💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
ኢእቲካፍ በምናደርግበት ጊዜ የተወደዱ ተግባሮች
➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛➛

ኢእቲካፍ ከሌሎች ጉዳዮች ራሱን አግልሎ መስጂድ ውስጥ የሚቆይበት ተግባር በመሆኑ በኢእቲካፍ ጊዜ ሰላት፣ ዚክር፣ ዱዓ (ፀሎት)፣ ቁርአን ማንበብ፣ ምህረትን መማፀንና ሌሎችንም አምልኳዊ ተግባራት በብዛት መፈፀም ይወደዳል::

ኢእቲካፍ ለሚፈፅም ሰው የተፈቀዱ ነገሮች
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭

➧ኢእቲካፍ ላይ ያለ ሰው ምግብ የማይቀርብለት ከሆነ ለመመገብ ለመፀዳዳት ለጀናባ ትጥበትና ውዱእ ለማድረግ ከመስጂድ መውጣት ይፈቀድለታል፡፡

እንዲሁም በጠቃሚ ጉደዮች ከሰው ጋር ማውራት የተፈቀደ ሲሆን ነገር ግን በማይጠቅሙ አሉባልታ ወሬዎች ጊዜውን ማጥፋት ከኢእቲካፍ ዓላማ ጋር ተፃራሪ ነው::ኢእቲካፍ በመፈፀም ላይ ያለን ሰው መጥቶ መጎብኘትና በአንዳንድ ጉዳዮች ማውራት እንግዳውንም ለመሸኘት መውጣት ይፈቀዳል፡፡ ሶፊያ ረድየሏህ ዐንሃ እንዲህ ብላለች

➧“ነቢዩ(ﷺ) ኢእቲካፍ ላይ ባሉበት በምሽት መጥቼ ሰላም ብዬ ትንሽ ካጫወትኳቸው በኋላ ስመለስ ለመሸኘት ተከትለውኝ ወጡ”::አልቡኻሪ (2ዐ35) ሙስሊም (2175)

ኢእቲካፍ ላይ ያለ ሰው የመስጂዱን ንፅህና ጠብቆ መስጂድ ውስጥ መመገብ መጠጣትና መተኛት ይችላል፡፡

ኢእቲካፍን የሚያፈርሱ ነገራቶች
➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱

➲ያለ ምክንያት ከመስጂድ መውጣት የኢእቲካፍ ዋናው መሰረት መስጂድ ውስጥ መቆየት በመሆኑ ያለምክንያት ትንሽ ለመቆየት ቢሆንም እንኳን ሆን ብሎ ከመስጂድ ውጭ መውጣት ኢእቲካፉን ያበላሻል:: አዒሻ ረድየሏህ ዐንሃ እንድህ ብላለች

➲“ነቢዩ(ﷺ) ኢእቲካፍ ላይ ሆነው ለጉዳይ እንጂ ቤት አይገቡም ነበር፡፡”አል ቡኻሪ (2ዐ29)

የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም የግብረ ስጋ ግንኙነት በሌሊትና ቤት ውስጥም ቢሆን ኢእቲካፍን ያፈርሳል፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፦

▪️وَلَا تُبَـٰشِرُوهُنَّ وَأَنتُمْ عَـٰكِفُونَ فِى ٱلْمَسَـٰجِدِ البقرة: ١٨٧

እናንተም በመስጊዶች ተቀማጮች ስትኾኑ አትገናኙዋቸው”፡፡አል-በቀራህ 187

ከግብረ ስጋ ግንኙነት ውጭ የዘር ፈሳሽ እንዲፈሰው ማድረግም ኢእቲካፍን ያፈርሳል::

የአእምሮ ጤና ማጣት በእብደት ወይም በስካር አእምሮን ማጣት ኢእቲካፍን ያበላሻል::

የወር አበባ ወይም የወሊድ ደም መምጣት ኢእቲካፍን ይበላሻል፡፡

ከእስልምና መውጣት፡- ከእስልምና መውጣት ስራን ሙሉ በሙሉ ያበላሻል። አላህ እንዲህ ብሏል፦

▪️لَئِنْ أَشْرَكْتَ لَيَحْبَطَنَّ عَمَلُك الزمر: ٦٥

“ብታጋራ ሥራህ በእርግጥ ይታበሳል” አል-ዙመር 65

ምንጭ፦አል ፊቅሕ ሙየሰር

🖊ام فاروق

ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
📚ቁርአን በረመዷን አብረንእናኽትም!


➡️ ጁዝ ሃያ ሁለት
⬅️الليلة(22) رمضان

🎙الشيخ علي الحذيفي حفظه الله

🎧ይቀጥላል ኢንሻ አላህ .........

https://t.me/https_Asselefya1
اللهمّ إنّكَ عفوٌ تُحب العَفو فَاعفُ عنّا.
▪️قال الإمام أحمد رحمه الله:

سامح أخاك
وما ينفعك أن يعذب الله أخاك المسلم بسببك.

📓سير أعلام النبلاء (٢٦٢/١١)
ያኢላሂ!!
➱➱➱➱

በኢማን ሙላን፣
በኢስቲቃማ አሳምረን፣
የሚጠቅመንን አሳውቀን፣
መንገድህን አመላክተን
ፍለጋህን አስተምረን።

اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عني
አሏህ ሆይ! አንተ ይቅር ባይ ነህ ይቅርታንም ትወዳለህ ይቅር በለኝ
ይችን ዱዐ አብዙ!!
➡️እስቲ ተጠየቅ

አስር ቁልፍ ተሰጥቶህ ከነዚህ ቁልፎች ውስጥ አንዱ በወርቅ፣ በብርና በዶላር የተሞላ የመጋዘን ቁልፍ ነው ከፍተህ የፈለከውን ውሰድ ብትባል ምን ታደርጋለህ?

ሀ】በግምት አንዱን ቁልፍ መርጬ ሌላውን እተዋለሁ
ለ】ሁሉንም አልፈልግም ብዬ እተዋቸዋለሁ
ሐ】ትክክለኛው ቁልፍ እስካገኝ አስሩንም እሞክራለሁ

♦️መልስህ ያለምንም ጥርጥር "ሐ" እንደሚሆን እገምታለሁ።

ለይለተል ቀድርም ልክ እንደዚሁ ምሳሌ ነው።

በአስሩ የረመዷን የመጨረሻ ቀናቶች ውስጥ ፈልገው ተብሎ አስር ቁልፍ ቀናቶች ተሰጥቶሀል።
አላህ ይህንን ታላቅ እድል ይወፍቅህ ዘንዳ በአስሩም ሌሊቶች ውስጥ ፈልጋት።

ወርቅና ብር እኮ ርካሽ የዱንያ ቁስ ናቸው። ለይለተል ቀድር ግን ከሰማንያ ሶስት አመት በላይ የሆነ ኢባዳ የምታገኝበት፣ ወንጀልህ የሚማርበት፣ የአላህ ውዴታ የምትሸምበትና ጀነት የመግቢያ ሰበብ ነው።

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#تــلاوات

﴿قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّى ۝ وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّى﴾

- «سُبْحَانَ اللهِ»
- «الحَمْدُ للهِ»
- «لَا إلَهَ إلَّا اللهُ»
- «اللهُ أكْبَرُ»
- «سُبْحَانَ اللهِ وَبِحَمْدِهِ»
- «سُبْحَانَ اللهِ العَظِيمِ»
- «لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إلَّا بِاللهِ»
- «أسْتَغْفِرُ اللهَ وَأتُوبُ إلَيْهِ»
- «لَا إلَهَ إلَّا أَنْتَ سُبْحَانَكَ إنِّي كُنْتُ مِنَ الظَّالِمِينَ»

https://t.me/https_Asselefya1
Audio
📚ቁርአን በረመዷን አብረንእናኽትም!


➡️ ጁዝ ሃያ ሶስት
⬅️الليلة(23) رمضان

🎙الشيخ علي الحذيفي حفظه الله

🎧ይቀጥላል ኢንሻ አላህ .........

https://t.me/https_Asselefya1