💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.49K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
🌸ውድ የሆነች ምክር🌸

💎እናታችን አዒሻ ረዲየ አላሁ ዓንሀ እንዲት ትላለች፦

➻እናንተ ምዕመናን እንስቶች ሆይ ከእናንተ እንዳችሁ የሆነን ኃጢያት የሰራ እንደሆን አደራ ያንን ለሰው አይነገር፡ነገር ግን አላህን ምህረት ይጠይቅ ወደሱም ንስሓ በማድረግ ይመለስ።

📚مكارم الأخلاق للخرائطي ص (503)

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
▸◉የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ◉◂

➩◉ከትንሳኤ ➷መቃረብ ምልክቶች ➷መካከል‼️

➩◉የእውቀት መነሳት ➷የአላዋቂነት መብዛት ➷የዝሙት መብዛት ➷የአስካሪ መጠጦች መብዛት ➷ለአንድ ወንድ ሀምሳ ሴት ➷እስክትደርስ ድረስ የሴቶች ➷ቁጥር መብዛት ነው‼️

#ምንጭ 《صحيح البخاري》
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
✅♻️ ትክክለኛነቱ እርግጠኛ ያልሆንበት ነገር ከመፃፍና ሰዎችም የፃፋት ሳናረጋግጥ ዝም ብሎ ከማሰራጨት ልንቆጠብ ይገባል።

🔵‏قال الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله:

〰〰〰〰〰〰➰➰➰➰➰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰

«واليوم الواحدُ منَّا يكتب سطرًا وهو في بيته ربَّما قرأَه الملايين، فإن لم يكن متيقِّنًا أنَّه خيرٌ فلا يُدخل نفسه في هذا الباب، فلربَّما جاء يوم القيامة وهو يجرُْ سيئات كثيرة بسبب هذا السطر»

♻️ሸህ ሱለይማን አሩሀይሊይ (አላህ ይጠብቀውና) እንዲህ ይላል

🔺 ዛሬ ከኛ መካከል አንዳችን እቤቱ ሆኖ አንድ መስመር ፅሁፍ ይፅፋል። ይህንን ፅሁፍ ሚሊዮኖች ነው ሚያነቡት። በትክክለኛነቱ (በመልካምነቱ) እርግጠኛ ካልሆንን እንዲህ አይነት ነገር ውስጥ ልንገባ አይገባም። ምክንያቱም ይህ ሰው በዚህ ፅሁፍ የተሳሳቱና ወንጀል ውስጥ የወደቁ ሰዎችን ወንጀል ይዞ የውመልቂያማ ይመጣልና።

[ شرح رسالة ابن القيِّم (ص٧) ]

👉 መፃፍ ስለቻልን ብቻ አንፃፍ
👉 ምንፅፈው ነገር ቀድመን ከቁርአን ከሀዲስ መልእክት ጋር ያለ መጋጨቱን እናረጋግጥ
👉 ምንፅፈው ነገር ለሰዎች እውቀት የሚያሲዝ ነገር ይሁን
👉 ያልተረጋገጡ ቂሳዎች፣ ቁም ነገር የሌላቸው ፅሁፎች፣ ቀልድና ዛዛታዎች በመፃፍ የኛንም የሰዎችንም ጊዜ ልንገድል አይገባም
👉 አንዳንዶቻችንማ የሆነ ግሩፕ ላይ ስላገኘነው ብቻ ሳናነበው ምን እንደሆነ ነገሩ ሳናይ እናስተላልፋለን ይህም ይስተካከል

✍ ኢብኑ ኸይሩ
ከምን ይሆን የምንማረው?
~~~~~~~~~
በወቅታዊ የሃገራችን ፖለቲካ ትኩሳት የተነሳ ብዙ ነገር እያየን፣ ብዙ ነገር እየሰማን ነው። አላህ ከጠበቀው በስተቀር አብዛኛው ሰው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የችግሩ አካል ሆኗል። ዛሬ ገዳይ ለምን እንደሚገድል፣ ሟች በምን ሰበብ እንደሚገደል በማያውቁበት ሁኔታ እንደዋዛ የሰው ነፍስ እየጠፋ ነው። ነቢዩ - ﷺ - እንዲህ ብለው ነበር፡-
" والذي نفسي بيده ليأتين على الناس زمان لا يدري القاتل في أي شيء قتل، ولا يدري المقتول على أي شيء قتل"
“ነፍሴ በእጁ በሆነው ይሁንብኝ! በሰዎች ላይ ገዳይ በምን ጉዳይ እንደገደለ፣ ሟች በምን ጉዳይ እንደተገደለ የማያውቅበት ዘመን ይመጣል።” ሙስሊም የዘገቡት ነው።
እያየን ያለነው በአመዛኙ ይህንን ነው። በተልካሻ ነገር ህይወት ይቀጠፋል። በተልካሻ ሰበብ ደም ይፈሳል፣ አካል ይቆስላል፣ ደካማ ያለቅሳል፤ ህይወት ይመሰቃቀላል። እንደዋዛ የደካሞች ንብረት ወደ አመድነት እየተቀየረ ነው። ሁሉም የራሱን አጥፊ ከመኮነን፣ ጠማማውን ለማቃናት ከመጣር ይልቅ ጣት የሚቀስርበት ነው የሚፈልገው። ጭፍን ወገንተኝነት አናታችን ላይ ወጥቷል። ስንኮንንም፣ ስናወድስም እየመረጥን ነው፣ የኛና የነሱ ብለን። ከግል እስከ መንግስት ያሉ ሚዲያዎችን ታዘቡ። እየመረጡ ያራግባሉ፤ እየመረጡ ያልፋሉ። አብዛኛው ህዝብም በዚሁ ፋሺን የተሰፋ ሆኗል። ማዶ ለማዶ ቆሞ እሳት የሚጭረውን አጋጋይ (አክቲቪስት) ታዘቡማ። የሌሎችን ጭራቅነት ለማሳየት እስከ ጥግ ይሟሟታል። በራሱ ወገኖች ደካሞች ላይ የሚፈፀመውን ግን እንዳላየ ነው የሚያልፈው። ከተቸም በስሱ ነው የሚነካው። ይሄ ምናልባት የሁሉም ካልሆነ የብዙሃኑ መታወቂያ ሆኗል። እንዲያውም ከሸረሪት ድር የደከሙ ሰበቦችን እየደረደረ የወገኖቹን ጥፋት “ጀስቲፋይ” ሲያደርግ ነው የሚታየው። እንዲያውም ይሄ ከአጋጋዩ አልፎ የአብዛኛው ህዝብ ባህሪ ከሆነ ሰነባበተ። ይህ ባይሆን ኖሮ እነዚህ እሳት አራጋቢዎች ገበያቸው ባልደራ ነበር። ይሄ ግን ለእሳት ጫሪውም፣ ለአጋጋዩም፣ ዳር ቆሞ ለሚታዘበውም አይጠቅምም። ሁላችንም የራሳችንን ክፉ አመል ልንገታ፣ ዋልጌዎቻችንን እጃቸውን ልንይዝ ይገባል። ካልሆነ ግን ውጤቱ አስከፊ ነው።
በእንደዚህ አይነት ከባድ ጊዜ የእርስ በርስ ምክክራችን ከወትሮው ሊጠናከርና ልንተዋወስ ይገባል። አኺል ከሪም ኡኽቲል ከሪማህ! እኛ ሙስሊሞች ነን። የወቃሾች ወቀሳ ሳያስፈራን እያንዳንዱን ነገር በሃይማኖት መነፅር ልንመለከት ይገባል። ኢስላም ማለት መስጂድ ውስጥ ብቻ የሚፈፀም ሳይሆን መላ ህይወታችንን የሚዳስስ እምነት ነው። ከፊታችን ሞት አለ። ከፊታችን ከአላህ ፊት ቆሞ መመርመር አለ። ከፊታችን እሳትና ጀነት አለ። የዛሬ ስግብግብ ምኞት ነጋችንን እንዳያጨልምብን እንጠንቀቅ። ከዛሬ ይልቅ ለነጋችን ቅድሚያ እንስጥ። ጌታችን እንዲህ ብሏል፡-
وَمَا هَٰذِهِ الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا لَهْوٌ وَلَعِبٌ ۚ وَإِنَّ الدَّارَ الْآخِرَةَ لَهِيَ الْحَيَوَانُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ
“ይህቺም የቅርቢቱ ህይወት መታለያና ጨዋታ እንጂ ሌላ አይደለችም። የመጨረሻይቱም አገር እርሷ በእርግጥ የዘላለም ህይወት አገር ናት። የሚያውቁ ቢሆኑ ኖሮ፤ (ጠፊን ህይወት አይመርጡም ነበር)።” [አሩም፡ 64]
ስለሆነም እያንዳንዷ እርምጃችን ይህንን ከግምት ባስገባ መልኩ መሆን አለባት። ወንድም እህቶቼ! ማንም የእኛ ቀብር አይገባልንም። ማንም የእኛን ምርመራ አይመረመርልንም። ስለዚህ ቆም ብለን እንመልከት። ነገ ከአላህ ፊት የሚያሳፍረን ተግባር ውስጥ እንዳንገባ እንጠንቀቅ። በራሳችን ላይ እንዲፈፀም የማንፈልገውን በደል ሌሎች ላይ አንፈፅም። በደል ነገ ንብርብር ጨለማ ነው። ማንንም በህይወቱ፣ በንብረቱ፣ በክብሩ እንዳንበድል እንቆጠብ። በደል ነገ ቀርቶ ዛሬንም ያጨልማል። ነቢያችን - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፡-
اتَّقُوا دَعْوَةَ الْمَظْلُومِ وَإِنْ كَانَ كَافِرًا فَإِنَّهُ لَيْسَ دُونَهَا حِجَابٌ
“የተበዳይን ዱዓ ተጠንቀቁ፤ ከሃዲ እንኳን ቢሆን። ምክንያቱም (አላህ ዘንድ ከመድረስ የሚያግዳት) መጋረጃ የለምና።”
ወንድም እህቶች! ሶሪያ ያማረች አገር ነበረች። የህዝቦቿም ኑሮ ከኢትዮጵያ ህዝብ ኑሮ በእጅጉ የተሻለ ነበር። ዛሬስ? ዛሬማ ሶሪያ ፈርሳለች። ወደነበረችበት ለመመለስ ዘመናት ያስፈልጓታል። እጅግ በርካታ ህዝቦቿ በአሰቃቂ ሁኔታ አልቀዋል። ሚሊዮኖች በመላው አለም ተበትነዋል። ከፊሎቹ በስደት ላይ ውሃ በልቷቸዋል። ከፊሎቹ ኢትዮጵያም አገር ሆና ወደኛ መጥተዋል። ያለ ጥርጥር ትላንት ላይ ሆነው የዛሬ ሁኔታቸውን ቢመለከቱ ኖሮ ጥፍራቸውን በሰበሰቡ ነበር። ግና እድላቸው አምልጧቸዋል። የሚያሳዝነው እኛ ከነሱ ልንማር አለመፈለጋችን ነው። “እድለኛ ማለት ከሌሎች የሚማር ነው” የሚል አባባል ነበራቸው ዐረቦች። ብዙዎቹ አልተማሩበትም እንጂ። አዎ “ብልጥ ሌሎች ላይ ከሚደርሰው ይማራል። ሞኝ ግን ራሱ ላይ ከሚደርሰው ነው የሚማረው።” እኛስ ከየትኛው ምድብ ነን? ሌሎች ላይ የደረሰውን አይተናል። ግን አልተማርንበትም። እዚሁ ባቅራቢያችን የተለያዩ ክስተቶች እየደረሱም እያየን ነው። ይህም እያስተማረን አይመስልም። ይህ ሁሉ ካላስተማረን ምን ይሆን የሚያስተምረን?
ሳጠቃልል ከበደል እንቆጠብ። በደል ውጤቱ መሪር ነውና። ሰዎች ነንና እንሳሳታለን። ባይሆን አንዳችን ሌላችንን ለማረም አንቦዝን። ተግባራችንም፣ ንግግራችንም በፍትህ ይሁን። የምንናገረውም፣ የምንፅፈውም፣ የምናሰራጨውም ፍትሕ የሰፈነበት ይሁን። ጌታችን እንዲህ ሲል በፍትህ አዞናል፡-
﴿ إِنَّ اللَّهَ يَأْمُرُ بِالْعَدْلِ وَالْإِحْسَانِ وَإِيتَاءِ ذِي الْقُرْبَى وَيَنْهَى عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنْكَرِ وَالْبَغْيِ يَعِظُكُمْ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّرُونَ﴾
“አላህ በፍትሕ፣ በማሳመርም፣ ለዝምድና ባለቤት በመስጠትም ያዛል። ከብልግና፣ ከመጥፎ ነገር እና ከመደበልም ይከለክላል። ትገነዘቡ ዘንድ ይገስፃችኋል።” [አነሕል፡ 90]
በተለያዩ ምክንያቶች የምንጠላቸው ሰዎች ካሉም ጥላቻችን ድንበር አያሳልፈን። የላቀው ጌታ እንዲህ ይላል፡-
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُونُوا قَوَّامِينَ لِلَّهِ شُهَدَاءَ بِالْقِسْطِ ۖ وَلَا يَجْرِمَنَّكُمْ شَنَآنُ قَوْمٍ عَلَىٰ أَلَّا تَعْدِلُوا ۚ اعْدِلُوا هُوَ أَقْرَبُ لِلتَّقْوَىٰ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ለአላህ ቀጥተኞች በትክክል መስካሪዎች ሁኑ። ህዝቦችንም መጥላት ባለማስተካከል ላይ አይግፋችሁ። አስተካክሉ። እርሱ (ማስተካከል) ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነውና። አላህንም ፍሩ። አላህ በምትሰሩት ሁሉ ውስጠ አዋቂ ነው።” [አልማኢዳህ፡ 8]
በሐዲሠል ቁድሲይም እንዲህ ብሏል፡-
يا عبادي، إني حرمت الظلم على نفسي وجعلته بينكم محرماً فلا تظالموا
“ባሮቼ ሆይ! እኔ በደልን በራሴ ላይ ክልክል አድርጌያለሁ። በእናንተ መካከልም ክልክል አድርጌዋለሁ። ስለሆነም አትበዳደሉ።” ሙስሊም ዘግበውታል።
በአላፊ ብልጭልጭ ጥቅሞች፣ በጊዜያዊ ሆይሆይታዎች፣ በወገ
ናዊ ስሜቶች፣ በጭፍን ጥላቻዎች፣ ባጋደሉ ትርክቶች፣ … ተነሳስተን ሰላማዊ ሰዎችን እንዳንጎዳ እንጠንቀቅ፡፡ ካልሆነ ግን ከነሱ በላይ የምንጎዳው እኛ ነን፡፡ በፍርዱ ቀን በገንዘብ የማይካስ፣ በዋዛ የማይታለፍ ምርመራ ይጠብቀናል፡፡ ዋ ያኔ! ዛሬ በዘር፣ በቋንቋ የሚማግደን ሁሉ ለኛ ቀርቶ ለራሱም አይሆንም፡፡ “የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም፡፡”
ሙዚቃ የሚያዳምጥ ሰው ፡ ቁርአን መቅራትና ማዳመጥ ክብድ ብሎ ይታየዋል።

ኢብኑል ቀይም
✍አንዱ የሱፍያን አሠውሪይ ረሂመሁላህ ጓደኛ፤ "አጠር ያለች ምክርን ይለግሱኝ።" ሲል ደብዳቤ ፃፈላቸው።
እሳቸውም፦
📄"እኔንም ሆነ አንተን ከመጥፎ ሁሉ አላህ ይጠብቀንና ይበለንና!
ወንድሜ ሆይ! ዱንያ ማለት፤ ጭንቀቷ አያልቅም፣ደስታዋ አይዘወትርም፣ሀሳባ አይጨረስም። ስለሆነም ከፈታናዎቿ እስክትድን ለነፍስህ ስትል መልካምን ስራ፣ ዛሬ ነገ እያልክ ወደኋላ አትበል ለጥፋት ትዳረጋለህ። ሰላም ባንተ ላይ ይሁን(አበቃሁ)።"
📕 ሒልየቱ አል አወሊያ(7/5)

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ስሙ የሸይኸ ሷሊህ አል ፈውዛንን ሀፊዘሁሏህ መተናነስን !

تواضع الشيخ الفوزان حفظه الله لما سُئل:
كيف الوصول الى علم الشيخ ابن باز وعلمكم ؟!!
https://t.me/Umu_Meryem
♻️♻️🔺ጣፋጭ ምክር🔺♻️♻️

🔵‏قـال الـشّيخ صالح الـفوزان حفــظه الله تعالى:
✅ ሸህ ፈውዛን (አላህ ይጠብቃቸውና) እንዲህ ይላሉ።

الـّذِيْ نـُوْصِيْ بِهِ أَنـْفُـسَنَـا وَإِخْـوَانَنَـا
تَـقـْوَى اللّهِ، والـتّمَسُـكُ بِمَنْـهَجِ الـسّـَلـَفِ الـصَّالـِحِ ؛

♻️ እኛንም ወንድሞቻችን #አደራ የምንለው ፦
🔺አላህን መፍራትና
🔺በደጋግ ቀደምቶች (በሰለፎች) መንገድ አጥብቀው በመያዝ ላይ ነው

الّـذِيْ نُـوْصِيْ بِهِ أَنـْفُـسَنـَا وَإِخْـوَانَنـَا
الـحـَذَرُ مِنَ الـبِـدَعِ وَالـمُبْتَدِعـِيْنَ ؛

♻️ እኛንም ወንድሞቻችን #አደራ የምንለው ፦
🔺ከቢድአና
🔺ከቢድአ ባልተቤቶችን በመራቅ ላይ ነው

الـّذِيْ نـْوْصِيْ بِهِ أَنـْفـُسَنَـا وَإِخْـوَانَنـَا
الـعِنَـايَة بـِدِرَاسَـةِ الـعَقِـيْدَةِ الـصَّحِيْحـَةِ وَمـَا يُضَـادُّهَـا ؛

♻️ እኛንም ወንድሞቻችን #አደራ የምንለው ፦
🔺ትክክለኛውና የተስተካለው አቂዳ
🔺የሷ ተቃራኒ የሆነውን (የተባለሸ አቂዳ) በመማርና በማስተማርና በመራቅ ላይ ነው

الـّذِيْ نـُوْصِيْ بِهِ أَنـْفـُسَنـَا وَإِخـْوَانَنـَا
الأَخـْذَ عَنِ الـعُلَمَـاءِ الـمُوْثُوقِيْنَ فِي عِلْـمِهِمْ وَفَي عَـقِيْدَتـِهِمْ ؛

♻️ እኛንም ወንድሞቻችን #አደራ የምንለው ፦
🔺በአቂዳቸውና
🔺በእውቀታቸው አስተማማኝ (የሰለፎችን ጎዳና ከሚከተሉ) ኡለማዎች ኢልምን በመውሰድ ላይ ነው
الـّذَيْ نـُوْصِيْ بهِ أَنْفُـسَنَـا وَإِخـْوَانِنـَا
الـحَذَر منْ دُعـاةِ الـسُّـوء الـذّيْن يُلـبِسُـونَ الْـحـَقّ بِالـبَاطِـلِ.

♻️ እኛንም ወንድሞቻችን #አደራ የምንለው ፦
🔺ከመፍፎ (ከአጥማሚ) ዳኢዎችና
🔺እውነትን በውሸት ከሚያለባብሱ ተጣሪዎች በመራቅ ላይ ነው
📕 [ الأجوبة المفيدة ص١١٢ ]
Forwarded from Deleted Account
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
👉 አንድ ሴት ባሏ ኒቃብ ቢጠላና ፊቷን እንድትገልጥ ቢያዛት ልትታዘዘው አይገባም የሱን ሀቅ ከመጣስ አይቆጠርም

👉 አንዳንድ አላዋቂዎች ኒቃብ #ሱና ነው ባልን መታዘዝ #ግዴታ ስለሆነ ልትታዘዘው ይገባል ይላሉ ይህ ግንዛቤ ትክክል አይደለም
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Audio
الدرس الأول من "إرشاد الأنام إلى أصول ومهمات دين الإسلام"

#ኢርሻዱል አናም

#ክፍል (1)

#ቦታ ገራዶ ቢላል መስጊድ

#ሰአት ከመግሪብ ሶላት ቡሃላ

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
እኛማ! አላህ ይድረስልን!

ዘይድ አልያሚ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:–
"አንዲት የኢብኑ መስዑድ ንግግር ሃያ አመት ዝም አስብላኛለች። እሷም:
‘ንግግሩ ተግባሩ ጋር የማይገጥም የሆነ ሰው እራሱን ነው የሚወቅሰው’ የምትለዋ ነች።"
[ዑዩኑል አኽባር: 2/179]
Audio
ስለ ድንበር ማለፍ በኡስትዝ ኢብኑ ሙነወር

👇👇👇👇👇👇

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
►◉ወደ ሸር እሚጣሩ ብዙ ናቸው በኢስላም ስም ወደ እሳት በር እሚጣሩ ‼️

►◉ወደ ኸይር እሚጣሩ ግን ጥቂት ናቸው እነሱ ናቸው ኸይር ለእነሱ 《ጡባ እሚባል ጀነት》
አላችው‼️

🎤ሸይኽ ፈውዛን ሃፊዘሁላህ

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
ዚክር፣ የዘነጋነው ሃብት
~~~~~~~~>
መቼም ሰው ነንና ፈራሽ እንደሆንን እናውቃለን። እንደ ሙስሊም ከሞት በኋላ ህይወት እንዳለ እናምናለን። ስለሆነም የአኺራችን ጉዳይ ያስጨንቀናል። ለዚህም ሲባል በጌታችን ህግ ለመኖር፣ ትእዛዛቱን ለመፈፀም ክልከላውን ለመራቅ፣ ስለ ድክመታችን ተውበት ለማድረግ እንሞክራለን። ሆኖም ግን አንድ በቀላል ጥረት ብዙ ትርፍ የምንሸምትበትን ነገር ስንዘነጋ እንስተዋላለን።
አዎ ስራሽን እየሰራሽ፣ መኪናህን እየሾፈርክ፣ ወረፋ እየጠበቃችሁ፣ በመኪና እየተጓዝክ፣ ሰው እየጠበቅሽ፣ በእግራችን እየተንቀሳቀስን፣… ዚክር ቢደረግ በየእለቱ ስንትና ስንት አጅር በሰበሰብን ነበር። ዚክር ከምናስበው እጅግ የላቀ ፋይዳ አለው። ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዲህ ብለዋል:–
"أَلَا أُنَبِّئُكُمْ بِخَيْرِ أَعْمَالِكُمْ، وَأَزْكَاهَا عِنْدَ مَلِيكِكُمْ، وَأَرْفَعِهَا فِي دَرَجَاتِكُمْ، وَخَيْرٌ لَكُمْ مِنْ إِنْفَاقِ الذَّهَبِ وَالْوَرِقِ، وَخَيْرٌ لَكُمْ مِنْ أَنْ تَلْقَوْا عَدُوَّكُمْ، فَتَضْرِبُوا أَعْنَاقَهُمْ، وَيَضْرِبُوا أَعْنَاقَكُمْ ".
قَالُوا : بَلَى.
قَالَ : " ذِكْرُ اللَّهِ تَعَالَى".
"ከ(መልካም) ስራዎቻችሁ በላጭ፣
ከንጉሳችሁ ዘንድ የጠራ፣
ደረጃዎቻችሁን ከፍ የሚያደርግ፣
ወርቅና ብር ከመለገስ የሚሻላችሁ፣
ጠላቶቻችሁን አግኝታችሁ አንገቶቻቸውን ከምትመቱና አንገቶቻችሁን ከሚመቱ (ከጂሃድ) የሚበልጥባችሁን አልነግራችሁምን?"

√ (ሶሐቦች):– "እንዴታ! (ይንገሩን) የአላህ መልእክተኛ ሆይ" አሉ።
"አሸናፊና የላቀውን አላህ ማውሳት" አሉ።
[ቲርሚዚ ዘግበውታል: 3377]

ትልልቅ ምንዳ ያላቸው አጫጭር ዚክሮች
~~~~~~~~~~~~~~~~~
① ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዲህ ብለዋል:–
(مَن قال: سبحان الله وبحمده، في يوم مائة مرة، حُطَّت خطاياه وإن كانت مثل زبد البحر)؛
"በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ ‘ሱብሓነላ፞ሂ ወቢሐምዲሂ’ ያለ ሰው ወንጀሎቹ እንደ ባህር አረፋ ቢሆኑ እንኳን ይረግፉለታል።" [ቡኻሪ]

② እናታችን ጁወይሪያህ ቢንቲል ሓሪሥ ረዲየላ፞ሁ ዐንሃ ባስተላለፈችው በአንድ ወቅት ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም ሱብሕን ከሰገዱ በኋላ ማለዳ ላይ ከሷ ዘንድ ወጡ። እሷ መስገጃዋ ላይ ተቀምጣ ዚክር ላይ ነች። እዚያው እንደተቀመጠች ረፋድ ላይ ተመለሱ።
"ካንቺ ከተለየሁ ጊዜ አንስቶ እስካሁን በተለየሁብሽ ሁኔታ ላይ ከመሆን አልተወገድሽም?" አሏት።
"አዎ" አለች።
በዚህን ጊዜ እንዲህ አሉ:–
" لَقَدْ قُلْتُ بَعْدَكِ أَرْبَعَ كَلِمَاتٍ ثَلَاثَ مَرَّاتٍ، لَوْ وُزِنَتْ بِمَا قُلْتِ مُنْذُ الْيَوْمِ لَوَزَنَتْهُنَّ : سُبْحَانَ اللَّهِ وَبِحَمْدِهِ عَدَدَ خَلْقِهِ، وَرِضَا نَفْسِهِ، وَزِنَةَ عَرْشِهِ، وَمِدَادَ كَلِمَاتِهِ ".
"በእርግጥም ካንቺ በኋላ አራት ንግግሮችን ሶስት ጊዜ ተናግሬያለሁ። ከንጋት ጀምሮ አንቺ ካልሺው ጋር ቢመዘኑ (እኔ ያልኳቸው) ይመዝናሉ።
ሱብሓነላ፞ሂ ወቢ ሐምዲሁ ዐደደ ኸልቂሁ፣
ወሪዷ ነፍሲሂ፣
ወዚነተ ዐርሺሂ፣
ወሚዳደ ከሊማቲሂ።" [ሙስሊም የዘገቡት]

③ ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዲህ ብለዋል:–
(كلمتان خفيفَتان على اللسان، ثقيلَتان في الميزان، حبيبَتان إلى الرحمن: سُبحان الله وبحمده، سبحان الله العظيم)؛
"ምላስ ላይ የቀለሉ፣ ሚዛን ላይ የከበዱ እና አረ፞ሕማን ዘንድ የተወደዱ ሁለት ንግግሮች አሉ። ‘ሱብሓነላ፞ሂ ወቢሐምዲሂ፣ ሱብሓነላ፞ሂል ዐዚም።" [ቡኻሪና ሙስሊም]

④ ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም ከጀነት ድልብ ሃብቶች ውስጥ እንደሆነ የገለፁት የዚክር አይነት
(لا حول ولا قوة إلا بالله)؛
"ላ ሐውለ ወላ ቁወ፞ተ ኢላ፞ ቢላ፞ህ" [ኢብኑ ሒባ፞ን]

⑤ ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዲህ ብለዋል:–
(مَن قال: لا إله إلا الله وحده لا شريك له، له الملك وله الحمد وهو على كل شيء قدير - عشر مرات - كان كمَن أعتق أربعة أنفُسٍ مِن ولد إسماعيل)

"አስር ጊዜ ’ላ ኢላሀ ኢለ፞ላ፞ህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ። ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ። ወሁወ ዐላ ኩሊ፞ ሸይኢን ቀዲር’ ያለ ሰው ከኢስማዒል ልጆች አራት ነፍሶችን ነፃ እንዳወጣ ነው።" [ሙስሊም]

⑥ ነብዩ ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዲህ ብለዋል:–
(سيِّد الاستغفار أن تقول: (اللهمَّ أنت ربي، لا إله إلا أنت، خلقتَني وأنا عبدُك، وأنا على عهدك ووعدك ما استطعتُ، أعوذ بك من شرِّ ما صنعتُ، أبوء لك بنعمتك عليَّ، وأبوء لك بذنبي، فاغفر لي، فإنه لا يغفر الذنوب إلا أنت، قال: ومَن قالها من النهار موقنًا بها، فمات من يومه قبل أن يُمسي فهو مِن أهل الجنَّة، ومَن قالها من الليل وهو مُوقن بها، فماتَ قبْل أن يُصبح، فهو مِن أهل الجنَّة)؛
"የኢስቲግፋር ሁሉ አለቃ ‘አላ፞ሁመ፞ አንተ ረቢ፞ ላ ኢላሀ ኢላ፞ አንተ። ኸለቅተኒ። ወአነ ዐብዱከ። ወአነ ዐላ ዐህዲከ ወወዕዲከ መ’ስተጦዕቱ። አዑዙ ቢከ ሚን ሸሪ፞ ማ ሶነዕቱ። አቡኡ ለከ ቢኒዕመቲከ ዐለየ፞። ወአቡኡ ለከ ቢዘንቢ። ፈግፊር ሊ። ፈኢነ፞ሁ ላ የግፊሩ ዙ፞ኑበ ኢላ፞ አንተ’ የሚለው ነው።
በሷ አረጋግጦ በቀኑ ካላት በኋላ ሳያመሽ በእለቱ የሞተ ሰው እርሱ ከጀነት ሰዎች ነው። በሷ አረጋግጦ በሌሊት ካላት በኋላ ሳያነጋ የሞተ ሰው እርሱ ከጀነት ሰዎች ነው።" [ቡኻሪ]

እነዚህ ምሳሌዎች ብቻ ናቸው። ሌሎችም ብዙ አሉ። ከነዚህ በተጓዳኝ ከውዱእ በኋላ፣ ከአዛን በኋላ፣ መስጂድ ስትገባ፣ ከመስጂድ ስትወጣ፣ ከሶላት በኋላ፣ ከምግብ በኋላ፣ ስትተኛ፣ ስትነሳ፣ ወዘተ ያሉትን ብትል ቆጥረህ የማትዘልቀው አክተር አለህ።
በጥቅሉ ጊዜህን መድበህ ዚክርን የህይወትህ አካል አድርገው። ለዚህ ከተቸገርክ እየሰራህ፣ እየተጓዝክ ዚክር ትኩረት እንጂ የረባ ጥረት አይጠይቅህም። መልእክተኛው ሶለ፞ላ፞ሁ ዐለይሂ ወሰለ፞ም እንዳሉት "ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አትወገድ።"

✍ ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁሏህ

@IbnuMunewor

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
👉ሴት ልጅ ከሀይዷ ከጠራችና ደሙ ከተቋረጠ በኋላ መታጠብና ኢባዳዋን መቀጠል ይኖርባታል
👉ደሙ ከተቋረጠ በኋላ ለሚወጣው ፈሳሽ ቦታ ልትሰጠው አይገባም።
👉ደሙ ከተቋረጠ በኋላ የሚፈሰው ፈሳሽ ሁክሙ እንደ ሽንት ነው የነካው ሰውነቷም ሆነ ልባሷን በማጠብ እስቲንጃእ በማድረግ በኢባዳዋ መቀጠል አለባት
👉ስለዚህ አንድ ሴት ከሀይድ መጥራቷን ምታረጋግጠው ደሙ በመቋረጡ እንጂ ከዛ በኋላ በሚፈሰው ፈሳሽ እንዳልሆነ ልታውቅ ይገባል

🎙 ج/ الشيخ العلامة الإمام:
محمد بن صالح العثيمين
-رحمه الله تعالى-
https://t.me/joinchat/AAAAAFgdAPPfoRzUemL4vw
صفات الزوج الصالح
ሸይኽ ፈውዛን (ሀፊዘሁላህን)
➧ወንዶች ጥሩ ሚስት እነደሚያስፈልጋቸው ሁሉ ሴቶችም ጥሩ ባል ያሰፈልጋቸዋል፡፡

➧በሁለቱም ወገን ትዳር ሲታሰብ ጥሩ ጓደኛ ወይም የሂይወት አጋር የሚሆን ሰው ማግኘት ዋናውና አሳሳቢው ጉዳይ ነው፡፡

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w