💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ" ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ➧ክፍል ስምንት ➠ቁርኣን የአላህን ስሞች እና መገለጫዎች ከማውሳት ያገለለ አይደለም! ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➠አላህ ለእርሱ ከጣዖቶች አምሳያ ወይም ቢጤ ከማድረግ ከልክሎናል፡፡ ምክንያቱም አላህ አንድም እርሱን የሚመስል የለውም፡፡ ለእርሱም ተጋሪ ፣ ለእርሱ አቻ የለውም፡፡ አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ጌታ…
➲ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ"
➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯

➳ክፍል ዘጠኝ

➧በሌሎች የዲን መሰረቶች ማመን
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➠በሌሎች የዲን መሰረቶች ማመን፡ በመላኢካዎች ፣ በመጽሐፎች በመልእክተኞች ፣ በመጨረሻው ቀን ፣ መልካምም ይሁን መጥፎ በአላህ ውሳኔ የሚከናወን መሆኑን ማመን ናቸው
፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ በአላህ የማመን ተከታዮች ወይም በአላህ የማመን ቅርንጫፎች ናቸው፡፡ ምክንያቱም የመላኢካዎችን መኖር የነገረን አላህ ነው፡፡

➻ያለፉ የሩቅ ሚስጢሮችን ለምሳሌ፡ የመልእክተኞችን መላክ ፣ስለመጨረሻው ቀን እና በእርሱ ውስጥ የሚሆነውን ሁሉ የነገረን አላህ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ማመን በእኛ ላይ ግዴታ ነው
፡፡

➠አብዛኛው በሩቅ ሚስጢር ማመን
በሚለው የሚካተት ነው፡፡


➸እኛ በአላህ እናምናለን በመላኢካዎች እናምናለን ፤ ይህ በሩቅ ሚስጢር
ከማመን ውስጥ ትልቁ ነው፡፡

➸ልክ እንደዚሁ ባናያቸው እንኳ በመልክተኞች እናምናለን ፤ ነገር ግን
የምናምነው አላህ አብሳሪ እና አስጠንቃቂ መልእክተኞችን ፤ የመጀመሪያው ኑህ የመጨረሻው ሙሀመድ መሆናቸውን ስለነገረን ነው፡፡

➸ባናያቸው እንኳ አላህ እና ረሡል صلى الله عليه وسلم ስለነገሩን በመላኢካዎች እናምናለን፡፡

➸አሁን ተከስቶ ባናገኘው እንኳ አላህና ረሡል صلى الله عليه وسلم ስለመጨረሻው ቀን ስለነገሩን በመጨረሻው ቀን እናምናለን፡፡ ይህ ትክክለኛው እምነት ነው፡፡


➧በቀደር ማመን
➫➫➫➫➫➫

➤በቀደር የማመን ደረጃዎች መልካምም ይሁን መጥፎ በአላህ ውሳኔ የሚከናወን መሆኑን እናምናለን፡፡ በቀደር ወይም በአላህ ውሳኔ ማመን የራሱ የሆኑ አራት ደረጃዎች አሉት፡-

➻የመጀመሪያው ደረጃ፡ ከዚህ በፊት የሆነውንም ይሁን ለወደፊት የሚሆነውን አላህ አውቆታል ፤ ያውቀዋል ብሎ ማመን ነው፡፡ በምድርም ይሁን በሰማይ ፤ ያለፉትም ይሁን የወደፊት ስውር ሚስጢሮች ከአላህ አይደበቁም። በእውቀት ሁሉም ነገር ከአላህ ዘንድ እኩል ነው፡፡

➻ሁለተኛው ደረጃ፡ ውሳኔው በሙሉ “ለውሀል መህፉዝ” (ጥብቅ በሆነው ሰሌዳ) ላይ ጽፎታል ብሎ ማመን ነው፡፡
ረሡል صلى الله عليه وسلم በሐዲሳቸው የሚከተለውን ተናግረዋል፡-

"أول ما خلق الله القلم، قال له: اكتب، قال: ما أكتب؟ قال: اكتب ما هو كائن
إلى يوم القيامة"
➧አላህ ከፈጠረው የመጀመሪያው ቀለም ነው ፤ “ጻፍ” አለው ፤ “ምን ልጻፍ?” አለ ፤
“እስከትንሳኤ ቀን የሚሆነውን ጻፍ” አለው፡፡” አህመድ፡ ቲርሚዚይ፡አቡዳውድ፡ ሐዲሱን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል ሶሂህ አቡዳውድ፡


➠ማንኛውም በዚህ ዓለም የሚከናወኑ ነገሮችን ሁሉ አላህ አውቆታል ፤በለውሀል
መህፉዝ
ውስጥ ጽፎታል ብለን እናምናለንን፡

➨አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯ

◆مَا أَصَابَ مِن مُّصِيبَةٍ فِي الْأَرْضِ وَلَا فِي أَنفُسِكُمْ إِلَّا فِي كِتَابٍ مِّن قَبْلِ أَن نَّبْرَأَهَا ۚ إِنَّ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ

➾በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ (ማንንም) አትነካም ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትሆን እንጅ፡፡ ይህ በአላህ ላይ ገር ነው፡፡” (አል’ሐዲድ፡ 22

ኢንሻአላህ
ይቀጥላል

🖊ام فاروق
=
https://t.me/https_Asselefya1
አል-ኢኽዋነል ሙስሊሚን
የጂሂሊያህ ባለቤቶች አምሳያ ናቸው።
Sheki Muhammad Zayn
አል-ኢኽዋነል ሙስሊሚን በተመሰረቱበት ሀገር(መፈንቅለ መንግስት ለማረግ ሲሞክሩ) ምን ደረሰባቸው?

በዛያ ጭንቅ ጊዜ ማን አስጠጋቸው?


https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
•
~ አትዘን ፥ አላህ ከእኛ ጋር ነውና።
•
ይህች ውብና ጀግና የሆነሽን ቃል የተናገሩት የአላህ መልእክተኛ (ሰ ዐ ወ) ሲሆኑ ከወዳጃቻቸው ከአቡበከር አስ = ስዲቅ (ረ ዐ) ጋር ከሐዲያን ከበዋቸው በነበረበት ዋሻ ውስጥ ሆነው ሳሉ ነበር። በርግጥም ጽናትን የሚፈጥር ማንነትን የሚለውጥ ፣ በጉልበትና በጽናት ፣ በቆራጥነትና በእውነተኝነቱ ላይ ተመርኩዘው የተናገሯት ቃል ነበረች።
•
~ ምንግዜም አላህ ከእኛ ጋር ካለ ለምንድን ነው የሚታዘነው? ለምድን ነው የሚጨነቀው? ጽና ፣ ተረጋጋ ፣ ስከን በርግጥም አላህ ከእኛ ጋር ነውና።
•
~ በርግጥ አላህ ከእኛ ጋር ነውና አቡበከር ሆይ! ራስህን ከፍ አድርግ። አንደበትህን አረጋጋ። ልቦናህን አሳርፍ።
•
~ በርግጥ አላህ ከእኛ ጋር ነውና አቡበከር ሆይ! በስኬት ተሰበር። ድልን ጠብቅ። መከፈትን ተጠባበቅ።

https://t.me/abumahi13
https://t.me/abumahi13
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የላኢላሀ ኢለሏህ ዋጋና ትሩፋቶቿ!! 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ➻ክፍል 2 ➽ላኢላ ሀኢለሏህ ከዚክር ሁሉ በላጩ፣ከንግግርሁሉ በላይ ነች። ነብዩ ሰለሏህ አለይሒ ወሰለም እንድህ ይላሉ፦ {ከዱዓ ሁሉ በላጩ የዐረፍ ቀን ዱዓ ነዉ። እኔም ከኔ በፊት የነበሩ ነብያትም ከተናገርነዉ ሁሉ በላጩ ላኢላሀ ኢለሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሑል ሀምዱ ወሁወ ዕላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር የሚለዉ ነዉ።…
➲የላኢላ ሃኢለሏህ ዋጋና ትሩፋቶቿ!!
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➻ ክፍል ⓷

➧ላኢላ ሀኢለሏህ ህይወትና ንብረትን የሚጠበቁባት ዋስትና ነች ። ነብዩ ሰለሏህ አለይሒ ወሰለም እንድህ ይላሉ፦ ከአሏህ በስተቀር የሐቅ አምላክ እንደሌለ እና ሙሐመድም የአሏህ መልዕክተኛ እንደሆኑ እስኪመሰክሩ፣ሶላትን በሚገባ እስከሚሰግዱና ዘካን ለሚገባዉ እስከሚያደርሱ ድረስ ሰዎችን እንድዋጋ ታዝዣለሁ። ይህን ካደረጉ ደማቸዉንና ገንዘባቸዉን ከኔ ጠብቀዋል ። በሐቆቻቸዉ ቢሆን እንጂ።(ዉስጣቸዉ በተመለከተ) ምርመራቸዉ በአሏህ ላይ ነዉ።}[ቡኻሪ:25፣ሙስሊም፡133}

➠ላኢላ ሃኢለሏህ የነብዩን ምልጃ ለማግኘት ዋና ሰበብ ነች። አቡ ሁረይራ ነብዩን ሰለሏህ አለይሒ ወሰለም ``በእለተ_ቂያማ ምልጃዎትን በማግኛት ከሰዉ ሁሉ አድለኛዉ ማነዉ?''ብለዉ ሲጠይቋቸዉ በቂያማ ቀን ምልጃዬ ከሰዉ ሁሉ እድለኛዉ ከልቡ ወይንም ከነፍሱ ጥርት አድርጎ''ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም ያለ ነዉ አሉ። {ቡኻሪ:99}

➲እነዚህ ከላኢላ ሃኢለሏህ እጂግ በርካታ ጥቅሞች ዉስጥ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ። በጥቅሉ ላኢላ ሃኢለሏህ
ከድንጋጌዎቹ ሁሉ ከባዷ ፣ከትዕዛዝ ሁሉ ቀዳሚዋ ነች። ላኢላ ሀኢለሏህ መልዕክተኞች ሁሉ የተላኩባት፣ መለኮታዊ መፀሀፍ ሁሉ የወረዱባት፣ ሰማያትና ምድር የቆሙባት፣ ፍጡራን ሁሉ የተፈጠሩባት፣ የሃይማኖት መሠረት የተጣለባት ፣ቂብላ የተወሰነባት፣ የጂሃድ ሰይፍ የተመዘዘባት ቃል ነች።

➳ላኢላ ሀኢለሏህ በባራያዎች ሁሉ ላይ የተጣለች ንፁህ የአሏህ ቃል ነች።

➳ላኢላ ሀኢለሏህ በዱኒያ ደም፣ገንዘብና ቤተሰብን ጠባቂ፣ በአኺራ ከቀብር ቅጣትና ከእሳት ቅጣት አትራፊ ነች
።

➳ላኢላ ሃኢለሏህ ያለሷ ማንም ጀነት የማይገባባት ልዩ መልዕክት ናት።

➳ላኢላ ሃኢለሏህ ወደ አሏህ መድረሻዋ ብቸኛዋ ገመድ ነች
።

➳ላኢላ ሀኢለሏህ ሙስሊም መሆኛ ወሳኝ ቃል የሠላሙ ሀገር ቁልፍ ናት።

➳በላኢላ ሀኢለሏህ ሳቢያ ``ሰዎች እድለኛ`` እና እድለ ቢስ''ክቡርና''እርጉም ተብለዉ ለሁለት ይፈረጃሉ።

➳በላኢላ ሀኢለሏህ ሳቢያ ሀገራት የክህደት እና የኢስላም ተብለዉ ሀገራት ለሁለት ጎራ ይከፈላሉ
።

➳በላኢላ ሃኢለሏህ የወዳኛዉም አለም የፀጋ ሀገርና የዉርደት ሀገር ተብሎ ለሁለት ይከፈላል።

➳ላኢላ ሃኢለሏህ አምልኮቶች በሙሉ የሚቆሙባት ተሸካሚ ምሶሶ ናት
።

➠መጨረሻ ላኢላ ሃኢለሏህ የሆነ ሰዉ ጀነትን ይታደላል።(አድዳኡ ወድደዋእ፡301)

➮ተዉሒድ የሁለት ሃገር የስኬት ቁልፍ ከሚለዉ ከኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁሏህ መፀሃፍ
ከገፀ 104____105 የተወሰደ!!



🖊𝐔𝐦𝐮 -𝐔𝐬𝐞𝐲𝐦𝐢𝐧

https://t.me/https_Asselefya1
" የሰው ልጅ ደካማ ከመሆኑ የተነሳ
⇨ አንድ ቃል ታስደስተዋለች
⇨ አንዷ ደግሞ እንዲያዝን ታደርገዋለች

( وَخُلِقَ ٱلْإِنسَٰنُ ضَ
عِيفًۭا )
" ሰውም ደካማ ሆኖ ተፈጠረ ፡፡"
[ኒሳእ 28]
◾️ኢብኑል ጀውዝይ አላህ ይዘንለትና እንዲህ አለ። 【ከሙሲባዎች ውስጥ ትልቁ፦ መንገድ ስተህ ሳለ ሸይጣን የተስተካከልክና ቀጥ ያልክ አስመስሎ ያቀረበልህ ጊዜ ነው።】
كشف الشبهات ١۰
<unknown>
📚አዲስ የተጀመረ ኪታብ ደርስ!
〰〰〰〰〰〰〰〰
🔻
#ከሽፉ_ሹቡሀት ‼️
~
✍ الشيخ الإسلام محمد ابن عبدالوهاب رحمه الله

🔅 شرح : العلامۃ الفقيه محمد ابن صالح العثيمين رحمه الله

✅ ክፍል => 🔟 የመጨረሻው ክፍል

🎙 አብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ" ➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯ ➳ክፍል ዘጠኝ ➧በሌሎች የዲን መሰረቶች ማመን ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➠በሌሎች የዲን መሰረቶች ማመን፡ በመላኢካዎች ፣ በመጽሐፎች በመልእክተኞች ፣ በመጨረሻው ቀን ፣ መልካምም ይሁን መጥፎ በአላህ ውሳኔ የሚከናወን መሆኑን ማመን ናቸው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ በአላህ የማመን ተከታዮች ወይም በአላህ የማመን ቅርንጫፎች…
➢ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ"
➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯

➳ክፍል አስር

➽በቀደር የማመን ደረጃዎች የሚለውን ቀጣዩን
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ሰማያትና ምድር ከመፈጠራቸው አምሳ ሽ አመት በፊት አንድም ሳይቀር ውሳኔዎች ሁሉ “ለውሀል መህፉዝ” ላይ ተዘግቧል፡፡ ሁሉም ነገር በለውሀል መህፉዝ የተጻፈ መሆኑ በትክክለኛ ሀዲስ ተዘግቧል፡፡

አላህ በተከበረው ቁርዓናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

◆وَعِندَنَا كِتَابٌ حَفِيظٌ

“እኛም ዘንድ ጠባቂ መጽሐፍ አልለ፡፡” (ቃፍ፡ 4)

➠ሶስተኛው ደረጃ፡ አጠቃላይ በሆነው የአላህ መሽአ እና ኢራዳ እናምናለን፡፡ አላህ ከውንያ በሆነው ኢራዳ አንድን ነገር ከፈለገ መፈጸሙ አይቀርም፡፡በዓለም አንድም ነገር አይከሰትም በርሱ ፍላጎት ፣ መሽአ እና አስተዳደር ቢሆን እንጅ፡፡

➠አራተኛው ደረጃ፡ ሁሉም ነገር ለአላህ ፍጡር ነው ብለን እናምናለን፡፡ አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀፅ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

◆اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ

“አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡”
አዝ ዙመር፡62

➳በዓለም የሚከሰተው ነገር ሁሉ የአላህ መፍጠርና ማስገኘት ነው፡፡ ከአላህ ውጭ
አንድን ነገር ማስገኘት እና መፍጠር የሚችል የለም
፡፡

➲የሰው ልጆች ኢራዳ (ፍላጎት) ከአላህ ኢራዳ (ፍላጎት) አለመውጣት
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➠ይህ የሰው ልጅ ለመስራትም ይሁን ለመተው ፣ በእርሷም ጎጅውን ከጠቃሚው ለመምረጥ የሚያስችለው የራሱ የሆነ ኢራዳ (ፍላጎት) ፣ መሽአ ፣ ምርጫ ከመኖር የሚከለክል አይደለም፡፡

➧የሰው ልጅ በኢራዳው መልካምን ፣ በጎ ነገሮችን ፣ የአላህን ትዕዛዛት ይፈጽማል፡፡
በኢራዳው (በፍላጎቱ) ትዕዛዝን እና ዋጅብ የሆኑ ነገሮች ይተዋሉ፡፡ በእርሷም ክፉ ነገሮች ፣ ወንጀሎችና ተቃርኖዎች ይፈጸማሉ፡፡ በእርሱ ኢራዳና ተግባር ሂሳብ ይደረጋል፡፡


➳ነገር ግን የእርሱ ኢራዳውና መሽአ ከአላህ ኢራዳና መሽአ የሚወጣ አይደለም፡፡

አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል

◆وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ

“የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡” አት ተክዊር፡ 29

➽ለባሪያው መሽአን አጸደቀ፡፡ ነገር ግን ከእርሱ መሽአ ጋር አቆራኘው፡፡ በዚህ
ምክንያት አንድ ሰው “ማሻአሏሁ ወሽእተ” በማለት ለነብዩ ያናገራቸው ጊዜ የሚከተለውን ምላሽ ነበር የሰጡት፡-"ለአላህ ባላንጣ ታደርገኛለህ እንዴ?” ፤ “ማሻአሏህ ሱምመ ሽእተ” (አላህ የሻው
ከዚያም አንተ የሻሀው) በል አሉት፡፡ ወይም “ማሻአሏሁ ወህደሁ” (እርሱ የሻው ብቻ ሆነ) በል አሉት፡፡


አልባኒ ተህዚር አስ ሳጅድ፡ አህመድ ሻኪር ዑምደቱ አት ተፍሲር፡

ኢንሻአላህ
ይቀጥላል


=
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️አዝካር ወል አዳብ
➖➖➖➖➖➖
🔻الأذكار والآداب

➡️ መጥፎና ጥሩ ጓደኛ
➡️ ሙስሊምን ዝቅ ማድረግ
➡️ የሚስጥር ሹክሹክታ
➡️ ሙዚቃና የሙዚቃ መሳሪያ

↪️ ክፍል 3⃣8⃣ ↩️
〰〰〰〰〰〰

🎙 አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💦አል-ሓሪስ ኢብን ዓሲም አል-አሽዓሪይ እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ።

▪️“ጡሃራ (ንጽህና)የኢማን ግማሽ ነው።
▪️ አልሓምዱሊላህ (ምስጋና ለአላህ ነው)ሚዛን ትሞላለች።
▪️ ሱብሓነላህ ወልሓምዱሊላህ (አላህ የጠራ ነው እና ምስጋና ለአላህ ነው)በሰማይና በምድር መካከል ያለውን ይሞላሉ ወይ ትሞላለች።

▪️ሶላት ብርሃን ነው።
▪️ሰደቃ ማስረጃ ነው።
▪️ትእግስትም ብርሃን ነው።
▪️ቁርአንም ላንተ ወይንም ባንተ ላይ ማስረጃ ይሆናል።
↪️ሁሉም ሰዎች ይማልዳሉ ነፍሶቻቸውን ይሸጣሉ አንዳንዶቹ ነፍሶቻቸውን ነጻ ያወጣሉ፥ አንዳንዶቹ ደግሞ ነፍሶቻቸውን ያጠፋሉ።

📚(ሙስሊም ዘግቦታል።)

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
የሰለፍያ ጎዳና ትክክለኛው ጎዳና ናት
ኢብኑ ተይሚያ ረሂመሁሏህ

መጅሙዕ አል ፈታዋ 99/10
➲ያኦኽቲል ጋሊያህ ባለቤትሽን ስለ መልካምነቱ ማመስገንሽ ፍቅራችሁን ከማጎልበቱና እሱን ለበለጠ መልካምነት ከማበረታታቱ ባሻገር አላህን ማስደሰት ነው!!

قال صلى الله عليه وسلم : (لا ينظر الله إلى امرأة لا تشكر لزوجها و هي لا تستغني عنه) رواه النسائي و صححه الألباني في الصحيح 289

➧የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል

«ከባሏ የማትብቃቃ ስትሆን ባሏን የማታመሰግን ሴት፣ አላህ በእዝነት አይኑ አይመለከታትም።”
➳ኢማሙ ነሳኢ ዘግበውታል፤ አልባኒም ሰሒህ ብለውታል

➧እናማ ኦኽታየ ባለሺ ነገር ተብቃቂ የዱኒያ ጥቅማ ጥቅም አያታልሺ የሙዕሚን ሀገር ዱኒያ አይደለችም!!! ለዲኒያ ብለሺ አኼራሺን እንዳታበላሺ እንትብሂ!

🖊የፋሩቅ ማም

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w