💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
ሰለፎች ከሚያደርጉት ዱአ ውስጥ አንዱ እንዲህ የሚል ነበር፦

【አላህ ሆይ፦ አንተን በመታዘዝ አልቀኝ አንተን በማመፅ አታዋርደኝ】ይሉ ነበር።
📚الداء و الدواء (٩٤)
📩ይድረስ👇
ኢንተርኔት ለምትጠቀሙ እህቶች‼️

♻️በኢንተርኔት ከንቱ ምኞት ትዳርዋን የተበላሸባት፤ ህይወቷን የጨለመባት እንስት አስተማሪ ታሪክ…

ወጉ ወዲህ ነው👇
ሚስት አላህ ይጠብቀንና በኢንተርኔት ሱስ የተጠመደች ናት። ባለቤትዋ ከዚህ ተግባርዋ እንድትቆጠብ በተደጋጋሚ ቢመክራትም ልትቀበለው አልቻለችም። ብዙ ለመናት ብዙ አስመከራት "አሻፈረኝ" አለች። የምትጠቀምበትን ስልክ ሳይቀር ወስዶባታል። እሷም ሌላ ስልክ በመፈለግ ኢንተርኔት ላይ መዘውተሯን ቀጠለች።

በዚህ ጊዜ ባል አንድ ዘዴ ይዘይዳል👇
ወደ facebook በመግባት እንደ ሚባለው "fake acount" (የውሸት አድራሻ) በመክፈት ስሙን ይቀይርና ፕሮፋይሉ ላይ ሀብታምና ቆንጆ የሚመስል የወንድ ምስል ያስቀምጣል። ከዝያ በኋላ የሚስቱን የ facebook አድራሻ በመፈለግ ያናግራት ጀመረ።

👆ጨዋታው የተጀመረው እዚህ ቦታ ነበር
በሰላምታ የተጀመረው ንግግር ወደ ትውውቅ ይሸጋገርና ያለችበትን የኑሮ ሁኔታ ጨርሳ ትነግረዋለች። እሱ ግን እየዋሻት እሷን በምትፈልገው አይነት ራሱን እየገለፀ ያጫውታታል።
ባለ ትዳር እንደሆነችና ነገር ግን በትዳሯ ላይ ደስተኛ እንዳልሆነች ስትነግረው
"እንግዲያውስ ባልሽን ይፍታሽና ከእኔጋ እንደመር" ይላታል።
ባቀረበላት ሀሳብ ደስተኛ ሆና ከባልዋ ጋ በምን ዓይነት መልኩ መፋታት እንዳለባት መላ ይፈልጋሉ። እሱም "በቃ ሳትጎዳዱና ሳትጨቃጨቁ እንድትለያዩ ችግር በማይፈጥር መልኩ ባህሪሽን ቀይሪበት" ይላታል።

ባል ስራ ውሎ ማታ ሲገባ የሚስቱ ባህሪይ ከቀን ወደ ቀን እየተቀያየረ ይመጣል። ሚስት የማታውቀው ባል የፈጠረው ጨዋታ ነውና ቀን እያወራት ማታ ገብቶ ይታዘባታል። [አላህ ይጠብቀን]

ጨዋታው ሲጧጧፍ ባል ማታ ይገባና
"ሰሞኑ እያየሁብሽ ያለው ነገር እያስደሰተኝ አይደለም ምን ተፈጥሮ ነው?" ይላታል
"ምንም" ትለዋለች
"ንገሪኝ ችግርሽ ዝምታ መፍትሄ አይሆንም" ሲላት
"ምንም አልሆንኩም" ትለዋለች
"ሀሳብሽ በግልፅ ንገሪኝ ከእኔ መለየት ትፈልጊያለሽ ያልተመቸሽ ነገር አለ እንዴ?" ሲላት
"ቢሆን አይከፋኝም" ብላ ፍላጎትዋን ገለፀችለት።

ፍላጎቷን ግልፅ ካደረገች በኋላ ባልየው ቀጥታ ወደ ፈለገው ጨዋታ ይገባና ያናግራታል👇
"እንግዲህ መለያየታችን አይቀሬ ከሆነ አንቺም የሄድሽበት እንዲቀናሽ እኔም ቤቴና ንብረቴ ተበታትኖ ህይወቴ እንዳይበላሽ ከመሄድሽ በፊት ሁለተኛ ላግባና ልክ እንዳገባኋት ለእሷ አስረክበሽ ትሄጃለሽ" ይላታል።
  ሚስትም ያሳሰባት ሁለተኛ ማግባቱ አለ ማግባቱ ሳይሆን የእሷ መፈታት ነበርና "ምንም ችግር የለውም" ብላ ትስማማለች።

ባልየው በማግስቱ ወደ ሚስቱ ቤተሰቦች በመሄድ የተነጋገሩበት ነገር ያጫውታቸውና ሁለተኛ ሊያገባ መሆኑ ይነግራቸዋል።
ሁለተኛ ሚስት ፍለጋ ተ ጀ መ ረ

ባል ሊያገባት ሚስት ደግሞ አስረክባት የምትወጣዋ ሁለተኛ ሚስት በሁለቱም ብርቱ ፍለጋ "ትሆናለች፣ ትመጥናለች" የተባለችዋን አፈላልገው አገኙ።
ያዝ እንግዲህ……

የሁለተኛዋ ሚስት የኒካህ ቀጠሮ ይያዛል። ልብ በሉ ሁለተኛዋ እንደ መጣች የመጀመሪያዋ ተሸኝታ 👉ያ በኢንተርኔት መንፈስ ብቻ የምታውቀው ባልዋ ሊያገባት ነው።

የማይደርስ የለምና የኒካሁ ቀን ደረሰ። ባል ልክ የሁለተኛ ሚስቱ ኒካህ እንዳሰረ ያ ሚስቱን ሌላ ሰው መስሎ ያወራበት የነበረው የ facebook አድራሻ ዘግቶት ከኢንተርኔት መንደር ይወጣል።
لا إله إلا الله

የመጀመሪያዋ ሚስት ባልዋ ሌላ እንዳገባና ከባልዋ ተለያይታ አዲስ የተዋወቀችው ሰወዬ ልታገባው እንደሆነ ልታበስረው ስትገባ ያ በውሸት ሲያወራት የነበረው ባለ facebook አድራሻው ዘግቶ ከመንደሩ ጠፍቷል።

ዱንያ የት አትጥበባት?
"ምድር ዋጭኝ" ብትላት መች ልትውጣት? ህይወት ጨልሞባት፣ መኖር አስጠልቷት ራሷን እየረገመች አዝና ተክዛ ቁጭ ብላለች።

ባል አዲሷ ሙሽራው ጋ መቆየት ያለበትን ቆይቶ መጫወት ያለበትን ተጫውቶ ወደ ቀድሞ ሚስቱ ቤት ሲሄድ በሀዘን ተውጣ ተቀምጣለች።
"ምንድን ነው ሰላም አይደል እንዴ?" ሲላት
"ሰላም ነው" ትለዋለች
"ምን ሆንሽ?"  "ምንም"
ትቷት ይሄዳል።

አሁንም ተመልሶ ሲመጣ ሰውነቷ ከሳስቶ ፊቷ ተሸብሽቦ ያገኛታል
"ምንድን ነው የሆንሽው?"
"ምንም አልሆንኩም"
"ያስቀየምኩሽ ነገር አለ"
"ኧረ የለም"
"ሀሳብ መቀየር አስበሽ ነው?"
ፀጥ ረጭ አለች።

የዛኔ ባል አጠገቧ ቁጭ ብሎ እያፅናናት
"ምን ላርግ ታድያ? ከአንቺ መኖር እየፈለግሁ፣ ሳልጠላሽ፣ ሳላስከፋሽ በራስሽ ፍላጎት ያመጣሽው ሀሳብ ነው። እኔ ግን አሁንም ቢሆን የማከብርሽ የምወድሽ ባለቤቴ ነሽ። አንቺም ከእኔ የመለየት ፍላጎት ከሌለሽ ያመጣኋትም ሙስሊም እህትሽ ናት አብራችሁ ትኖራላችሁ። እሷም በቤቷ አንቺም በቤትሽ አብረን እንኑር።" አላት

በዚህ ሰዓት ካላይዋ ላይ የተጫናት ተራራ የተነሳላት በሚመስል መልኩ በደስታ ፈንጥዛ ባልዋን እየሳመችና እያመሰገነች እያለቀሰች ደስተኝነቷን ገለፀችለት።

በመጨረሻም ባልየው ባለ ሁለት ሲም ሆኖ ከሁለቱም ሚስቶቹ ጋ አብረው መኖር ጀመሩ።


NB: ታሪኩ ላይ የተጠቀሱ በሸሪዓ ክልከላ ያለባቸው ነጥቦች አሉ [ፎቶ መጠቀምና ውሸትን] ይመስል
ዘንግተናቸው ሳይሆን ከታሪኩ ብዙ ሰው ሊማር ይችላል ብለን ስላሰብን ነው።
ማስተላለፍ የተፈለገውም ባሎች እንዲህ እንዲያደርጉ ሳይሆን ሴቶች ከምንም ነገር በፊት ክብራቸውን (ትዳራቸውን) ማክበርና መታዘዝ እንዳለባቸው ለማስገንዘብ ነው።


ኮፒ!!
↪️የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች

👉ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ታዲያ ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖትችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ጥፋቶች አሉ። ከነዚህም ውስጥ
1. ቀዳሚው ድግምትና ጥንቆላ ነው፡፡ በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሀሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት እጅግ ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። ጥንቆላና ድግምት:-


ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል።} [አሶሒሐህ፡ 3387]

➧ ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን እንዲህ ይላል፡- “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም።” [ጦሃ፡ 69]

➧ደጋሚዎች የሰዎችን ገንዘብ በማታለል የሚበዘብዙ መዥገሮች ናቸው። ገንዘቡን ለነሱ የሚሰጥ አካልም አላህ ፊት ተጠያቂ ነው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {የኣደም ልጅ በቂያማህ ቀን አምስት ነገሮችን ሳይጠየቅ እግሮቹ አይንቀሳቀሱም። እድሜውን በምን እንዳጠፋው፤ ወጣትነቱን በምን እንደጨረሰው፤ ገንዘቡን ከየት እንዳመጣው፤ እንዲሁም በምን እንዳወጣው፤ ባወቀው ምን እንደሰራ።} [አሶሒሐህ፡ 946]

ደጋሚዎች የነገር ቋቶች የማህበራዊ ህይወት ጠንቆች ናቸው። የተቸገረ ደንበኛቸው መፍተሄ ፈልጎ ሲመጣባቸው በብዛት የችግሩ መንስኤ የሆነው ወይ ጎረቤቱ፣ ወይ ዘመዱ ወይ ደግሞ የቤተሰቡ አባል እንደሆነ በመጠቆም ሰዎች ውስጣቸው እንዲሻክር አለመተማመን እንዲነግስ ያደርጋሉ። በድግምቶቹ ምክንያት የጤና መጓደል፣ የትዳር መፍረስ፣ የዝምድና መቆራረጥ፣ የጎረቤቶች በጎሪጥ መተያየት አልፎም ደም የሚያቃባ ግጭት እንዲከሰት ሁሉ ሰበብ ሊሆኑ ይችላሉ።

➧ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም።} [ሙስሊም፡ 5957]

2. ሌላው በ “ዘመን መለወጫ” አካባቢ የሚፈፀመው ጥፋት በአንዳንድ አካባቢ ያለው ጳጉሜን ተከትሎ ለዱዓህ መሰባሰብ ነው። እነዚህ አካላት የጳጉሜ ዱዓህ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) በማለት ነው ወቅቱን በዱዓእ የሚያሳልፏት። በጣም የሚገርመው ለዱዓህ የሚጥጠሩት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ማለታቸው ምንኛ የሚደንቅ ሐቅ ነው?! ዲን ያስተምራሉ ተብለው የሚታሰቡት አካላት ክርስቲያናዊ አቆጣጠርን መሰረት ያደረገ ዒባዳህ እየፈፀሙ ሰዎችን ወደ ጥፋት ሲወስዱ በገሃድ ይታያሉ።


3. ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-


👉አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
👉አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
👉የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
👉እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡ ይህንን ስንል የሚደብራቸው ክርስቲያኖች አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ሰው እንዴት የኔን እምነት ካልተከተላችሁ ብሎ ሌሎችን በአክራሪነት ይፈርጃል?!

የእምነታችንን ጉዳይ ለኛ ብትተውልን። እምነታችን ሌሎች ህዝቦች በሚልለዩባቸው እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።

(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)


የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
متن أصول الثلاثة ۱۱
Abu Useymin
ተከታታይ የኪታብ ደርስ


📚ኪታብ ኡሱሉ ሰላሳ

            ➧ክፍል 
➊➊

🎙በአብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1

@abuUseyminabdurehman
#ዘመን_መለወጫ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ዘመን መለወጫ የለንም ወዳጄ፡
ኮተት አልፈልግም ዘወር በል ከደጄ፡
ሙሉ ፅድት ያለ ሐቅ ነው መንሀጄ፡
ከሉቃስ ዩሀንስ ከማርቆስ ክርስቶስ፡
ከሰውች ወደሰው ከቄርቆስ ቆሮንጦስ፡
ኸረ ለቀቅ አርገኝ አያልቅም ያንተ ጦስ?
ወደ ሰው መጠጋት ሙስሊሞች አንወድም፡
ከአንድ አምላክ በስተቀር ለማንም አንሰግድም፡
ለማርቆስ ለሉቃስ አናጎበድድም፡
ምንክንያቱም ሙታን ምንም አይፈይድም፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ስለዚህ ራቂኝ ማነሽ እንቁጣጣሽ፡
ወደኛ አትጠጊ ዞር በይ እስከ ሻንጣሽ፡
እኛ እናውቅሻለን ከየት እንደመጣሽ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
በእስልምናችን የለም እንቁ ጣጣሽ፡
ዘመን መለወጫ የሽርክ ብጥስጣሽ፡
የድግምት የመተት ክፋት መተግበሪያ፡
የክፋት የሴራ ተንኮል መቀመሪያ፡
እውነታ የሌለሽ የኩፋር መመሪያ፡
እውነትን ሰርዘሽ ውሸት ማስተማሪያ፡
ሐቅን ባጢል ብለሽ ጥመት ማበጠሪያ፡
ውስጥሽ ውጭሽ ቦድ ግድግዳሽም ጣሪያ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኢብሊስ የገነባሽ የጭፍሮቹ መተት፡
አማኞች አያውቁም እንድህ አይነት ኮተት፡
ሐቁ መመሪያችን ካላፀደቀልን፡
ውዱ ነብያችን ካልመሰከረልን።
በነሉቃስ ቀመር ተጓዥ አይደለንም፡
ዘመን መለወጫ ፈፅሞ የለንም፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የአመፅ የበደል የወንጀሎች ቅርጫ፡
የሸይጣን የአጋንንት የጥመት መፈንጫ፡
የመጥፎነት ማዕረግ የሙሽሪኮች ዋንጫ፡
ሽርክን ክህደትን በጥብጦ መጠጫ፡
ሙስሊሞች የለንም ዘመን መለወጫ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ ኑረዲን አል አረቢ 01/26/1443
http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
Audio
🎧تلاوة جميلة لخواتيم سورة المؤمنون

🎙 للقارئ صالح الفالح

https://t.me/https_Asselefya1
ልጅ መውለድን አብዙ ሲሳያችሁ ይበዛል

💭ሙሀመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን አሏህ ይዘንላቸውና እንዲህ ይላሉ:-

➲"በጌታው ላይ መጥፎ ጥርጣሬን በማሳደር ልጆችን አታብዙ፤ ሲሳያችሁ ይጠባል ያለ ሰው በእርግጥም ግልጽ የሆነ ጥመትን ተጣሟል።

➲በአርሹ ጌታ እምላለሁ በዚህ ንግግራቸው ዋሽተዋል። ይልቁንም ልጅ ሲያበዙ አሏህ ሲሳያቸውን ያበዛላቸዋል።


➲ምክንያቱም በምድርም ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም ሪዝቋ በአላህ ላይ ያለ ቢኾን እንጂ፡፡ ወጪ ታደርግላቸው ዘንድ የልጆችህን ሲሳይ የሚከፍትልህ አሏህ ነው።


➲አብዛኛው ሰው ግን በጌታው ላይ መጥፎ ጥርጣሬ ያሳድራል፤ ፊት ለፊቱ ባለው በሚታየው ቁሳዊ ነገር ላይ ብቻ ይደገፋል፤ የወደፊቱንም አያይም፣ የጌታውንም ችሎታ አይመለከትም። ልጆች ቢበዙም ሲሳይን የሚለግሰው እሱ 7 ነው።ልጆችን አብዛ ሲሳይህ ይሰፋል።ትክክለኛው ይህ ነው ።"

📚ሸርህ ሪያዱሷሊሂን [1/91]


https://t.me/https_Asselefya1
➧የዕለቱ መልዕክት➛ወንድ ሁን!

ሴት ልጅ ትለምነኝ ትለማመጠኝ አትበል
ትታገልልኝ ላድክማት  ልፈትናት ልንቀባረርባት አትበል
!!

ወንድ ሁን አንዱ የውንድነት መገለጫህና ውበትህ የወንድነት መለያህ  ከላይ የተጠቀሰው በግልባጭ አንተጋ ሚገኙ ሲሆኑ ነው በቃ ወንድነሃ እነዚህ ያንተ ስራዎች ናቸው ወንድነት በፆታ ብቻ አይገለፅም በዋናነት ተግባሩ ነው ሚገልፀው!
!

ስለዚህ ቀድህ ተገኝ ለሴት ልጅ ተንበርከክጂ እንድትን በረከክልህ አትፍቀድ አሸንፍጂ አትሸነፍ  ቅደምጂ አትቀደም ኢማም ሁንላትጂ ኢማም  አትሁንልህ ፈጣን ቀልጣፋ ጂ ልፍስፍስ አትሁን ምራትጂ አትምራህ አስተዳድራትጂ አታስተዳድርህ አግባትጂ አታግባህ ለምናትጂ አትለምንህ  ምከራትጂ አትምከርህ አስተምራትጂ አታስተምርህ!!

ደግ ሁንላትጂ አትክፋባት ታዘዛትጂ አትገልምጣት እጄ አስገባኋትጂ እጄ አስገባሁት አትባል በቃ ወንድ ሁን ቀዳሚጅ ተቀዳሚ አትሁን ፈጣን እንጂ አዝግም አትሁን!

አስተዋይ እንጂ ዝፍቅ አትሁን ሚያስደስትንና ሚያስጠላን ራስህ ለይጂ ሰዎች እንዲለዩልህ አትፍቀድ ጧሊበተል ኢልምጂ ጃሂል አትሁን በቃ ቅደምምምምም  ይህ ነው በወንድ ላይ ሚያምረው ሚገልፀው ስለዚህ መገለጫዎችህን እወቅ ላንተ የሆኑትን ያልሆኑ ቦታ ላይ እንድታይ አትፍቀድ......!!

ኮፒ!

https://t.me/https_Asselefya1
➧ሀቢብቲ ያንቺ  መከናነቢያና ኒቃብሽ ⁈

በእምነትሽ ላይ ያለሽን እውቀት
የሚገልፅ ነው።  አለማወቅን መላቀቅሽንና
ብልጠትሽን እጅግ ውብ ዘመናዊነትሽን ያሳያል።


እንደመሸፋፈኛሽ አንደበትሽም ንቁና የተረጋጋ አሰተዋይ ሀቀኛ ይሆን ለማወቅ በምታደርጊው ጥረት ድክመትሽን ጃሂልነት  ያደረጉ ለሚቆነጥጡሽ ሰዎች በመልካም ባህሪ አዋቂነትሽን አሳያቸው።

አላህ በሰጠሽ እውቀት ላይ አመስጊኝ  ጭማሪን ታገኚ ዘንድ በተሰጠሽ ላይ አለማመሰገን አንድ ክህደት ነውና !!

وإذ تأذن ربكم لئن شكرتم لأزيدنكم ولئن كفرتم إن عذابي لشديد
ማወቅ ባለብሽ ነገር ላይ ጥረትን አድርጊ በጥረትሽ ላይ አላህ እንዲ ከፍትልሽ ዱዓ አድርጊ፣አስባቡንም  አድርሺ፣ስራሽን ፍፁም ለጌታሽ አጥሪ አላህ ለሱ ብሎ የታገሉትን አይጥልምና !

وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا
وَإِنَّ اللهَ لَمَعَ المُحْسِنِينَ
እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡

https://t.me/https_Asselefya1
➧ኢብኑ ተይሚያ የሱናዉ አንበሳ የሱንዮች መድረክ በቴሌግራም የሚተላለፉ ትምህርቶች ለመከታተል ከታች ባሉት አድራሻ ይቀላቀሉ!

↪️በግሩፓችን የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች፦

➲የአቂዳ ኪታቦች
➲የፊቅህ ግንዛቤዎች
➲የጥያቄና መልስ ውድድር
➲የሱና ኡለማዎች ፈትዋ

➲ወቅታዊ ምክሮች
➲የቁርአን ቂርአትና ሌሎችም
@IbnuTeymyaYesunawAmbesa
@IbnuTeymyaYesunawAmbesa

↪️በቻናላችን የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች

➲የአቂዳ ኪታቦች
➲የፊቅህ ግንዛቤዎች
➲የሱና ኡለማዎች ፈትዋ
➲ወቅታዊ ምክሮች

➲የቁርአን ቂርአትና ሌሎችም
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
➧ስራችን ሁለየ ለአላህ አጥርተን ከሰራን ምንግዜም ደስተኞች ነን። ነገር ግን የሰዉ ሙገሳ ፈልገን ለሰዉ ብለን ከሆነ ያ ሙገሳና ለሱ ብለን የሰራነዉ ዝም ሲሉን ሁለየ መጨናነቅ መጠበብ ነዉ። አደራ ስራን አጥርቶ በመስራት ላይ ነፍሳችንን እንታገል

✍️Binet Aragaw

https://t.me/https_Asselefya1
መውደድ የቻለ ልብ መጥላትም ይችላል !!
ነፍስህን በከንቱ አታስጨንቃት!
እንዲያልፍህ የተፃፈ አያገኝክም
ሊያገኝክ የተፃፈ አያልፍክም...!!


ስለዚህ ነፍስህን አታስጨንቃት ጭንቀትም በሺታ ነው።