💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
‏قال تعالى

﴿وَمَن يُؤْمِن بِاللَّهِ يَهْدِ قَلْبَهُ ۚ﴾

▪️‏قال ابن ؚباس -رضي الله عنه-

‏«يهدي قلبه لليقين، فيعلم أنَّ ماأصابه لم يكن ليخطئه، وما أخطأه لم يكن ليصيبه».

📓[«تفسير الطَّبري» (٤٢١/٢٣)]
አድስ የሰማሁት ቃሪዕ ነዉ ተጋበዙ!

@ሀበሻዊ ቃሪእ
السلام عليكم ورحمه الله وبركاته
ውድ እህቶች እና ወንሞች  የኸን በፎቶው ላይ እምትመለከቱትን ልጅ አፈልጉን ከየመን ወደ ድንበር መጥቷል ከተባለ አምስት ወሩ ነው ከዛ ወድህ አየነው እሚልም ሆነ እሱም ድምፁም አልተሰማ ያያችሁ እባካችሁ አድራሻውን ንገሩን
  ስም ሁሴን አደም አሊ የትውልድ ሀገር  ወሎ ወረዳ ሀብሩ ቁጥር 10 ነው
በዚህ ቁጥር በኢሞም በቴሌግራምም በመስመርም  በዋትሳፕም (0554836852 ወይም+966556285832 በሁሉም ይሰራል አሳውቁን ባረከሏሁ ፊኩም እናት እና አባቱ ተጨንቀው ሊሞቱ ነው
የኢትዩ ቁጥር +251937438584
የሚታረደው እንስሳ በግ፣ ፍየል፣ ከብት እና ግመል ብቻ መሆን አለበት።
የሚታረደው እንስሳ እድሜው የደረሰ መሆን አለበት፡፡ በግ 6 ወር፣ ፍየል 1 አመት፣ ከብት 2 አመት፣ ግመል ከሆነ 5 አመት የሞላው መሆን አለበት፡፡
https://t.me/fejir_tube
Audio
❝አዲስ የአቂዳ ኪታብ ቂርአት❞
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️


☞የኪታብ ርዕስ፦ሚን ኡሱሊ አቂደቲ አህሊ ሱነቲ ወልጀመዓ!!

❂ ክፍል   09

📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟 ⇩⇩
t.me/https_Asselefya1/11411

🎙በአቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ

  ⇘⇘⇘⇘⇘⇘⇙⇙⇙⇙⇙⇙
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
https://t.me/https_Asselefya1
Forwarded from đŸ’ŽŘŁŮŘŽŮ’تِي عَيْشِي مَعَ الكِتٰابْ وَالسُّنَّة💎
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🏙☀️
ጫሊ
~
ሰሞኑን ጫሊ፣ ጫሊ የሚሉ ፅሁፎችን እያየሁ ነው። ማለታቸው ባልከፋ! ወሬያቸው እንዳለ ልጓም በሌላቸው አፍሰህ አቅመኝ ወሬ የተሞላ መሆኑ እንጂ። ከነዚህ ፅሁፎች ጫሊን ትልቅ የዒልም ማዕከል አስመስለው የሚያቀርቡ እያየሁ ነው። ጫሊ የጭፈራና የቂምሃ እንጂ የዒልም ማዕከል አይደለም። ይሄ የብዙ የሃገራችን ስመ ገናና ቦታዎች የጋራ እውነታ ነው። የሱፊያ አድናቂዎች ለህዝብ የሚስሉት የተጋነነ ምስልና መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እጅግ የተራራቀ ነው። የሚገርመው ስንት ትምህርት የሚሰጥባቸው ማዕከላት ባቅራቢያ እያሉ ስማቸውንም ሳያነሱ ነው የ "ሐድራ" ቦታዎችን የውሸት ቂሷ እየፈበረኩ በፈጠራ ታሪክ የሚያስተዋውቁት። እንዲያውም አብዛኞቹ እነዚህ ቦታዎች የሺርክ ማዕከላት ናቸው። ለምሳሌ የጫሊን መንደር ብንወስድ ለመውሊድ በሚታደሙ ሰዎች ሺርክ የሚፈፀምበት የሸህ ጫሊ ዶሪሕ (ቤት የተሰራበት ቀብር) አለ። እዚያ ቦታ ላይ አገር አቆራርጠው ለመውሊድ ለሚታደሙ ሰዎች የቀብር አፈር ሁሉ ይከፋፈላል። ይሄ እራሴ በአይኔ ያየሁት ነው።

"ጫሊ የት ነች?" ለምትሉ፡ ደቡብ ወሎ ውስጥ ከሐይቅ ከተማ በስተምስራቅ አቅጣጫ 48 ኪሎ ሜትር አካባቢ ርቀት ላይ ወረባቦ ወረዳ ውስጥ የምትገኝ ትንሽ መንደር ነች። የመንደሯ ስም ገንዲ ጎራ ነው። ባቅራቢያ ባለው የሚሌ - አዋሽ ገባር በሆነው የጫሊ ወንዝ ሰበብ ከገንዲ ጎራ ይልቅ ጫሊ በሚለው ስም ይበልጥ ትታወቃለች።
=
https://t.me/IbnuMunewor
➡️ ሴት ልጅ ማረድ ትችላለች⁉️
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰

✅ ሴት ልጅ አስተራረድ የምታውቅና አሳምራ የምታርድ እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶች የምታሟላ ከሆነ ችግር የለውም ማረድ ትችላለች። ሶሂሁል ቡዃሪ ላይ እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ በድንጋይ ፍየል ያረደችን ሴት ተግባር አፅድቀውላታል። እንደውም ያረደችውን እንዲበላ አዘዋል። ስለዚህ ሴት ልጅ ልክ እንደ ወንድ ልጅ ግመል፣ በሬ፣ ፍየል፣ በግና ዶሮ ማረድ ትችላለች።

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
በጣም የወደደ ልብ በጣም ይጠላል......!!!
ህይወት ውስጥ ሁሌም የሚያስደስትህ፣ሁሌም የተመኘኽው ፣ሁሌም እንደፈለከው አታገኛትም።ስትደሰት ስትከፋ ስትመኝ ስትኖር በተስፋ ስታገኝ ስታጣ፣ስትወድቅ ስትነሳ ፣ አንዳንዴም በእውን አንዳንዴም. በተስፋ ትኖራለህ ።ይቺ ናት ህይወት. እወቃት!

@AbuHafsaYimam
ደም መለገስ አላስፈላጊ ደም ውስጥ ያሉ ስቦችን ይቀንሳል። ይህም ለልብ ህመም ተጋላጭነትን ይቀንሳል።

https://t.me/drdawudconsultancy
የእድሜሽ መሄድ ሳይሆን ልትጨነቂ የሚገባሽ በዚህ እድሜየ ምን ሰርቻለሁ ለአኼራየ ብለሽ መጨነቅ ያለብሽ እድሜ አትጨነቂ ከተፃፈልሽ ዉጭ አትቀንሽም አትጨምሪም!!

=

t.me/https_Asselefya1
ነፍስህ ልክ እንደጠላትህ ነች ቆራጥ ስትሆንባት ትታዘዝሀለች። ደክመህ ስታገኝህ ግን ታስርሃለች"

📝 ኢብኑል ቀይዪም ፦ቢዳየቱል ፈዋኢድ

@https_Asselefya1
«ለሰለፍያ እንስቶች ማስታወሻ ትሁንልኝ»
       
  📝ምድር  ተውባለች📝

በአላህ ትእዛዝ ጅልባብሽ ተጊጠሽ
በነአኢሻ ፈለግ  ኒቃብን ጨምረሽ
በቁርአን በሀድስ ኑሮሽ የምትመሪ
አኼራን አስታውሰሽ በደስታ እምትኖሪ
በመዝሀበል ሀቅ የተገነባሽው
ጀግና ሰለፎችን ሞደል ያደርግሽው
ምድሪቱ ደምቃለች በእንደ አንች አይነት ጀግና
የአላህን ትእዛዝ   አክባሪ ነሽና
ለሌሎች ተምሳሌት በተውሂድ በሱና
መሆንሽ ግልፅ ነው ሁሉም ያውቃልና
ሀቅን የምትወጂ ከማንም ከምንም
ሀታ ቢሆን እንኳ ከናትም ከአባትም
በእምነትሽ ለመጣ ማንም አትሰሚም
በሱናሽ ላሾፈ አትደራደሪም
የቀደምቶች መንገድ ሲነካ ያምሻል
ሰው ሽርክ ሲያቦካ ሁሌም ይቆጭሻል
ብቻ ምን ልናገር አላህ አድሎሻል
በመንሀጀ ሰለፍ ብዙ አሳልፈሻል
ሁሉን ተቋቁመሽ እዛሬ ደርሰሻል
ውበት ጥንካሬሽ ሁሉን ያስገርማል
ለአህለል ባጢሎች የእግር እሳት ሁኗል
ለሱና ሰወች ግን እጅግ ያስደስታል
ምሳሌሽ ፋጢማ እጅጉን ያማረች
ጀግና የጀግና ልጅ ውብ የተከበረች
ማለዳ ተንስታ ፀሀይዋ እስከወጣች
በሰለፍያይቱ በአንች እንደደመቀች
አልሀምዱሊላሂ ምድር ተውባለች


አቡ ሹራ➭ነሀሴ/18/12/2014

𝐓𝐞 ~ t.me/https_Asselefya1
▪አንዳዴ .......

ድብር ይላል ይሄ ኢማናችን ሲደክም ነዉ።
አላህ ኢማናችንን ያጠንክርልን!

=
📝ኢብኑ ረጀብ አላህ ይዘንላቸውና ከፊል ሰለፎች እንዲህ ብለዋል አሉ።

➘ ማፍጠሪያህ ሞት እስኪሆን ድረስ በዱንያ አለም ላይ እስካለህ ከሀራምና አላህ ከከለከላቸው ነገራቶች ሁሉ ፁም (ተከልከል)።
📚لطائف المعارف
@https_Asselefya1
«ወሎ እንኳን ሄደዉበት ስሙ ሲጠራ በደስታ የሚፈነድቁ ብዙ ናቸዉ። «ወሎ የደጋጎች ሀገር !!»

«መልካም ጉዞ 🚐 መልካም ቆይታ ወንድሜ አብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን»

«ኡስታዛችን ፏ አድርጋችሁ ተንከባክባችሁ ሸኙልን ወለየዎችዬ! የኔ ጀግኖችዬ!!»
⭕️👉የነገውን የሰኞ ፃም እንዳያመልጠን እንፁመው። ብዙ መልካም ነገሮችን አቅፎ የያዘ ነው።

①) ነብዩ ሲፃሙት የነበረ የውዱ ነብያችን ሱና ነው
②) ስራዎች ወደ አላህ የሚወጣበት ቀንም ጭምር ነውና ስራችን ፃመኛ ሆነን አላህ ዘንድ እንዲቀርብልን የሚያደርግ ነው።
③) ይህ ቀን ደግሞ እጅግ ውድ በሆኑት የዙልሂጃ አስር ቀናቶች ውስጥ መገኘቱ ሌላው መለያ ነው።
④) በዙልሂጃ የሚፃም ሱና ፃም ከሌላ ጊዜ ከሚፃመው የበለጠና የላቀ አጅር ስለሚያስገኝ እንጹመው።


t.me/Sadik_Ibnu_Heyru