሰብ በደስታ ካለሽ ላይ ስጪ!!

ጆይን ይበሉ ⇣⇣⇘⇣⇣
http://t.me/https_Asselefya1
በነገራችን ላይ፡የሀገሩን ሴቶች ትቶ የባህር ማዶ ሴቶችን ለትዳር የፈለገ ሁሉ ገንዘብ ከጃይ አይደልም።የአካባቢውን ሴቶች አልፎ ከሌላ ሀገር ያገባም የሰፈሩን ሴቶች የጠላ አይደልም።ይልቅስ፡ኑሮ ፈላጊ ነውና አንድም በአስተሳሰቧ በሰል ያለች ሁለትም በቂሙያ ያላትን የቤት አያያዝ ልምድ ያላትን የፈለገ ነው።እስኪ ስለ እውነት ስትሉ እራሳችሁን ፈትሹ…አንዳንድ እህቶች እኮ ስለ ትዳር ስሙን እንጂ ብዙ አትረዱትም በጥሩ እናት እንክብካቤ ውስጥ ሰለሆነ ያላችሁት ደህና ሽሮ እንኳን አብስሎ ለመስጠት ገና ናችሁ።እህል አበጃጅቶ ወፍጮ ቤት ለመውሰድ እንኳን የሚቀራችሁ እኮ ናችሁ።እስኪ በማን ሀገር ነው "ጤፍ በውሃ የሚታጠበው"?! አንዳንዶቻችሁ የምትሆኑት እኮ ለሽርሽር ብቻ ነው።አንዳንዶች ደግሞ ቡፌና ቁም ሳጥን ያለበት ቤት በሄዳችሁ ቁጥር ማታ እቤት ስትመለሱ ለኔም ካልተሰራ ብላችሁ ቡፌ የምታክሉ ናችሁ እኮ? ታዳ ይሄ ሰው እንኳን ከባህር ማዶ የትስ ቢሄድ ያንሰዋል እንዴ? የምሬን እኮ ነው ላጤ በሆነበት ሂዎቱ፡ሽሮውንም አብስሎ፡ወፍጮ ቤትም ሂዶ አስፈጭቶ የጠነከረም እየጋገረ በልቷል ታዳ ደግሞ ካገባ ቡሃላ እንኳን አይቀርለትም እንዴ? ቢተጋገዙ ምን ችግር አለው እንዳትሉኝ እኔ ይሄን አልነቀፍኩም።

ማንቂያ፦ይሄን ስል ሁላችሁንም እህቶች እንዳልሆነ ካልተረዳችሁኝ እውነትም በመጥፎ ትጠረጥሩኛላችሁ ማለት ነው።የማወራው ያለውን እውነታ ነው።የአንዳችንም ሙገሳ አልፈልግም የሌሎችንም ወቀሳ አልፈራም።

~
አቡ ዑበይዳ ፦ t.me/AbuOubeida
~በነገራችን ላይ…ብዙ ጊዜ በርካታ ሰዎች ታዋቂ ሰው የትዳር አጋራቸው እንዲሆን ይፈልጋሉ። ግለሰቡ/ቧ ታዋቂ ከሆነ «የእገሌ ባል፣ የእገሌ ሚስት» መባል ይሻሉ። እውነታው ግን አላህ ካዘነላቸው ውጭ ታዋቂ ሰዎችን ማግባት ፈተናው ከተራው ሰው የበረታ ነው። በሆነ ባልሆነው በቅናት መቃጠሉ እንዳለ ሆኖ፤ በርካታ ታዋቂ ሰዎች የተቃራኒ ጾታ ጫና ይበዛባቸዋል።

~እንኳን የሚያናግራቸው አግኝተው እነርሱም ታዋቂነታቸውን በመጠቀም ማጥመቅ የፈለጉትን አካል በሐራም ጭምር ለማጥመቅ ሲሞክሩ ይስተዋላል።በአጭሩ ብዙዎቹ ለትክክለኛ ትዳር አይሆኑም። ስማቸው ነው እንጂ ውስጣቸው ሲፈተሽ ብዙ ጉዳጉድ አለው። ለአንቺ የሚጠቅምሽ ደግሞ የስማቸው መታወቅ ሳይሆን ቤት ውስጥ ትክክለኛ የትዳር አጋር ሆነው መገኘታቸው ነው።

~ምናልባት በመልካም ነገር ታዋቂም ሆኖ በተጨባጭ የትዳር ህይዎት ላይም መልካም ሰው ከሆነ ይሄ ማሻ አላህ ነው። ለእንዲህ አይነቱ ቢጓጉም አይቆጭም። ያስመሰግናል እንጂ አያሳፍርም።ከዚያ ውጭ ግን ውጭ ላይ የሚወራን ዝናና ቁሳዊ ሃብት መሠረት በማድረግ ብቻ የትዳር አጋር ለማድረግ መቋመጥ፤ ኋላ ያልታሰበ መዘዝ አምጥቶ ትልቅ ዋጋ ያስከፍላል። ከጊዚያዊ ሞቅታና ጨቅላ እሳቤ ወጥቶ፤ የነገንም ራቅ አድርጎ ማሰብን ይጠይቃል። ታዋቂነቱን ሳይሆን ትክክለኛ ስብዕናውን ተመልክተን ብንመርጥ የተሻለ ነው። የታወቀ ዝነኛ ሁሉ ጥሩ አይደለም። ያልታወቀ ሚስኪን ሁሉ መጥፎ አይደለም። ቁም ነገሩ አላህ ዘንድ መታወቅ እንጂ ሰዎች ዘንድ መታወቅ ላይ አይደለምና!

አላህ ሁላችንንም አስተካክሎ ለሚወደው ተግባርና ንግግር ይወፍቀን።
=
t.me/AbuSufiyan_Albenan
እነዚያ የቻነልህን ሊንክ ነቅለው እያነሱ የራሳቸውን የሚተክሉት ሰዎች፡የፖሰትከው ፖስት እንዳስተማራቸውና ሌሎችንም እንደሚያስተምር አምነዋል።ነገር ግን የነርሱን ሊንክ በመትከል ኬላ ላይ ቆመው ወደራሳቸው ጉምሩክ ነው ማስገባት የፈለጉት።ክፉ ልማድ ቢሆንም እነርሱን ካስደሰታቸው ግደለም ይሁን ፍላጎታችን ትምህርቱ እንዲደርስ ነው ደርሷል።
~
አቡ ዑበይዳ ፦ t.me/AbuOubeida
አንዳዴ....

ነገሮች ከአቅማችን በላይ ሲሆኑ
ምንም ማድረግ ሳንችል ስንቀር ዝም እንላለን!

እስኪ አንተ ታወለቃለህ ጀሊሉ.......!

=
አቂደቱል ዋሲጢያህ ኪታብ በአማረኛ
ግቡ አንብቡ ሸርሁ የሸይኽ ፈዉዛን ኪታብ በአረበኛ ብቀሩት የበለጠ ሸጋ ነዉ አረበኛ ለከበደዉ በአማረኛ ማንበብ➴➴
t.me/Binit_Seid_Usman_Al_kelaliya/761
t.me/Binit_Seid_Usman_Al_kelaliya/761
Forwarded from Sadat_Business
ሙሀመድ ባቲ የአይሱዙ እና የFSR መኪና መለዋወጫ እቃ አቅራቢ:
ለነጋዴዎች ለግል,ተጠቃሚዎች ባሉበት ቦታ እልካለው የሞተር የቦዲ የሰርቪስ እቃዎች በኦርጅናል በሎካል አቀርባለው ታማኝነት የዲናችን መሰረት ነው


አድራሻ አዲስ አበባ አብነት ዋሄነት ህንፃ ግራውንድ ላይ


ስልክ:0912201407/0920881222
ሴት ልጅ ገንዘብ ትወዳለች አሉ ለመሆኑ እዚች ምድር ላይ ገንዘብ የሚጠላ አለዴ እ!?

~
የአላህ ሚዛን ከፍጥረታት የተለየች ናትና ዋጋህን አላህ ዘንድ እንጂ የሰው ልጅ ዘንድ አትፈልግ።

~
t.me/https_Asselefya1
~አንድ ሰው አፍቅራችሁ፤ አብሮ ለመኖር ተመኝታችሁ ከሆነ… አገኘው አጣው ይሆን ብላችሁ  ብዙ አታስቡ፤ አትብሰልሰሉ። አላህ ያለው ይሆናል፣ እሱ ያላለው አይሆንም። «ቀደር»አንድም ይሰበስባችኋል ወይ ይበትናችኋል።

ቀደር ማለት 6ኛው የኢማን ማዕዘን ነው። በጎ ይሁን መጥፎ ስለኛ ነገር የተፃፈው ሁሉ ጥንት ከመፈጠራችን በፊት ነው። እኛም እየኖርን ያለነው ከዚህ ቀደም የተፃፈልንን ነው። አላህ ያልፃፈልንን ብንስገበገብ ጎትተን አናመጣውም። እሱ የፃፈልንን ገፍተን አንመልሰውም።

ሁሉም ነገር ከልኩ ላያልፍ የምን መባከን የምን ብዙ መጨነቅ!
=
t.me/AbuSufiyan_Albenan