💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.49K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
Forwarded from đŸŒAbu Hafsua [አቡ ሐፍሷ] (أبو حفؾ؊ إمام)
አንዳንዴም አንሸወድ
ስማቸው አቡ ፋላና አሰለፊ ኡሙ ፋላና አሰለፍያ የሆነ ፣ፕሮፋይላቸው አጂብ የሚያሰኝ ግን ሰለፍይነታቸው ከፕሮፋይልና ከስም ያልዘለለ ፣ የእውነት ሰለፍይ ያልሆኑ ከሴቱም ከወንዱ እጅግ ነው።

@AbuHafsaYimam
ከጠንካራ ሰዎች ጥንካሬን ትማራለህ!

✍️
:
ምክር ለሴቶቻችን

አንድ ሰው ብቻ የሚመኝሽ ተራ ሴት አትሁኚ!!!

⇝ ተማሪ
⇝ አንብቢ 
⇝ በእውቀትሽም በሳል ሁኚ
⇝ ውበትሽን ጠብቂ
⇝ ጥብቅ እና ጠንቃቃ ሁኚ

ከዛስ...................??.................

↬ በሺዎች የሚቆጠሩ ጎበዞች የሚመኙሽ እንቁ ትሆኛለሽ!!!

t.me/selahudin_Islamic_knowlages
👉ስምህ በታሪክ መዝገብ ውስጥ መስፈር አለመስፈሩ አያስጨንቅህ። እሱ የስኬት መስፈርት አይደለም። ብቻ አንተ መቸም ቢሆን መልካም ደግ ሰው ሁን! ምንዳህን ከሀያሉ ጌታ ታገኘዋለህ ወዳጀ።
ሙሃደራ ሱረቱል ፋቲሃ
አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
✅አዲሥ ሙሓደራ

         →ርዕስ↓


❞مع سورة الفاتحة❝

👉ከሱረቱል ፋቲሃ ጋር

🕌 ወረባቦ ቀበሌ 018 ገላና (ገጠር)

🎙አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም

t.me/abu_reyyis_arreyyis/7124
t.me/abu_reyyis_arreyyis/7124
☑️ «ታጋሽ በመሆንህ የምታተርፈው እንጂ የምትከስረው ምንም ነገር የለም።»

➡️ ታላቅ ብስራት ለታጋሾች

📖{ إنما يوفى الصابرون أجرهم بغير حساب }
➲«ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚስሰጡት ያለ ሂሳብ ነው፡፡»

📖{ اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ }
➲«በመታገስና በሶላት ተረዱ። አላህ ከታጋሾች ጋር ነው።»

📖{ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ }
➲«ታጋሾችን (በጀነት) አበስራቸው።»

📖{ ŮˆŮŽŘ§Ů„Ů„Ů‘ŮŽŮ‡Ů يُحِبُّ الصَّابِرِينَ }
➲«አላህ ታጋሾችን ይወዳል።»

📖{ واصبروا ان الله مع الصابرين }
➲«ትዕግስት አድርጉ። አላህ ከታጋሾች ጋር ነው።»


http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
ኢብኑ ተይሚያ የተውሂድ የሱና ቻናል
☑️ «ታጋሽ በመሆንህ የምታተርፈው እንጂ የምትከስረው ምንም ነገር የለም።» ➡️ ታላቅ ብስራት ለታጋሾች 📖{ إنما يوفى الصابرون أجرهم بغير حساب } ➲«ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚስሰጡት ያለ ሂሳብ ነው፡፡» 📖{ اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ } ➲«በመታገስና በሶላት ተረዱ። አላህ ከታጋሾች ጋር ነው።»…
☑️ እነዚህ አንቀፃች ተግባራዊ ብናደርጋቸው ከብዙ ወንጀሎች በዳንን ነበር።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰

①) እውነተኛ እንሁን ከእውነት ጎን እንቁም።
۞ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَكُونُوا مَعَ الصَّادِقِينَ
➲ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ፡፡

②) ፍትሀዊ እንሁን በነፍሳችን ላይ ቢሆንም እንኳ
۞ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُونُوا قَوَّامِينَ بِالْقِسْطِ شُهَدَاءَ لِلَّهِ وَلَوْ عَلَىٰ أَنفُسِكُمْ أَوِ الْوَالِدَيْنِ وَالْأَقْرَبِينَ
➲ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በነፈሶቻችሁ ወይም በወላጆችና በቅርብ ዘመዶች ላይ ቢኾንም እንኳ በትክክል (በፍትሕ) ቋሚዎች ለአላህ መስካሪዎች ኹኑ፡፡

③) ነገራቶች እንደወረደ ከመቀበል ይልቅ እውነታውን ለማጣራት እንሞክር።
۞ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِن جَاءَكُمْ فَاسِقٌ بِنَبَإٍ فَتَبَيَّنُوا أَن تُصِيبُوا قَوْمًا بِجَهَالَةٍ فَتُصْبِحُوا عَلَىٰ مَا فَعَلْتُمْ نَادِمِينَ
➲ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ኾናችሁ ሕዝቦችን እንዳትጎዱና በሠራችሁት ነገር ላይ ተጸጸቾች እንዳትኾኑ አረጋግጡ፡፡

④) ለሰዎች ያለን ጥላቻ ድምበር እንድናልፍ አያድርገን።
۞…وَلَا يَجْرِمَنَّكُمْ شَنَآنُ قَوْمٍ عَلَىٰ أَلَّا تَعْدِلُوا ۚ اعْدِلُوا هُوَ أَقْرَبُ لِلتَّقْوَىٰ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ
➲ ለሰዎች ያላችሁ ጥላቻ ፍትሀዊ ባለመሆን ላይ አይገፋፋችሁ፡፡ ፍትሀዊ ሁኑ፡፡ እርሱ ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡

⑤) የሰዎችን ነውር ከመከታተልና ከሀሜት እራሳችንን እናርቅ።
۞…وَلَا تَجَسَّسُوا وَلَا يَغْتَب بَّعْضُكُم بَعْضًا ۚ أَيُحِبُّ أَحَدُكُمْ أَن يَأْكُلَ لَحْمَ أَخِيهِ مَيْتًا فَكَرِهْتُمُوهُ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ تَوَّابٌ رَّحِيمٌ
➲ ነውርንም አትከታተሉ፡፡ ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ፡፡ አንደኛችሁ የወንድሙን ስጋ የሞተ ኾኖ ሊበላው ይወዳልን? (መብላቱን) ጠላችሁትም፤ (ሐሜቱንም ጥሉት)፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡

⑥) አጉል ጥርጣሬ እናስወግድ።
۞ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اجْتَنِبُوا كَثِيرًا مِّنَ الظَّنِّ إِنَّ بَعْضَ الظَّنِّ إِثْمٌ
➲ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከጥርጣሬ ብዙውን ራቁ፤ ከጥርጣሬ ከፊሉ ኃጢአት ነውና፡፡

⑦) የምንናገረውና የምንፅፈው ሁሉ በስራ መዝገባችን ላይ እየሰፈረ መሆኑን አንዘንጋ።
۞ مَّا يَلْفِظُ مِن قَوْلٍ إِلَّا لَدَيْهِ رَقِيبٌ عَتِيدٌ
➲ ከቃል ምንም አይናገርም በአጠገቡ ተጠባባቂና ዝግጁ የኾኑ (መላእክት) ያሉበት ቢኾን እንጅ፡፡

⑧) ባልገባን ነገር ላይ ሀሳብ ከመስጠትና ባላየነው ነገር ላይ ከመመስከር እንጠንቀቅ።
۞ وَالَّذِينَ لَا يَشْهَدُونَ الزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا بِاللَّغْوِ مَرُّوا كِرَامًا
➲ እነዚያም እብለትን የማይመሰክሩ፤ በውድቅ ቃልም (ተናጋሪ አጠገብ) ባለፉ ጊዜ የከበሩ ኾነው የሚያልፉት ናቸው፡፡

⑨) ውስጣችን እያወቀ የሰዎችን ስም ለማጥፋት እንዲመቸን ብለን እውነቱን ውሸት ውሸቱን እውነት አድርጎ ከማቅረብ እንጠንቀቅ።
۞ وَلَا تَلْبِسُوا الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُوا الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
➲ እውነቱንም በውሸት አትቀላቅሉ፡፡ እናንተም የምታውቁ ስትሆኑ እውነትን አትደብቁ፡፡

📍ይቀጥላል ኢንሻአላህ

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
☑️ እነዚህ አንቀፃች ተግባራዊ ብናደርጋቸው ከብዙ ወንጀሎች በዳንን ነበር። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ①) እውነተኛ እንሁን ከእውነት ጎን እንቁም። ۞ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَكُونُوا مَعَ الصَّادِقِينَ ➲ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ፡፡ ②) ፍትሀዊ እንሁን በነፍሳችን ላይ ቢሆንም እንኳ ۞ يَا أَيُّهَا…
✅ የነብዩላህ ዩሱፍ ወንድሞች ታሪክ
〰〰〰〰〰♦️♦️〰〰〰〰〰

ነብዩላህ ዩሱፍ ከሌሎች ወንድሞቹ ይልቅ ነብዩላህ ያእቁብ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነበር። ይህንን ሁኔታ እንቅልፍ የነሳቸው ወንድሞቹ በቅናት መንፈስ ተነሳስተው ዩሱፍን ለመግደል አሰቡ። ነገር ግን መገደሉ አላህ አልፈቀደውምና በጉድጓድ ሊጥሉት ወሰኑ። ዩሱፍን ከአባቱ ያእቁብ ለመነጠል ብዙ አሴሩ። በመጨረሻም እናጫውተው እናዝናናው ብለው ከአባቱ ነጥለው የጥፋት መረባቸው ውስጥ አስገቡት። እንዲህም አሉ፦ «ነገ ከእኛ ጋር ላከውና ይደሰት፤ ይጫወትም፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎች ነን፡፡ (ሱረቱ ዩሱፍ - 12)» በዚያ በጨቅላ እድሜው መሸከም ከሚችለው በላይ በደል አሸከሙት። ያደረጉትን ካደረጉ በኋላ አባታቸው ያእቆብን ለማሳመን የውሸት መላ ዘየዱ። ያሳምንልናል ብለው ያሰቡትን ሁሉ አደረጉ። «አባታቸውንም በምሽት እያለቀሱ መጡት፡፡ (ሱረቱ ዩሱፍ - 16)» ይህንን የውሸት ለቅሶ እውነት ለማስመሰል ሌላ ውሸት መፈብረክ ቀጠሉ። «አባታችን ሆይ! እኛ (ለሩጫና ለውርወራ) ልንሽቀዳደም ሄድን፡፡ ዩሱፍንም ዕቃችን ዘንድ ተውነው፡፡ ወዲያውም ተኩላ በላው፡፡ አንተም እውነተኞች ብንሆንም የምታምነን አይደለህም አሉ፡፡ (ሱረቱ ዩሱፍ - 17)» አባታችን ሆይ እውነተኞች ነን እመነን ብለው ድርቅ አሉ። ይህም አልበቃ ብሏቸው ሌላ የውሸት ጥግ ሄዱ። «በቀሚሱም ላይ የውሸትን ደም አመጡ፡፡ (ሱረቱ ዩሱፍ - 18)»።

ይህ ሁሉ ለቅሶ፣ ይህ ሁሉ ውሸት፣ ይህ ሁሉ ስም ማጥፋት ውስጥ የገቡት የፈፀሙትን በደልና ያሉበትን ውሸት እውነት ለማስመሰል ነው። ነገር ግን ውሸት የፈለገ ቢገን፣ ብዙዎችን ቢያሳስትም፣ ለጊዜው እውነት መስሎ ቢታይም መወገዱ አይቀርም። እውነት መቸም ቢሆን ተዳፍኖ አይቀርም አንድ ቀን ፈንቅሎ መውጣቱ አይቀርም። በልም «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡ (ሱረቱ አል-ኢስራእ - 81)»

በዘመናችንም ይህንን የዩሱፍ ወንድሞች ታሪክ የሚያስታውሱ ነገራቶች በብዛት ይከሰታሉ። ተበዳይ እያለ በዳይ የሚጮህበትና በውሸት እምቦ የሰዎችን ልብ ለመስረቅ የሚደረጉ ጥረቶች እጅግ ብዙ ናቸው። የውሸቱን እምባ እውነት ለማስመሰል የሚቀጠፋ ቅጥፈቶችም ይሰማሉ። እውነቱና ውሸቱ እስኪለይ ጊዜ ቢፈጅም አንድ ቀን መታወቁ ግን አይቀርም። ካልሆነም አላህ ሁሉን ያያል። ሁሉንም ይሰማል። የፍርዱ ቀን እያንዳንዱ የእጁን ያገኛል።

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
አንዳዴ አስተዋይ አርቆ አሳቢ መሆን ትልቅነት ነዉ።

✍️
✅🌹

fb ባልኖር ትምህርቶችሽ ባላገኛቸዉ ዛሬ ደረሱኝ አላህ ይጠብቅሽ የኔ እህት🌹
ያለ አቅም መንጠራራት መበጠስ ያመጣል
አቅማችንን እያወቅን ጎበዝ!

✍️
☑️ በሱና ላይ የተመሰረተ በዛውም ላይ የቀጠለ ትዳር ከጅማሬው እስከ ፍፃሜው የተዋበና ያማረ ነው።

📍ኢማሙ አህመድ አላህ ይዘንላቸውና ስለሚስታቸው አባሳ ቢንት አል_ፈድል (እሙ ሷሊህ) ሲናገሩ እንዲህ አሉ።

እሙ ሷሊህ ከኔ ጋር ሰላሳ አመት ኖራለች። በአንዲት ንግግር እንኳ ቢሆን አልተለያየንም። ከዚያም "አላህ ይዘንላትና" በዚህ ሁኔታ ላይ ሆና ሞተች።
📚 [تاريخ بغداد].

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
የትዳርን ጣዕም የሚያውቀው የገባበት ብቻ ነው። በውጭ ሲታይ እና ሲታሰብ ትዳር ያስፈራል። ነገር ግን እውነታው ተቃራኒ ነው።

ትዳር ረፍት ነው።
ትዳር በደስታ የተሞላ ነው።
ትዳር ልጆችን የምናገኝበት ቁልፍ ነው።

አግቡ አግቡ

ላገቡት መልካም ትዳርን እና ሷሊህ ልጆችን ላላገቡት ሷሊህ እንስትን ለሴቶችም ሷሊህ ዘውጅን ይወፍቃቸው።


©ከባለ ትዳሮች ሰፈር የተገኘ¡


https://t.me/https_Asselefya1
Forwarded from đŸ’ŽŘŁŮŘŽŮ’تِي عَيْشِي مَعَ الكِتٰابْ وَالسُّنَّة💎
ማንም ከማንም አይበላለጥም ኢላ ቢተቅዋ
አንች ከማንም መብለጥ ከፈለግሽ አሏህን አጥርተሽ ከማወቅ እና ነብያችን ያሉትን ከመስራት አትዘናጊ አንች ማለት ውድ እንስት ነሽ ኡክቲ ተከብረሽ እምኖሪው ጌታሽ ያዘዘሽን ስታከብሪ እና ወደ ጌታሽ ስትተናነሽ ነው ያንች ተምሳሌቶች እነማን እንዴሆኑ ጠንቅቀሽ ልታቂ ይገባሻል አንች ማለት ውድ የተነጠር ወርቅ ነሽ እህቴ💎

https://t.me/beytbenatasselfyat
👉ኢላሒ ሰትረን‼
➖➖➖➖➖➖

✅ኢብኑ አል-ቀይም "በሆነ ወንጀል ሰውን ያነወረ ሰው ያንን ወንጀል ሳይሰራው አይሞትም" ይላሉ።
መሳደብም ሆነ መሳለቅ መልካም አይደለም። ሰውን መሠተር ነው እንጂ ማዋረድ ትርፍ የለው።

👉ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ደግሞ
"በውሻ ባሾፍ እንኳ ውሻ እንዳልሆን ብዬ እፈራለሁ፡፡"

✅ደጋጎችና ጥንቁቆቹ እንዲህ ናቸው። በሰው ነውር ላይ ሙድ አይዙም፤ አላህ በፈተነው ሰው አያላግጡም፣ በአፈጣጠሩም ሆነ በእንከኑ አያሾፉም፣ ያጠፋውን ቀርበው ይመክሩታል እንጂ አያሙትም፣ አይስቁበትም።
...
✅ሷሊሖቹ ሰዎች የጠፉት እንዴት እንደጠፉ ሳይሆን ነጃ የወጡት እንዴት ነጃ እንደወጡ ነው ጭንቀታቸው። ዛሬ በሰው ወንጀል የምትስቁ ነገስ እናንተ ላለመሥራታችሁ ምን ዋስትና አላችሁ!!
አላህ ይሠትረን።


منقول
https://t.me/https_Asselefya1
⇛ስንት እና ስንት ሴቶች አሉ ከወንዶች በላይ የሆኑ… በ አስተሳሰቧ፣ በ ሀይማኖቷ፣ በስነ_ስርዓቷ

قال الشيخ عبد العزيز بن باز رحمه الله:

" فَكَمْ لِله مِنْ امرأة فوقَ كثيرٍ مِنَ الرجال في عَقلها ، ودِينها ، وضَبْطِها ".

{ مجموع الفتاوى - ٢٩٣/٤ }

الإمام الفوزان - حفظه الله - :

رب بنت صالحة خير من ألف ابن.

درس ليلة ١٩-٣-١٤٤١

@AbuSufiyan_Albenan
⭕️ኢማም ሻፊዕይ እንድህ ይላሉ፦
ﻳﻘﻮﻝ ﺍﻟﺸﺎﻓﻌﻲ :
ﻣﻦ ﻳﻈﻦ ﺁﻧﻪ ﻳﺴﻠﻢ ﻣﻦ ﻛﻶﻡ ﺁﻟﻨﺂﺱ ﻓﻬﻮ ﻣﺠﻨﻮﻥ ﻗﺂﻟﻮﺁ ﻋﻦ ﺁﻟﻠّﻪ : ﺛﺂﻟﺚ ﺛﻶﺛﺔ ! ﻭﻗﺂﻟﻮﺁ ﻋﻦ ﻣﺤﻤﺪ : ﺳﺂﺣﺮ ﻭﻣﺠﻨﻮﻥ ! ﻓﻤﺂ ﻇﻨﻚ ﺑﻤﻦ ﻫﻮ ﺩﻭﻧﻬﻤﺂ ؟


«ከሰወች ንግግር(ወቀሳ) ነፃ እሆናለው ብሎ የሚያስብ ካለ ይህ ሰው እብድ ነው! (ምክኒያቱም) በአላህ ላይ”የአንድ ሶስተኛ ነው” አሉ፤ በነብያችን ሙሀመድ ላይ“ ደጋሚ እና እብድ” ናቸው አሉ። ከነሱ በታች በሆነው ላይ ታድያ(እንዴት ነፃ ይወጣሉ ብለህ) ትጠራጠራለህ!?

➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷
t.me/IbnuTeymyaYesunawAmbesa