💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
አንድ አህያ ሞታ መስጂድ በር ላይ ትጥላለች። ታዲያ ምዕመናኑ ሲወጣ ሲገባ ሽታው አላስወጣ አላስገባ ቢላቸው አንድ የመስጂድ ኢማም ለከተማዋ ከንቲባ ይደውሉና «አህያ ሞታ መስጂዳችን በር ላይ ተጥላለች እባካችሁ ... » ብለው ወሬ ከመጀመራቸው…
ከንቲባው በንቀት:
«ሙታንን አጥቦ ገንዞ መቅበርኮ የእናንተ የኃይማኖት አባቶች ስራ መሰለኝ ሲላቸው!»
ኢማሙ ተናደው:
«እሱስ አዎ! ግን ያው ከመቅበራችን በፊት ለቤተሰቦቿ መርዶ እንገር ብለን ነው!» "ብለውት እርፍ"

አንዳንድ ኢማሞች እኮ አይናገሩ እንጂ ከተናገሩ የመልስ ምታቸው ናላ ያዞራልi

t.me/abdu_rheman_aman
እራሳችንን በእራሳችን በቁርኣን እናክም!
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

✍[ ክ ፍ ል አ ን ድ]

✳️ብዙ ሰዎች በተለያዬ ምክንያት ሩቃ ቤት በመፈለግ በጣም ሲቸገሩ ይስተዋላል!

በተለይ  ከሃገር ወጭ የሚኖሩ እህትና ወንድሞች! !
ልክ እንዲሁ ሐገር ውስጥ ያሉትም ቢሆን " ታማኝ " ሩቃ ቤትን ስለሚፈልጉ እነርሱም በፍለጋ ይቸገራሉ ..

በጣም ችግሩ የጠናባቸው ደግሞ "በኢንተርኔት ሩቃ "አስደርገው " ብራቸውን "ሲበዘበዙ ይስተዋላል !

✅ ሁሉም ሰው ማዎቅ ያለበት ነገር  አላህን መፍራትና ዱአ ማብዛት ፣ ለበሽታዎች ሁሉ ፈውስ መሆን ዋነኛው ሰበብ ቁርአን ነው። ከቁርኣን መገለጫዎች መካከል አንዱ ደግሞ "ሺፋእ/ መድሃኒትነቱ" መሆኑ ነው።


➖አላህም(ሱብሃነሁ ወተዓላ) ፈውስነቱን ሲገልፅ ⤵️

ከቁርኣንም ለምእመናን <መድኀኒትና> እዝነት የኾነን እናወርዳለን፡፡ በዳዮችንም ከሳራን እንጂ ሌላ አይጨምርላቸውም፡፡ ይላል

وَنُنَزِّلُ مِنَ الْقُرْآنِ مَا هُوَ شِفَاءٌ وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ ۙ وَلَا يَزِيدُ الظَّالِمِينَ إِلَّا خَسَارًا

ቁርኣን፣ነቢያዊ ዚክርና ዱዓዎች (ሩቃ) ለሁሉም አይነት በሽታና ችግሮች መፍትሄ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።

↘️እናም ማንኛውም በቁርኣን ፈውስነት የሚያምን ግለሰብ ፋቲሓንና ሌሎችንም አጫጭር (በቀላሉ መቅራት የሚችላቸውን) ሱራዎች እንኳ ቢሆን እየቀራ ለራሱ " ሩቃ "ማድረግ ይችላል።

📌ራስን በራስ ለማከም ካልተቻለና ነገሩ ከጠና ሩቃ አድራጊ ፍለጋ ርቆ ለመሄድ ሳንገደድ፤ በቤተሰብ፣ አሊያም በዘመድና በጎረቤት ማስደረግ ይቻላል።

┈•••✿❒❒✿•••┈┈┈┈•••✿❒❒✿•••┈┈

ነገርግን ከዚህ ካለፈ በዲን የተሻለ እውቀት እና አላህን በመፍራት ወደ የሚታዎቁ የሩቃ ሃኪም ቤት መሄዱ መልካም ነው።

📚ለህክምና ዋናው ነገር ብዙ መቅራቱ ሳይሆን አላህን በሚፈራና ተወኩል ባለው ልብ፣ በቁርኣን ፈዋሽነት አምኖ ፋቲሓን እና ሙአዊዘተይን ወዘተ.. በነቢያዊ ዱአ እና አዝካሮችን በመቅራት ለመዳን በቂ ሰበብ ነው!።

ነቢዩና ﷺ ሰሓቦቻቸውም በነዚህ ምእራፎች ሩቃ ያደርጉ እንደ ነበር ብዙ መረጃዎች ያስረዳሉና።


🤲 የላቀውና ከፍ ያለው አላህ ለታመመ ሁሉ ፈውሱን ቅርብ ያድርግለት 🤲 አሚን

✍ ወንድማችሁ ኡስማን ሰዒድ (አቡ አመቲረህማን)

🎓 ለሌሎች ትምህርቱን ያስተላልፉ!
https://t.me/alruqyehsheriyeh
https://t.me/alruqyehsheriyeh

ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል !!
ከሽፉ ሺቡሃት 008
አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
🎈መትን ከሽፉ ሹቡሓት

【 ክፍል  ➇ 】

🎙«𝐁𝐲 𝐀𝐛𝐮 𝐑𝐞𝐲𝐲𝐢𝐬 𝐈𝐛𝐧𝐮 𝐢𝐦𝐚𝐦 »

          √ የኪታብ 𝕡𝕕𝕗↓↓
t.me/https_Asselefya1/13134
«አባዬ»
➖➖➖
እወድክ አለሁ ብየ ነግሪክ ባላዉቅም፣
አባ እወድሀለሁ ባንተ ቀልድ አላዉቅም፣

ለጅ ያድጋል ብለህ የለፋኸዉ ልፍት፣
እንግልት ድካም ሀሳብና ጭንቀት፣

ያላየኸዉ የለም ያልሰራኸዉ ስራ፣
ኩራት እድሰማኝ በስምህ ሰጠራ፣


አንሸ እዳልታይ የማንም የበታች፣
ያላየኸዉ የለም ስትል ከላይ ከታች፣

ስትለፋ ድካምህ ስታጣ ጭንቀትህ፣
ብዙ ትጥራለህ ለወለድከዉ ልጅህ፣
አንተን የመግለጫ ቢያንስብኝ ዉለታህ፣
ለኔ ደስታዬ ነዉ መጠራት በስምህ፣
ዉለታህ አሳስቦኝ ሌት ቀን ባስብልህ፣

ዛሬ እኔም አድጌ አባት ብሆንልህ፣
ካልፈጠርኩኝ ደስታ ላንተም ካልኖርኩልህ፣
ልጄ ብለህ ጠርተህ አባዬ ካላልኩህ፣
እርፍትን ፈልገህ ድካም ከተሰማህ፣

የልጅ ሀቅ ልወጣ እኔም ልኑርልህ፣
ለስከዛሬዉ ጥፋት ይቅርታ ጠየቁህ፣
የስሜ መጠሪያ አሏህ ይጠብቅህ፣

✍️ሶላሁዲን አቡ ዑበይዳህ

⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱⋰⋱
t.me/selahudin_Islamic_knowlages
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
❝የሙናፊቆች ባህሪያት❞ ➖〰➖〰➖〰➖〰    ÂŤ ክፍል   ⓸» 🍁ሪያእ(እዩልኝ) ማለት፦አንድ ሰዉ የአምልኮን ተግባር ሲፈጽም  ሰዎች አይተዉ እንድያደንቁት  እንድያወድሱት እና እንድያሞግሱት በመፈለግ ግልፀ አድርጎ  መስራት ማለት ነዉ። 🍁ሱምዓ(ስሙልኝ)ማለት፦ደግሞ አንድ ሰዉ የአምልኮን ተግባር ሲፈጽም ሰዎች ሰምተዉ  እንድያደንቁት እንድያወድሱት እና እንድያሞግሱት በመፈለግ መናገር ማለት ነዉ። 🍁ሪያዕ…
❝የሙናፊቆች ባህሪያት❞
➖〰➖〰➖〰➖〰

ÂŤ ክፍል  ⓹ Âť

↷ከሙናፊቆች ጋር ተባብሮ መስራት ብይኑ↶

◉ قال تعاى: { سَیَحۡلِفُونَ بِٱللَّهِ لَكُمۡ إِذَا ٱنقَلَبۡتُمۡ إِلَیۡهِمۡ لِتُعۡرِضُوا۟ عَنۡهُمۡۖ فَأَعۡرِضُوا۟ عَنۡهُمۡۖ إِنَّهُمۡ رِجۡسࣱۖ وَمَأۡوَىٰهُمۡ جَهَنَّمُ جَزَاۤءَۢ بِمَا كَانُوا۟ یَكۡسِبُونَ }

↺አላህ እንድህ ይላል፦ እነርሱንም(ሙናፊቆች)ተዋቸዉ። እነርሱ እርኩሶች ናቸዉ።ይሰሩትም በነበሩበት ዋጋ መኖሪያቸዉ ገሀነም  ነዉ። አት_ተዉባህ:95


☛ይህቺ የቁርአን አያህ  ማስረጃ በማድረግ  ኢዝ_ብኑ ዐብዲስ_ሰላም የተባሉ ዓሊም ሙናፊቆች መራቅ ግድ ነዉ ይላሉ።

☛ሙነፊቆች  በዉስጣቸዉ ክህደት ስለሆነ የለሞላዉ  አላህ  ሲሞቱ  በነሱ ላይ እንዳይሰገድ አዘዘ፤ሐእነርሱም እዝነት እና ምህረት  እንዳይጠየቅላቸዉ ደነገገ፣ ንፍቅናቸዉ  ግልፀ ሆኖ የታወቀ እና በማስረጃዎች የተረጋገጠ ከሆነ  ከእነርሱ የሚኖር እይታ እና ምልከታ ከከሐድዎች  እና ከአጋሪዎች የማይተናነስ ነዉ። የበለጠ ሊሆን የሚችልበትም አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል።

☛ንፍቅናቸዉን ግልፀ ያወጡም ይሁን  ሰዉን ለማታለል እና ለመሸወድ ብለዉ  የደበቁም አንድ ናቸዉ። ሙናፊቆች ላይ ጠንከር ያለ አቋም ማንፀባረቅ  የእምነት ጥንካሬ ምልክት እንጂ ሙርጅአዎች እና መሰሎቻቸዉ እንደሚሉት የአክራሪነት መገለጫ አይደለም።ለዚህ ማስረጃዉ አላህ በምናፍቃን ላይ እንዳይሰገድና በቀብራቸዉም ላይ ተቁሞ ምህረት እንዳይለመንላቸዉ የሚከለክለዉን ትእዛዝ ለረሱላችን ﷺማዉረዱ ነዉ።

◉ قال تعالى :{ وَلَا تُصَلِّ عَلَىٰۤ أَحَدࣲ مِّنۡهُم مَّاتَ أَبَدࣰا وَلَا تَقُمۡ عَلَىٰ قَبۡرِهِۦۤۖ إِنَّهُمۡ كَفَرُوا۟ بِٱللَّهِ وَرَسُولِهِۦ وَمَاتُوا۟ وَهُمۡ فَـٰسِقُونَ }

↺አላህ እንድህ ይላል፦ ከእነርሱም በአንድም በሞተ ሰዉ ላይ ፈጽሞ አትስገድ።በመቃብሩም ላይ አትቁም።እነርሱ አላህ እና መልዕክተኛዉን ክደዋል።እነርሱም አመጻኞች  ሆነዉ ሞተዋልና።(አት-ተዉባህ፡84)

◉ قال تعالى:{ ٱسۡتَغۡفِرۡ لَهُمۡ أَوۡ لَا تَسۡتَغۡفِرۡ لَهُمۡ إِن تَسۡتَغۡفِرۡ لَهُمۡ سَبۡعِینَ مَرَّةࣰ فَلَن یَغۡفِرَ ٱللَّهُ لَهُمۡۚ ذَ ٰ⁠لِكَ بِأَنَّهُمۡ كَفَرُوا۟ بِٱللَّهِ وَرَسُولِهِۦۗ وَٱللَّهُ لَا یَهۡدِی ٱلۡقَوۡمَ ٱلۡفَـٰسِقِینَ }

↺አላህ እንድህ ይላል፦ለእነርሱ ምህረትን ለምንላቸዉ ፣ወይሞ ለእነሱ  ምህረትን አትለምንላቸዉ(እኩል ነዉ)።ለእነርሱ ሰባ ጊዜ
ምህረትን ብትለምንላቸዉ አላህ ለነሱ በፍፁም አይምርም።
ይህ እነርሱ  አላህ እና መልዕክተኛዉ መካዳቸዉ ነዉ።አላህሞ አመጻኛ ህዝቦችን አይመራምም። (እት ተዉባህ :80 )

◉ قال تعلى:{ وَإِذَا قِیلَ لَهُمۡ تَعَالَوۡا۟ یَسۡتَغۡفِرۡ لَكُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ لَوَّوۡا۟ رُءُوسَهُمۡ وَرَأَیۡتَهُمۡ یَصُدُّونَ وَهُم مُّسۡتَكۡبِرُونَ } { سَوَاۤءٌ عَلَیۡهِمۡ أَسۡتَغۡفَرۡتَ لَهُمۡ أَمۡ لَمۡ تَسۡتَغۡفِرۡ لَهُمۡ لَن یَغۡفِرَ ٱللَّهُ لَهُمۡۚ إِنَّ ٱللَّهَ لَا یَهۡدِی ٱلۡقَوۡمَ ٱلۡفَـٰسِقِینَ }

↺አላህ እንድህ ይላል፦ለእነሱም፦ኑ የአላህ መልዕክተኛ ለእናንተ ምህረት ይለምንላችኋል ፣በተባሉ ግዜ ራሶቻቸዉን ያዞራሉ። ብትለምናቸዉ ወይም ምሕረትን ባትለምንላቸዉም በእነርሱ ላይ እኩል ነዉ።አላህ ለእነርሱ በፍፁም አይምርም። አላህ  አመፀኞችን ህዝቦች አይመራም ።(አል ሙናፊቁን:5_6)

☛አንድ ሰዉ እምነቱ  የሚሞላዉ የአላህን ወልዮች ባሪያዎች ሲወዳጂ እና የአላህን ጠላቶች ፤የሰይጣንን ባልደረቦች ሰራዊቶች ሲጠላ፣በምላሱ እና በጦሩ ሲወጋ ነዉ።ይህም እስልምና ከመጣባቸዉና ካፀደቃቸዉ ታላላቅ መሠረቶች ዉስጥ አንዱ ነዉ።

☛ሙናፊቆችንና ከሀዲዎችን ጓደኛ አድርጎ መያዝ ንፍቅና ነዉ።ሙናፊቆችን የሚወዳቸዉ ሙናፊቅ ሲሆን የሚጠላቸዉ ደግሞ ሙእሚን ነዉ።

📔ይቀጥላል  ኢንሻ አላህ..........

⇣⇣↷⇣⇣↷⇣⇣↷⇣⇣↷⇣⇣↷⇣⇣↷⇣⇣
https://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
https://t.me/https_Asselefya1
ከሽፉ ሹቡሃት 009
አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢማም
🎈መትን ከሽፉ ሹቡሓት

【 ክፍል  ➈ 】

🎙«𝐁𝐲 𝐀𝐛𝐮 𝐑𝐞𝐲𝐲𝐢𝐬 𝐈𝐛𝐧𝐮 𝐢𝐦𝐚𝐦 »

          √ የኪታብ 𝕡𝕕𝕗↓↓
t.me/https_Asselefya1/13134
⭕️👉ደስተኛ መሆን ትፈልጋለህ? … እንግዲያውስ ዲንህን ተማር እውቀትን ፈልግ።

☑️ ሸኽ ሷሊህ አልፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና እንዲህ አሉ።

«(በዱንያም በአሄራ) ደስታ የምትፈልግ ከሆነ እውቀትን ፈልግ። ባወቅከው ላይም ስራ። የዛኔ በአላህ ፍቃድ ሙሉ ደስታ ታገኛለህ።»

📗شرح منظومة الأحسائي صـ13

𝐓𝐞❝ t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
👌 መንገድ ላይ እነዚህ ሁለት ቡርትካኖችን ብታገኝ የቱን ትመርጣለህ???


መልእክቴ ለሴቶች የደረሰ መሰለኝ…
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
❝የሙናፊቆች ባህሪያት❞ ➖〰➖〰➖〰➖〰 ÂŤ ክፍል  ⓹ Âť ↷ከሙናፊቆች ጋር ተባብሮ መስራት ብይኑ↶ ◉ قال تعاى: { سَیَحۡلِفُونَ بِٱللَّهِ لَكُمۡ إِذَا ٱنقَلَبۡتُمۡ إِلَیۡهِمۡ لِتُعۡرِضُوا۟ عَنۡهُمۡۖ فَأَعۡرِضُوا۟ عَنۡهُمۡۖ إِنَّهُمۡ رِجۡسࣱۖ وَمَأۡوَىٰهُمۡ جَهَنَّمُ جَزَاۤءَۢ بِمَا كَانُوا۟ یَكۡسِبُونَ…
❝የሙናፊቆች ባህሪያት❞
➖〰➖〰➖〰➖

«ክፍል  ⓺ Âť

ከሙናፊቆች ጋር መስራት ብይኑ ከትላት የቀጠለ!


⇘አላህ  ምእምናንን ወደ ከሐድ ዉሸታም ሙናፊቆች እንዳይዘነበሉ እነርሱን ጓደኛና ወዳጂ  አድርገዉ እንዳይዙ በጥብቅ ያስጠነቅቃል።

⇘አላህ የእርሱን ቃል አፍርሶ ከእነርሱ ጋር እነርሱ በአንቀፁና በተአምራቱ ሊያሾፉና ሲያላግጡ አብሮ የተቀመጠና ከእነርሱ ጋር የሆነ ሰዉ ከእነርሱ ምንም አይነት ልዩነት እንደሌለዉና ከእነርሱ ጋር እንደሆነ ሲናገር እንድህ ይላል፦

◉ قال تعالى:{ وَقَدۡ نَزَّلَ عَلَیۡكُمۡ فِی ٱلۡكِتَـٰبِ أَنۡ إِذَا سَمِعۡتُمۡ ءَایَـٰتِ ٱللَّهِ یُكۡفَرُ بِهَا وَیُسۡتَهۡزَأُ بِهَا فَلَا تَقۡعُدُوا۟ مَعَهُمۡ حَتَّىٰ یَخُوضُوا۟ فِی حَدِیثٍ غَیۡرِهِۦۤ إِنَّكُمۡ إِذࣰا مِّثۡلُهُمۡۗ إِنَّ ٱللَّهَ جَامِعُ ٱلۡمُنَـٰفِقِینَ وَٱلۡكَـٰفِرِینَ فِی جَهَنَّمَ جَمِیعًا }

⇘አላህ እንድህ ይላል፦
በእናንተም ላይ በመፀሀፉ ዉስጥ የአላህን አንቀፆች  በርሷ ሲካድበትና በርሷም  ሲላገጥበት በሰማችሁ ግዜ በሌላ ወሬ ዉስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከእነርሱ ጋር አትቀመጡ።ማለትን በእርግጥ አወረደ። እናንተ ያን ግዜ  አምሳያዎቻቸዉ ናችሁኒ።አላህ መናፍቃንን እና ከሐደሐዎችን በሙሉ በገሀነብ ዉስጥ ሰብሳቢ ነዉ ።(አንኒሳዕ፡140)


⇲አላህ በዚህ አንቀፀ ላይ በታምራቶቹ በሚያሾፉት እና በሚያጋልጡት ጋር መቀማመጥና እነርሱን መዉደድ መጥፎ ተግባር ሲሰሊ አይቶ የማይከለክልን ሰዉ  ከእነርሱ ጋር እኩል ወንጀለኛ እና ጥፍተኛ አድርጎ ቆጥሮታል፣እዚት በዱኒያ ላል በአላህ አንቀፀ ለማሾፍና ለማላገጥ እንደተሰበሰቡትም ነገ በመጨረሻ ቀን አላህ በገሀነብ እሳት ዉስጥ ከከሐዲዎች ጋር ይሰበስባቸዋል።

    «ሙናፊቆችን  ማጋለጥ»
   〰〰〰〰〰〰〰〰

☞ የሙናፊቆች ቁጥር መዝገብ ማገላበጥ፤ ያላቸዉ መጥፎ አድራጎትና ተግባር ለሙእሚኖች ማሳወቅና  ሙእሚኖች ከእነዚህ መጥፎ ሰዎች ማስጠንቀቅ፣የእነሱን ድብቅ ሚስጥር እያወጡ ማጋለጥ፤እነርሱን ማዋረድና ማሳፈር አላህ እና መልዕክተኛዉ ﷺየተከተሉት መንገድ ነዉ።

☞አላህ በሱረቱ አት_ተዉባ (አል_ፋድሃ)አዋራጇ በመባል በምትጠራዉ ምእራፍና በሱረቱል በቀራህ ይባስ ብሎም በስማቸዉ ሱረቱል ሙናፊቁን /የመናፍቃኖ ምዕራፍ ተብላ በምትጠራዉ/ምእራፎች ላይ ሾለ እነሱ ምንነት  ማንነት አበጥሮና አንጠርጥሮ በዝርዝሮ ለሙእሚኖች አቅርቧል። መልዕክተኛዉንም ﷺ፦

قال تعالى: { یَـٰۤأَیُّهَا ٱلنَّبِیُّ جَـٰهِدِ ٱلۡكُفَّارَ وَٱلۡمُنَـٰفِقِینَ وَٱغۡلُظۡ عَلَیۡهِمۡۚ وَمَأۡوَىٰهُمۡ جَهَنَّمُۖ وَبِئۡسَ ٱلۡمَصِیرُ }

☞አንተ ነብዩ ሆይ!  ከሐድዎችንና መናፍቃንን ታገል። በእነርሱም ላይ ጨክን። መኖሪያቸዉም ገሀነም ናት ። መመለሻይቱም ከፍች።( አት_ተዉባህ :73) በማለት  እነርሱን መዋጋትና መታገል እንዳለባቸዉ አዟቸዋል።

☞አላህ  በበቀራህ ምእራፍ ላይ ሾለ ሙእሚኖች አራት አያህ/አንቀፀ/ ሾለ ከሀድዎች 2አንቀፀ ሲጠቅስ ስለሙናፊቆች ግን  አስራ ሶስት አያህ ነዉ  ያብራራዉተ ይህም የሆነበት  የእነርሱን ብዛትና መጥፎነት አላህ ለሙእሚኖች ሊያብራራያ ሊተነትን ነዉ።

☞ምክንያቱም ሙናፊቆች በእስልምና ጥላ ሾር ሙስሊም መስለዉ  ተጠልለዉ፣የእስልምናን ባንድራ/አርማ/አዉለብልበዉ፤ በሙስሊም ምሽግ ተከልለዉ፣በሙስሊሞች መሳሪያ እስልምናንና ሙስሊሞችን የሚያጠቁና  የሚዋጉ ሙስሊም ህብረተሰብ በቀላሉ ሊቃወሟቸዉና ሊለያቸዉ የማይችሉ የእስልምናና የሙስሊሞች ጥላት በእስልምና ጉዳይ ስም የእስልምና ገዳይ አረመኔዎች ስለሆኑ ነዉ።

✎ሙስሊም የሆነ ሰዉ ሙናፊቆችን ማድረግ ያለበት ወደፊት ሳይሆን ወደ ኋላ፤ማሳደግ ሳይሆን ማሳነስ፣ማቅረብ ሳይሆኖ ማራቅ፤መዉደድ ሳይሆን መጥላት ፣ማሞገስ ሳይሆን ማዋረድ ነዉ።

✎ምክንያቱም ሙናፊቆች የአላህ እና የመልዕክተኛዉ ጠላቶች የምእምናን ባላጋራዎች ናቸዉ።ሙስሊም የሆነ ሰዉ ለሙናፊቆች ምንም አይነት እርዳታና ትብብር  ሊያደርግ አይፈቀድለትም።

📔ይቀጥላል ኢንሻ አላህ...........

↶↷↶↷↶↷↶↷↶↷↶↷↶
https://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
https://t.me/https_Asselefya1
🛑👉አንድ ሴት ሰለፍይ ወይም ሷሊህ ደግ ናት ማለት ወንጀል የማትሰራ የማትሳሳት ጥቡቅ ናት ማለት አይደለም። ነገር ግን፦

☞ሲያስታውሷት ትነቃለች
☞ሲመክሯት ትቀበላለች
☞ከስህተቷ ትመለሳለች
☞ለወንጀሏ እስቲግፋር ትጠይቃለች።


𝐓𝐞❝ t.me/Sadik_Ibnu_Heyru