💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
#አታውልቂው_ያምርብሻል
ሚያስደስተኝ እኔ ሳይሽ
ተሸፋፍነሽ በኒቃብሽ
በሽተኛን አደናብረሽ
የሱናን ሰው ልቡን ማርከሽ
ረመድ ረመድ ስትይ አንገት ደፍተሽ
እያት እስኪ ተነቅባ
ሃያእ ከላይ ደራርባ
ብለው ሰዎች ሲያወሩ
በውበትሽ ሲፎክሩ
አይቅርብኝ እኔም ብዬ
በተቻለኝ ሞራል የአቅሜን ችዬ
የውበት ጥግ አላብሶሻል
አታውልቂው ያምርብሻል!!
𝑨𝒃𝒖 𝒔𝒐𝒇𝒊𝒚𝒂...✍️

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
የሱና ዑለማዎችን ለሚያከብሩ ብቻ!
~~~~~~~~~~
ኢኽዋንዮችን ተዋቸው። የሱና ዑለማዎችን ማንቋሸሽ የመንሃጃቸው አካል ነው። በሰለፊያ ስም የሚንቀሳቀሱ፣ የኢኽዋንን ጅራት ተከትለው የሚነፍሱ፣ እያንቀላፉ እንደነቁ የሚያስቡ፣ ከጊዜ ጊዜ ቁልቁል እየተጓዙ ያሉ ሳይሞቅ ፈላዎችን እያየን ነው። "ሰለፍዮች ነን" ይላሉ። ለሰለፊያ መንሃጅ ግን ክብር የላቸውም። መመሪያውን አይጠብቁም። ከወሰኑ አይቆሙም። ልካቸውን አያውቁም። ድመት ሳያክሉ እንደ ነብር ይሰራቸዋል። ዑለማዎች ከቆሙበት አይቆሙም። አሁንማ ይባስ ብለው ጭራሽ ዑለማዎቹንም መዳፈር ጀምረዋል። ለኢኽዋን አጋፋሪዎች፣ ለአሕባሽ ዐቂዳ አራማጆች ሙገሳ የሚሰፍረው ብእራቸው ለሱና ሰዎች ግን እሾህ እየሆነ ነው። ሒክማቸው፣ ሪፍቃቸው፣ ዐድላቸው ለቢድዐ አንጃዎች ነው። ለኢኽዋኖች ከሚሰፍሩት ሪፍቅና ዐድል እሩቡን ለሰለፍዮች አይሰጡም።
ይሄ የሱና ዑለማዎችን ክብር መዳፈር፣ በነገር መውጋት፣ ባደባባይ በክፉ እየነካኩ ክብራቸውን ማቃለል፣ በዚህ አይነት መሰሪ አካሄድ ከቢድዐ አንጃዎች ጋር መጋፋት ጀግንነት ሳይሆን አጉል ጀብደኝነት ነው። ሰውዬ! የምትጎዳው እነሱን ሳይሆን እራስህን ነው። ታላቁ ዓሊም አቡ ሓቲም አራ፞ዚይ ረሒመሁላ፞ህ እንዲህ ይላሉ:–
علامةُ أهل البدع الوقيعةُ في أهل الأثر
"የቢድዐ ሰዎች መታወቂያ የቀደምቶችን ፈለግ የሚከተሉ ሰዎችን ማንቋሸሽ ነው።" [ዐቂደቱ ሰ፞ለፍ: 105]

ሰለፊይነት በተግባር እንጂ በምላስ አይደለም። ኢኽዋንን በመተቸታቸውና ኸዋሪጅን በማውገዛቸው ምክንያት ዑለማዎች ላይ የሚሳለቅ ሰው ፈፅሞ የሱና፞ ሰው ሊሆን አይችልም። የሱና፞ ሰው ማለት ታላቁ ሰለፍ አቡበክር ብኑ ዐያ፞ሽ ረሒመሁላ፞ህ እንዳሉት "ስሜቶች (ቢድዐዎች) በሚወሱ በሚወገዙ ጊዜ ለየትኛውም ወግኖ የማይቆጣ ነው። [አሸሪዐ ሊልአጁሪ፞]
ዛሬ የኢኽዋን ቫይረስ ተንሰራፍቷልና ኢኽዋን ተነካ ብሎ የሚነጫነጭ፣ ኸዋሪጅ ተወገዘ ብሎ ፀጉሩን የሚነጭ ሰው ማየት የሚደንቅ አይደለም። የሚደንቀው አንድ ሰው ሰለፊ ነኝ ካለ በኋላ እነዚህ የጥፋት አንጃዎች ስለተነኩ ተበሳጭቶ የሰለፊያ ዑለማዎችን ባደባባይ ማጠልሸቱ፣ በነገር መውጋቱ ነው።
ለማንኛውም ለዑለማእ ክብር ያላቸው ሰዎች ይገሰፁበት ዘንድ ተከታዩን የሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊን ሐፊዞሁላ፞ህ ንግግር አያይዣለሁ።

✍ኢብኑ ሙነወር
🖊نصيــحـة الشيـــخ صــالح الفــوزان -حفظه اللّه- للمـرأة السلفيّـة

🌷احرصي على تنظيم وقتك حتى يكون عملك متعة

🌷واجعلي البيت دائمًا كالروضة نظافة وترتيبًا
فالبيت دليل على صاحبته

🌷النظافة والترتيب يكون البيت بأجمل صورة

🌷ولو كان الأثاث متواضعًا والعكس بالعكس .



📜[دور المرأة في تربية الأسرة].


https://t.me/g4448
ኢኽላስ እና ሙታበዓ ስራ ተቀባይነት እንዲኖረው መስፈርቶች ናቸው
አንገብጋቢነት
በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን
አዲስ ሙሐደራ

ሙሐደራ ቁ·120
#ኢኽላስ እና ሙታበዓ ስራ ተቀባይነት እንዲኖረዉ መስፈርት ናቸዉ

🔶 በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በቡታጅራ ከተማ በቆዳና ሌጦ መስጅድ የተደረገ ሙሐደራ።

🎙 በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
"የውሻ ጩኸት ደመናን አይጎዳም!"
~~~~~~~~~~
በነብያችን ﷺ ላይ የሚሳለቅ እራሱን እንጂ እሳቸውን ምንም ሊያደርጋቸው አይችልም። የላካቸው አምላክ "መወሳትህን/ዝናህን ከፍ አደረግንልህ" ብሏቸዋል። ይሄው የዝናቸው ከፍ ማለትም ነው ዛሬ በርካታ ውሾችን እያስጮኻቸው ያለው። ትላንትም የዛሬዎቹ ውሾች አያቶች የመልእክተኛውን ክብር ሊያንቋሽሹ ሞክረው ነበር። አላህ ግን እራሱ ለመልእክተኛው ﷺ ተከላካይ ጠበቃ ይሆንና መልእክተኛው ግን ነገሩን ንቀው እንዲተውት እንዲህ ይጠቁማቸዋል፡-

(فَٱصۡدَعۡ بِمَا تُؤۡمَرُ وَأَعۡرِضۡ عَنِ ٱلۡمُشۡرِكِینَ ۝ إِنَّا كَفَیۡنَـٰكَ ٱلۡمُسۡتَهۡزِءِینَ ۝ ٱلَّذِینَ یَجۡعَلُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَـٰهًا ءَاخَرَۚ فَسَوۡفَ یَعۡلَمُونَ ۝ وَلَقَدۡ نَعۡلَمُ أَنَّكَ یَضِیقُ صَدۡرُكَ بِمَا یَقُولُونَ ۝ فَسَبِّحۡ بِحَمۡدِ رَبِّكَ وَكُن مِّنَ ٱلسَّـٰجِدِینَ ۝ وَٱعۡبُدۡ رَبَّكَ حَتَّىٰ یَأۡتِیَكَ ٱلۡیَقِینُ)

"የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለፅ፤ አጋሪዎችንም ተዋቸው። እኛ ተሳላቂዎችን ሁሉ በቅተነሃል። (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፤ በርግጥም (የስራቸውን ዋጋ) ወደፊት ያውቃሉ። አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መሆኑን በርግጥም እናውቃለን። ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው፤ ከሰጋጆቹም ሁን። እውነቱም (ሞት) እስከሚመጣህ ድረስ ጌታህን አምልክ።" [አልሒጅር 94-99]

ስለዚህ ተሳላቂዎቹ ውሾች ቢሳለቁም የነብያችን ﷺ ዝና የበለጠ ይገናል። የውሾቹ ስም ይከስማል። ውሻ ደግሞ ምን ታሪክ አለውና?!! እስኪ የነብያችንና የትላንት ጠላቶቻቸውን ዝና አወዳድሩ። ሲጀመር መወዳደር ይችላሉ? በጭራሽ!! “የሰማይና የመሬት ያክል ነው” ብንል እንኳ በትክክል አይገልፀውም።
ግን የነብያችንን ﷺ ክብር ለማጉደፍ ተፍ ተፍ የሚሉ ሰዎች አላማቸው ምን ይሆን? መልሱ ግልፅ ነው።
1. አንዳንዶቹ በነብዩ ﷺ እውቅና ሂሳብ እውቅና መሸመት የሚፈልጉ ናቸው። “አንዳንዶች ታዋቂዎችን በመተቸት ታዋቂ መሆን ይፈልጋሉ” ሲባል አልሰማችሁም?
2. ሌሎቹ ደግሞ የኢስላም ውበቱና ሁለንተናዊነቱ የሚያስቀናቸው፤ ከፍተኛ ግስጋሴው የሚያስበረግጋቸው ናቸው። ስለሆነም ሙሐመድን ﷺ ሲያንቋሽሹ የኢስላም ውበቱ የሚደበዝዝ፣ ግስጋሴው የሚገታ ይመስላቸዋል። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው። ኢስላም ዛሬ ጠላቶቹን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ በከፍተኛ ፍጥነት እየገሰገሰ ነው። ስለዚህ ውሾቹ አመል ሆኖባቸው ይጮሃሉ እንጂ የኢስላምን ግስጋሴ ሊገቱት አይችሉም!! ውሾቹ ይጮሃሉ፣ ዋው! ዋው!....። ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል። ውሻ ግመልን ማስቆም ከቻለች ትሞክር።
ባይሆን ከኛ አንድ ነገር ይጠበቃል። ከሃዲዎችን የነብያችንን ﷺ ስም ለመዘለፍ ያበቃቸው ለነብዩ አስተምሮ ያላቸው ጥላቻ መሆኑ ይታወቃል። አዎ የነቢዩ ﷺ ሱና እጅጉን ያስቆጫቸዋል!! እውነቱ ይህ ከሆነ ከሃዲዎችን የበለጠ ለማስቆጨት የሚጓጓ፤ ለሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ወዳጅነቱን ማንፀባረቅ የሚፈልግ፣ ብሎም የአላህን ውዴታ ማትረፍ የሚሻ የበለጠ ወደ መልእክተኛው ሱና ይቅረብ፤ ትእዛዛቸውንም ይፈፅም፤ ከከለከሉትም ይራቅ። ይህን የሚያደርግ ጠላቱን የበለጠ ያስቆጫል። የአላህንና የመልክተኛውንም ﷺ ውዴታ ያፍሳል። ያ ሱብሓላህ!!! የአላህና የመልክተኛውን ውዴታ ያገኘ ምን የቀረበት ነገር አለ?!!!! ያ ወሃ፞ቡ አንተ ወፍቀን!!! ኣሚን

(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 08/2005)

የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Audio
♻️🔺የትዳር አስፈላጊነት🔺♻️

🔺ላጤነት በእስልምና ቦታ የለውም


🎙አቡ አብደላህ ኢብኑ ኸይሩ
እናታችን ዓኢሻ (ረድየላሁ አንሀ) እንዲህ ትለናለች፦

➢ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተቀበሩት በቤታቸው ውስጥ ነበር እንዲሁም አባቷም አቡበከር (ረድየላሁ አንሁ) ከእርሳቸው ጋር አብሮ ነበር የተቀበረው። ማለትም በእናታችን ዓኢሻ ቤት ማለት ነው።

➢« ሁለቱም ሞተው ከተቀበሩ በኋላ እዛ ቤት እገባ ነበር ስገባም ሂጃቤን ባልተሟላ መልኩ ሳልለብስ ነበር
«እዚህ ቤት ውስጥ የተቀበሩት አባቴና ባሌ ናቸው ሌላ ሰው የለም» እልም ነበር።

➢በአላህ ይሁንብኝ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ አብሯቸው ከነሱ ጋር ከተቀበረ በኋላ ግን እዛ ቦታ ላይ አንድም ቀን ሂጃቤን በትክክል ለብሼ (ፊቴን ተሸፍኜ) ቢሆን እንጂ ገብቼ አላውቅም። ምክንያቱም ዑመር ረድየላሁ አንሁ (አጅነብይ በመሆኑ) ሀያዕ አደርጋለው ። »

(አህመድ ዘግበውታል )

💎https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
በአላህ ዲን ላይ መጽናት
በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን
👆👆👆
#በአላህ ዲን ላይ መጽናት

🔶በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ ቅበት ከተማ በኑር መስጅድ የተደረገ ሙሐደራ።

🎙 በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
ﻭﻗﺎﻝ ﺍﻟﻔﻀﻴﻞ ﺑﻦ ﻋﻴﺎﺽ ﻣﻦ
ﻋﻈﻢ ﺻﺎﺣﺐ ﺑﺪﻋﺔ ﻓﻘﺪ ﺃﻋﺎﻥ
ﻋﻠﻰ ﻫﺪﻡ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﻭﻣﻦ ﺗﺒﺴﻢ
ﻓﻲ ﻭﺟﻪ ﻣﺒﺘﺪﻉ ﻓﻘﺪ ﺍﺳﺘﺨﻒ
ﺑﻤﺎ ﺃﻧﺰﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﺰ ﻭ ﺟﻞ ﻋﻠﻰ
ﻣﺤﻤﺪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭ ﺳﻠﻢ
ﻭﻣﻦ ﺯﻭﺝ ﻛﺮﻳﻤﺘﻪ ﻣﺒﺘﺪﻉ ﻓﻘﺪ
ﻗﻄﻊ ﺭﺣﻤﻬﺎ ﻭﻣﻦ ﺗﺒﻊ ﺟﻨﺎﺯﺓ
ﻣﺒﺘﺪﻉ ﻟﻢ ﻳﺰﻝ ﻓﻲ ﺳﺨﻂ ﺍﻟﻠﻪ
ﺣﺘﻰ ﻳﺮﺟﻊ
ፉዶይል ኢብኑዒያድ አሏህ ይዘንላቸው እንዲህ ይላሉ
የቢድአ ባለቤትን ያከበረ እስልምናን በማፍረስ ላይ ተባብሯል ። ሙብተዲእ ፊት የሳቀ አሏህ በነብዩ ያወረደውን ቁርአንን አቃሏል ። ጥሩ ልጁን ለሙብተዲእ የዳረ ዝምድናዋን ቆርጧል ። የሙብተዲእን ጀናዛ የተከተለ እስከሚመለስ ድረስ በአሏህ ቁጣ ውስጥ ነው

ምንጭ_ሸርሁ_ሱና_ኢማም_በርበሃሪ_139
ከኢኽወኖች ጋር መተሻሸት መጨረሻው የሰለፎችን ግንዛቤ ወደ ጎን በማድረግ እንደፖለቲከኞች በስሜት ሰክሮ የሚናገሩትን አለማወቅ ያደርሳል።

በሰሞኑ ከኢብኑ መስኡድ ሴንተር ደጋፊዎች የታዘብነው ይህንኑ ነው። አንዳንዶች ታላላቅ ስመጥር አሊሞችን አሁን ላይ ካሉበት የስሜት ሞቅታ ጋር ስላልተጣጣመላቸው ሲተቿቸው እየየን ነው። አንዳንዶች ወረድ ብለው ከቀርደዊ እና ከዶ/ር ጀይላን ትምህርት እንወስዳለን የሚሉም አይተናል። አንዳንዶች የኢኽዋን መንሃጅ ትክክለኛ ነው ብለው በብዕራቸው የሚሰብኩ ሰዎችን መፅሀፍ እየገዙ ለሰው ሲሰጡም አይተናል።
ሰው መደገፍ የመጨረሻው ግብ አብሮ ቁልቁል መዝቀጥ ይለሀል እንደዚህ ነው።




ለዚህም ነው ሰለፎቻችን ከቢድዓ ሰዎች ጋር አትቀማመጡ እያሉ አበክረው የመከሩን።

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Audio
➚➶➚ የልዩነት ትልቁ መፍትሔ

በኮምቦልቻ ከተማ አንሷር
መስጂድ እየተሰጠ ከሚገኘው
ኮርስ የተቀነጨበ


ኮርሱ የሚቀጥል በመሆኑ በአካባቢው ያላችሁ ሰዎች ትጠቀሙበት ዘንድ እመክራለሁ

🎙 በሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን አቡ ጦልሃ ሀፊዘሁሏህ
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Audio
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤

"ወሏሂ ይቅርብህ"

በወንድማችሁ አቡ ሳራህ
===============>
➷➘➷➘
ወንድሜ አቡ ሳራህ ኸድር ከነዚህ ሰዎች ጋር በኮሚቴነት ሰርቷል። ከማንም በላይ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። እንቅስቃሴዎቻቸውን ሁሉ ከሁላችንም በላይ ያውቃል።

በመሆኑም ያንን ለሴረኞች ጠበቃ የሆነውን ሰው አድርሱለት
"ወላሂ ይቅርበት"
"ወላሂ ይቅርበት"
"ወላሂ ይቅርበት"
قال تعلى: ولا تكونوا من المشركين ➊➌ من الذين فرقو دينهم وكانوا شيعا كل حزب بمالديحم فرحون ➋➌

وقال صلى الله عليه وسلم: من مات وهو يدعو من دون الله ندا دحل النار.
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
ሙሓደራ 095 የ አላሀ እዝነት ለ ሙእሚኖች እጅግ ቅርብ ነው.mp3
Ustaz Kedir Ahmed
ሙሓደራ 095

በመርከዝ ኢብኑ አባስ በዛሬው እለት የተደረገ ሙሓደራ

የአሏህ እዝነት ለሙዕሚኖች እጅግ ቅርብ ነው

🎙በኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል_ከሚሴ (ሐፊዘሁሏህ ተዓላ)

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
➪ሴት ልጅ የራሷን ውበትና የቤቷን ጽዳት ስትጠብቅ ባለቤቷን ከማስደሰትም አልፎ ትዳራቸው የስኬት ቁልፍ ይሆናል !!!
(233 عشر النصحة النساء)
Forwarded from Deleted Account
የተጠው'ዉዕ ሶላት ትርጓሜ
የተጠው’ዉዕ ሶላት
ግዴታ ያለሆነና መስገዱ የተደነገገ ሶላት ነው፡፡

የተጠው’ዉዕ ሶላት ትሩፋት
1 - የተጠው’ዉዕ ሶላት አላህ አገልጋይ ባሪያውን እንዲወደው ምክንያት ይሆናል፡፡ በሐዲስ አልቁድሲ እንደተመለከተው አላህ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ባሪያዬ እስክወደው ድረስ በነዋፍል (ግዴታ ያልሆኑ ተጨማሪ ዕባዳዎች በማከናወን) ወደኔ መቅረቡን ይቀጥላል፤ከወደድኩት ደግሞ የሚያይበት ማያው፣የሚሰማበት መስሚያው፣የሚሰነዝርበት እጅ እና የሚጓዝበት እግር እሆንለታለሁ፡፡ ከለመነኝ በእርግጥ እሰጠዋለሁ፤ከኔ መጠጊያና መጠበቂያ ከፈለገም በእርግጥ እጠብቀዋለሁ፡፡›› [በቡኻሪ የተዘገበ]

2 - የተጠው’ዉዕ ሶላት በግዴታ ሶላቶች ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ጉድለቶችን ያካክሳል፡፡ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በትንሣኤ ቀን ከሥራዎቻቸው ውስጥ ሰዎች በመጀመሪያ የሚጠየቁበት ሶላት ነው፡፡ ጌታችን እርሱ የበለጠውን የሚያውቅ እየሆነ ለመላእኮች እንዲህ ይላል፡- ‹የባሪያዬን ሶላት አሟልቶት ወይም አጉድሎ ሰግዶ እንደሆነ እዩለት› ይላል፡፡ የተሟላ ከሆነ (ምንዳው) የተሟላ ሆኖ ይጻፍለታል፡፡ የጎደለ ነገር ካለ ደግሞ ባሪያዬ የተጠው’ዉዕ ሶላት እንዳለው እዩለትና ተጠው’ዉዕ ካለው ‹‹ለባሪያዬ የግዴታ ሶላቱን ከተጠው’ዉዑ አሟሉለት› ይላል፡፡ የተቀሩት ሥራዎችም በዚሁ ዓይነት ይወሰዳሉ፡፡›› [በአቡ ዳዉድ የተዘገበ]

3 - የተጠው’ዉዕ ሶላትን እቤት መስገድ ተመራጭ ነው

የጀማዓ ሶላት የተደነገገለት እንደ ተራዊሕ ያለው ሲቀር፣የተጠው’ዉዕ ሶላትን ከመስጊድ ይልቅ እቤት መስገድ ብልጫ አለው፡፡ ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹ከግዴታ ሶላት በስተቀር ያንድ ሰው በላጩ ሶላት እቤቱ የሚሰግደው ነው፡፡›› [በቡኻሪ የተዘገበ] ብለዋል፡፡

የተጠው’ዉዕ ሶላት ዓይነቶች
የተጠው’ዉዕ ሶላት ብዙ ዓይነቶች ያሉት ሲሆን ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው ፡-

አንደኛ- የግዴታ ሶላት ቀዳሚና ተከታይ ሱንናዎች (ረዋትብ) [ረዋትብ (ነጠላው ራትብ) ቋሚና የጸና ነገር ማለት ነው፡፡ ]
የፈርድ ሶላቶችን የሚከተሉ ረዋትብ ሲሆኑ የጸኑ ሱንናዎች ናቸው፡፡

የረዋትብ ሱንና በአጠቃላይ አስር ወይም አስራ ሁለት ረክዓዎች ናቸው፡፡ እነሱም ፡-

- ከፈጅር ሶላት በፊት ሁለት ረክዓ፤

- ሁለት ወይም አራት ረክዓ ከዙህር በፊትና ሁለት ረክዓ ከዙህር በኋላ፤

- ሁለት ረክዓ ከመግሪብ በኋላ፤

- ሁለት ረክዓ ከዕሻእ በኋላ ናቸው፡፡ እብን ዑመር ባስተላለፉት መሰረት፡- ‹‹ከነቢዩ ﷺ የያዝኩት አስር ረክዓዎችን ነው፡፡ ሁለት ረክዓ ከዙህር በፊት፣ሁለት ረክዓ ከዙህር በኋላ፣ሁለት ረክዓ ከመግሪብ በኋላ በቤታቸው፣ሁለት ረክዓ ከዕሻእ በኋላ በቤታቸውና ከሱብሕ ሶላት በፊት ሁለት ረክዓ ናቸው፡፡›› [በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ] ብለዋል፡፡

ከዙህር በፊት አራት ረክዓ ከማለታቸው ውጭ ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ዘገባ ከዓእሻ (ረዐ) ተላልፏል፡፡ [በሙስሊም የተዘገበ]

ቀዳማይ ሱንና  የፈርድ ሶላት ደህራይ ሱንና
ሁለት ረክዓ የሱብሕ ሶላት -------
አራት ረክዓ የዙህር ሶላት ሁለት ረክዓ
------- የዐስር ሶላት -------
------- የመግሪብ ሶላት ሁለት ረክዓ
------- የዕሻእ ሶላት ሁለት ረክዓ
ከረዋትብ ሱንናዎች ሁሉ በላጩና ነቢዩ ﷺ ከጉዞ ውጭና ተጓዥም ሆነው አዘውትረው የሰገዱት ሁለቱ የሱብሕ ቀዳሚ ሱንና ሶላት ነው፡፡ ዓእሻ (ረዐ) ባስተላለፉት መሰረት ፡- ‹‹ነቢዩ ﷺ ከነዋፍል ውስጥ ከሁለቱ የፈጅር ረክዓዎች ይበልጥ አጥብቀው ይፈጽሙት የነበረ ሌላ ምንም አልነበረም፡፡›› [በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ] ብለዋል፡፡

ዋጅቦቹን ካለማጓደል ጋር ረክዓዎቹን ቀለል አድርጎ መስገድ ሱንና ነው፡፡

ዓእሻ (ረዐ) ባስተላለፉት መሰረት፡- ‹‹የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሁለቱን የፈጅር ሱንና ረክዓዎች ከሱብሕ ሶላት በፊት ሰገዱና ፋቲሓን ቀርተውበታል ወይ? ብዬ እስከምጠራጠር ድረስ ያሳጥሩ ነበር፡፡›› [በቡኻሪና የተዘገበ] ብለዋል፡፡

የፈጅርን ሱንና ካመለጠ ሰግዶ መተካት የተፈቀደ ነው፡፡
1 - ከሱብሕ ሶላት በኋላ፤ቀይስ ብን ዐምር ባስተላለፉት መሰረት የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከሱብሕ ሶላት በኋላ የሚሰግድ ሰው አይተው፡- ‹‹የሱብሕ ሶላት ሁለት ረክዓ ነው›› [በአቡ ዳዉድ የተዘገበ] ሲሉት ፡- ‹‹ከበፊቱ ያለውን ሁለት ረክዓ አልሰገድኩምና ነው አሁን የሰገድኳቸው›› አላቸው፡፡ የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዝምታ አለፉት ብለዋል፡፡

2 - ጸሐይ ከወጣች በኋላ፤ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹የፈጅርን ሁለት ረክዓዎች ያልሰገደ ሰው ጸሐይ ከወጣች በኋላ ይስገዳቸው፡፡›› [በትርምዚ የተዘገበ] ብለዋልና፡፡

ጠቃሚ ነጥቦች
- ከዙህር በፊት አራት ረክዓ መስገድ ያለው ትሩፋት በሐዲስ ተረጋግጧል፡፡ ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹ከዙህር በፊት አራት፣ከዙህር በኋላም አራት የሰገደን ሰው አላህ (ገላውን) በእሳት ላይ እርም አድርጓል፡፡›› [በአቡ ዳዉድ የተዘገበ] ብለዋል፡፡

- ሙአክ’ከድ (የጸኑ) ካልሆኑ የተወደዱ (ሙስተሐብ) ሱንናዎች መካከል ከዐስር በፊት አራት ረክዓዎችን መስገድ አንዱ ነው፡፡ ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹ከዙህር በፊት አራት፣ከዙህር በኋላም አራት የሰገደን ሰው አላህ (ገላውን) በእሳት ላይ እርም አድርጓል፡፡›› [በአቡ ዳዉድ የተዘገበ] ብለዋልና፡፡

- ከዐስር፣ከመግሪብና ከዕሻእ ሶላት በፊት ሱንናነቱ ያልጸና ሶላት መስገድ ተንግጓል፡፡ ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹በየሁለቱ አዛኖች መካከል ሶላት አለ - ሦስት ጊዜ ደጋግመው በሦስተኛው ላይ - ለፈለገ ሰው፡፡›› [በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ] ብለዋል፡፡ ሁለት አዛኖች ማለት በየአዛኑና እቃማ መካከል ማለት ነው፡፡

- አንድ ሰው በእንቅልፍ ወይም በመርሳት ምክንት ያመለጠውን ሶላት፣መስገድ በተጠላበት ወቅትም ቢሆን ሰግዶ መተካት የተፈቀደ ነው፡፡ ነቢዩ ﷺ የዙህርን ደህራይ ሱንና ሳይሰግዱ ቀርተው ከዐስር ሶላት በኋላ መስገዳቸው ተረጋግጧል፡፡

ሁለተኛ- የውትር ሶላት
የውትር ድንጋጌና ትሩፋቱ
ውትር የጠበቀ ጽኑ ሱንና ነው፡፡ ነቢዩ ﷺ ፡- ‹‹አላህ ውትር (አንድ) ነው፤ውትርን (ኢተጋማሽን) ይወዳልና የቁርኣን ባለቤቶች ሆይ! ውትርን ስገዱ፡፡›› [በአቡ ዳዉድ የተዘገበ] ብለዋል፡፡ ነቢዩ ﷺ በሐዷርም ሆነ በሰፈር (እቤት እያሉም ሆነ በመንገደኝነት ጉዞ ላይ እያሉ) የውትር ሶላትን ተጠባብቀው ይሰግዱ ነበር፡፡

የውትር ሶላት አሰጋገድ
1 - የውትር ሶላት አነስተኛ ረክዓ አንድ ሲሆን ከፍተኛው ቁጥር አስራ አንድ ወይም አስራ ሦስት ረክዓ ነው፡፡ የሚሰገደው በሁለት-ሁለት ረክዓ ሆኖ በማጠቃለያው አንድ ረክዓ ብቻ ይሰገዳል፡፡

2 - ዝቅተኛው የምሉእነት ቁጥሩ ሦስት ረክዓ ሲሆን፣ሁለት ረክዓ ተሰግዶ በሰላምታ ካበቃ በኋላ አንድ ነጠላ ረክዓ ይሰገዳል፡፡ ሦስቱንም አገናኝቶ በአንድ ተሸሁድ ብቻ መስገድም ይቻላል፡፡

በመጀመሪያው ረክዓ ከፋቲሓ በኋላ ሱረቱል አዕላን፣ በሁለተኛው ሱረቱል ካፍሩንን፣በሦስተኛው ሱረቱል እኽላስን መቅራት ሱንና ነው፡፡

ኡበይይ ብን ከዕብ ባስተላለፉት መሰረት ፡- ‹‹የአላህ መልእክተኛ ﷺ በውትር የመጀመሪያው ረክዓ ‹ሰብ’ብሕ እስመ ረብብከል አዕላ›፣በሁለተኛው ‹ቁል ያ አይ’ዩሀል ካፍሩን››፣በሦስተኛው ‹ቁል ሁወል’ሏሁ አሐድ› ይቀሩ ነበር፡፡›› [በነሳኢ የተዘገበ] ብለዋል፡፡

የውትር ሶላት ወቅት
ከዕሻእ ሶላት በኋላ እስከ ጎሕ መቅደድ ድረስ ነው፡፡ በሌሊቱ የመጨረሻ ሲሶ መስገዱ በላጭ ነው፡፡ ከጃቢር በተላለፈው ሐዲስ ነቢዩ ﷺ ‹‹በሌሊቱ መጨረሻ ላይ አልነቃም ብሎ የፈራ ሰው ውትርን በሌሊቱ መጀመሪያ ላይ ይስገድ፡፡›› [በሙስሊም የተዘገበ]
🔸ሸይኽ ኢብን ባዝ ተጠየቁ :- ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ በመፍራት ነው
መልስ፡
"አዎን! ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ እንዲነቃ ለማድረግ ነው" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ ነበር
#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን ያዝከው "አለው
#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ
#የሚቀራው ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን ስላላወቀ ነው" አለው
#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው(እንዲያነቃው)"
#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ ረሂምሁሏህ እንዲህ አሉ ፡
"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ አይደፋም ምክኛቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች ምናልባትም በጂኖች አለም ወይም በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።ስለዚህ አንድ ሰው የሞቀን ውሃ መድፋት ከፈለገ በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር እስኪሆን ያብርደውከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ከፈለገ መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ.
፟፟======================
#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች በዚህ ሰበብ ችግር ውስጥ ይገባሉ ፓስታ የቀቀሉበትን ውሃ አውጥተው በመድፋት ስለዚህ አድርሱላቸው!
..🖋Bin Muhammed
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w