💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
◾️ክሪስማስ (ገና) ❌
➖➖➖➖➖➖➖

✅ የአይሁዶችና የነሷራዎችን አመት በአል ማክበርም ሆነ በበአሉ ላይ መገኘት እንደማይቻል ኢማሙ አህመድ ይህንን የቁርአን አንቀፅ እንደ መረጃ ጠቅሷል።
☑️ وَٱلَّذِينَ لَا يَشْهَدُونَ ٱلزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا۟ بِٱللَّغْوِ مَرُّوا۟ كِرَامًا
➡️ እነዚያም እብለትን የማይመሰክሩ፤ በውድቅ ቃልም (ተናጋሪ አጠገብ) ባለፉ ጊዜ የከበሩ ኾነው የሚያልፉት ናቸው፡፡ (ሱረቱል ፋርቃን 72)
📚مجموع الفتاوى لابن تيمية ٣٢٥/٢٥
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲የእውቀት ፍሬው ተግባር ነው ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➧ክፍል አምስት ➭➭➭➭➭➭➭➭ ▪️ሱፍያን ብን ዑየይናህ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡- "من فسد من علمائنا ففيه شبه من اليهود ، ومن فسد من عبادنا ففيه شبه من النصارى" ➧“ከዑለማዎቻችን የተበላሹት ከአይሁድ ጋር መመሳሰል አላቸው። ከዓቢዶቻችን(ያለጥልቅ እውቀት አላህን…
➲የእውቀት ፍሬው ተግባር ነው
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል ስድስት

➠በርካታ ሰለፎች የሚከተለውን ይናገሩ ነበር፡
"ليتني أنجو من علمي – يقصد من العلم الذي تعلمه – كفافا ، لا لي ، ولا علي"

“ለእኔም ሳይኖረኝ በእኔም ላይ ሳይኖር ከእውቀቴ (ሳልጠየቅ) ነጻ ብሆን እመኛለሁ፡፡”

➛በዚህም ፣ ሰለፎች የተስተካከለ እውቀትና ተግባር እያላቸው ምን ያክል አላህን እንደሚጠነቀቁና እንደሚፈሩ ያመላክታል፡፡

▪️ሀሰን አል'በስርይ -ረሂመሁሏህ- የሚከተለውን ተናግሯል፡-

"إن المؤمن جمع بين إحسان ومخافة ، والمنافق جمع بين إساءة وأمل"

✅“ሙእሚን መልካምንና ፍርሀትን አጣምሮ ይዟል፡፡ ሙናፊቅ ደግሞ ክፉ ስራንና መልካም ተስፋን አጣምሮ ይዟል፡፡” አዝ ዙህድ ሊብኒ አል ሙባረክ፡985

▪️ዓብደሏ ብን አቢ'ሙለይካ -ረሂመሁሏህ- ደግሞ የሚከተለውን ተናግሯል፡-
"أدركت أكثر من ثلاثين صحابيا كلهم يخاف النفاق على نفسه"

➤“ሁሉም ኒፋቅን በነፍሳቸው ላይ የሚፈሩ ከሰላሳ የሚበልጡ ሶሃቦችን አግኝቻለሁ፡፡”
ቡኻሪ በሶሂህ ታባቸው ኪታቡ አል ኢማን ባቡ ኸውፉል ሙእሚን ላይ በተዕሊቅ አውርትታል

➲ለአማኞች በአንድ ላይ ሁለት ታላላቅ ደረጃዎችን አጣምሮላቸዋል፡፡ በመልካም መታዘዝንና ያማረ ተግባርን እየሰሩ ስራችንን ከእኛ አይቀበልም ብለው አላህንእንዲፈሩ አድርጓቸዋል፡፡

▪️አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል

وَالَّذِينَ يُؤْتُونَ مَا آتَوا وَّقُلُوبُهُمْ وَجِلَةٌ أَنَّهُمْ إِلَىٰ رَبِّهِمْ رَاجِعُونَ

እነዚያም የሚሰጡትን ነገር እነርሱ ወደ ጌታቸው ተመላሾች መኾናቸውን ልቦቻቸው የሚፈሩ ኾነው የሚሰጡት፡፡አል ሙዕሚኑን 60

➲“እነዚህ አስካሪ መጠጥ የሚጠጡ ፣ ዝሙት የሚፈጽሙ ፣ የሚሰርቁ ናቸው?” በማለት ስለዚህ ቁርኣናዊ አንቀጽ ትርጓሜ ረሡልን صلى الله عليه وسلم ጥያቄ አቀረብኩላቸው ትላለች ዓኢሻ ረድየሏህ አንሃ ረሡልም صلى الله عليه وسلم፡ - “አይደለም፣ የ (አቡበክር) ሲዲቅ ልጅ ሆይ! ነገር ግን እየጾሙ፣ እየሰገዱ ፣ እየሶደቁ ከእነርሱ ይህን መልካም ስራችንን አላህ ላይቀበለው ይችላል ብለው ስጋት ያደረባቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች በመልካም የሚሽቀዳደሙ ናቸው፡፡” በማለት ምላሽ ሰጡ፡፡ አህመድ፡25263 ቲርሚዚይ፡ 3175ኢብኑ ማጀህ፡4198

✅አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናገረ፡

وَإِسْمَاعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا ۖ

“(ኢብራሂምና) ኢስማኢልም “ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡”
አል በቀራህ፡127

➧ውሀይብ ብን አልወርድ- ረሂመሁሏህ- ይህን የቁርኣን አንቀጽ አነበበና አለቀሰ፡፡ ከዚያም የሚከተለውን ተናገረ፡-

"يا خليل الرحمن ترفع قوائم بيت الرحمن وأنت مشفق أن لا يقبل منك!"

➭“የአላህ ወዳጅ (ኢብራሒም) ሆይ! የአላህን ቤት መሰረቶች ከፍ ታደርጋለህ፡፡
እንደገና ይህን ስራየን አላህ ላይቀበለኝ ይችላል ብለህ ትጨነቃለህ
፡፡” ተፍሲር ኢብኑ ከሲር፡1/206
◉
◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📚ዓብዱረዛቅ ብን ዓብዱልሙህሲን አል ዓባድ ኪታብ የተወሰደ በየሱፍ አህመድ የተተረጎመ

➭ጥሩ ፀሀፊ ባትሆን ጥሩ አንባቢ ሁን ትጠቀማለህ

➧ ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
ዚና የሰሩት አይሁዶች ታሪክ
Sheikh Muhammed Zeyn
➧ዚና የሰሩት አይሁዶች ታሪክ


🎙ሸይኽ ሙሀመድ ዘይን ሸይኽ አደም
Audio
♦️ تلاوة من سورة المؤمنون
♦️ القارئ: #صالح_الفالح
•••━══❁✿❁══━•••
✅ ማራኪ ቲላዋ
Audio
◾️ተከታታይ የቂርአት ፕሮግራም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➡️ ሸርህ አቂደቱል ዋሲጥያ የፈውዛን

➰ክፍል ③⑧➰
〰〰〰〰〰

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
🖋 قال العلامة ابن عثيمين رحمه الله :

أهم كتاب يعتني به طالب العلم كتاب الله عز وجل؛ لكن ليكن تلقيه لمعاني كتاب الله عز وجل من الكتب الموثوقة في التفسير التي قام بتأليفها علماء موثوقون في علمهم وفي دينهم وفي أمانتهم ، ثم بعد ذلك ما صح من أحاديث رسول الله صلى الله عليه وعلى آله وسلم .

📚 فتاوى نور على الدرب : (٢٣/٢).
አርበዒን 42ኛ ሐዲሥ
ኢብኑ/ሙነወር
↪️አድስ ተከታታይ የኪታብ ደርስ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖

↪️ አልአርበዑነ ነወዊያህ ከኢብኑ ረጀብ ጭማሬ ጋር

↪️ ሐዲሥ ቁጥር – 4⃣2⃣

🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Forwarded from MuhammedSirage M.Noor (MuhammedSirage MuhammedNoor)
ከአላህ ውጭ ሌሎች አካላት (ነቢያቶች ፣ ወሊዮች እና ሌሎችም ፍጡራን ) እንዲመለኩ ጥሪ የሚያደርግ በሙሉ መሃይም ነው!

ቁርአን ን ፣ ሐዲስን ፊቅህን እና በርካታ የዱንያ ትምህርቶችን አብዝቶ ቢያውቅና ቢሸመድድም እንኳን ፍጡራንን የሚመልክ ሁሉ መሃይም ነው!

قُلْ أَفَغَيْرَ ٱللَّهِ تَأْمُرُوٓنِّىٓ أَعْبُدُ أَيُّهَا ٱلْجَٰهِلُونَ
«እናንተ መሃይማን ሆይ! ከአላህ ሌላን እንድግገዛ ታዙኛላችሁን?» በላቸው፡፡
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➭መንዙማ ➫➫➫➫➫ ➧ክፍል ሰላሳ አራት 〰〰〰〰〰〰 ➲ነብዩ (صلى الله عليه وسلم (ወደመቃብር ከገቡ በኋላ ይህን የማድረግ ስልጣኑ አላቸውን? በጭራሽ!! ስልጣን እና ድርሻ የላቸውም። አለምን ማስተናበር ህያው የሆነው የማይሞተው አላህ ስልጣን ብቻ ነው። ➴“የፍቅር ነጋሪ ዝም ብየ ልምጣ፣ እባካችሁ ይቅር ሌላው ሀተታ፣ ጠዋትም ማታ ጀበል ወትውቱ (አጥብቃችሁ ጠይቁ)”…
➲መንዙማ
➫➫➫➫➫

➭ክፍል ሰላሳ አምስት
➛➛➛➛➛➛➛➛

➧ይኸው ለምነናል በቴሌ ግራሙ ግቡልን”
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➻ከደካማ ፍጡር ዘንድ የሚያፈጥ አካል ከለማኝ ፊት እንደቆመ ለማኝ ነው።ተለማኙ የማይሰማ የማይለማ፣ በቀብር ያውም በሩቅ ያለ ሙት ሲሆንስ? አሳዛኝ ነው።ጥሪን የሚሰማ፣ ተማፅኖን የሚቀበል ጌታ እያለ ይህን ያክል ከደካማ ፍጡሮች ያውም ከማይሰሙ ጋር ይህን ያክል ሙጭጭ ማለት ክፉ በሽታ ነው። በብቸኝነት ሊለመን የሚገባው አላህ ብቻ ነበር። ባርያዎቹ ሲለምኑትም መልስ የሚሰጠው እሱ ብቻ ነውና።

አላህ እንዲህ ይላል፡

وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ

“ጌታችሁም አለ ለምኑኝ እቀበላችኋለሁ።” [ጋፊር፡ 60]

➭በጅምላም ይበሉት በችርቻሮ ከአላህ ውጭ የሚለመኑት ምንንም መስጠትም
ሆነ መከልከል አይችሉም።ነፍሱ ላይ ጨክኖ ከአላህ ውጭ እያመለከ
“አትጨክኑብን” እያለ መጮሁ
ይገርማል።

➴➴“ግቡልን በማለት ጠራ መሀይሙ፣
አንተን በመውደዱ ሄደለት ህመሙ፣
ልቡ ተሸበረ እንዳየህ በህልሙ፣
አንተ ነህ ፀሎቱ ስግደትና ፆሙ፣
መወትወት ጀመረ ቢፈላበት ደሙ”


➧እኛ ስግደታችንን፣ እርዳችንን፣ ህይወታችንን እናም ሞታችንን የነብዩም صلى الله عليه وسلم ይሁን የሌሎች ፍጡራን ጌታ ለሆነው ለአንድ አምላክ አላህ ብቻና ብቻ በእርሱም ላይ ማንንም ሳናጋራ እንድንገዛው ነው የታዘዝነው።

የፍጡራኑን ጥሪ ሰሚ አላህ ብቻ ነው።
ከአላህ ውጭ ያሉትን ማንንም ይሁን ማን ቢወተውቱት ምንም መስጠጥም ሆነ
መከልከል አይችልም።

➴➴ “ሰላም አለይኩም ነቢ ያሰይደል አለሚን ፣
እያዩ መባዘኔን ምነው ጨከኑ በእኔ”

➧ነብዩ صلى الله عليه وسلم የሱን መባዘን አያዩም። አያውቁምም። እሳቸውን በመጣራቱም ከጌታው ጋር የሚያጣላው ትልቁ ሺርክ ላይ ከመውደቁ ውጭ የሚያተርፍለት ነገር የለም። እሳቸውን “ጨከኑብኝ” እያሉ ማናገርም አደበ ቢስነት ነው። “ያላዋቂ ሳሚ ንፍጥ
ይለቀልቃል።”


➧ በጭንቀት ጊዜ ማንን ይለምናሉ?
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➠የድሮዎቹ አጋሪያን የሚታወቁት በሰላሙ ጊዜ በማጋራት እና በጭንቀት ጊዜ ለአላህ ሃይማኖትን ያጠሩ ሲሆኑ እሱን በብቸኝነት በማምለክ ነበር።

فَإِذَا رَكِبُوا فِي الْفُلْكِ دَعَوُا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ فَلَمَّا نَجَّاهُمْ إِلَى الْبَرِّ إِذَا هُمْ يُشْرِكُونَ

“በመርከቦች ውስጥ በተሳፈሩ ጊዜም አላህን መገዛትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው ይጠሩታል። ወደ የብስ (በማውጣት) ባዳናቸው ጊዜም ወዲያውኑ እነርሱ (ጣዖትን) ያጋራሉ።”
[አልዐንከቡት፡ 65]

➛የዛሬዎቹ አጋሪያን ግን በሰላሙም በችግሩም ጊዜ በአላህ ላይ ያጋራሉ። በዚህ ንኡስ ክፍል ላይ ይህንን እውነታ የሚያሳዩ የመንዙማ ስንኞችን እንመለከታለን፡-

➴➴ሪጃለላህ ያሪጃለላህ፣
የአህለል በይቲ አጊሱና ቢላህ
”

➧ትርጉሙም፡- “እናንተ የአላህ ወንዶች ሆይ! እናንተ የአላህ ወንዶች ሆይ!
የነብዩ ቤተሰቦች ሆይ! በአላህ ይሁንባችሁ ከዚህ ጭንቀታችን ገላግሉን።”

➴➴“ያ ረሱለላህ አል መደድ”

ትርጉሙም፡- “አንቱ የአላህ መልክተኛ ሆይ! እርዳታዎትን።”

➴➴ “ሰላሚ አላ ገውሰል ዒባዲ፣
ዳኢመን ቢላ ዐደዲ”
ትርጉሙም፡- “የባሪያዎች የጭንቅ ገላጋይ የሆናችሁት ሆይ! ሰላም በናንተ ላይ ይሁን። ዘወትር ስፍር ቁጥር የሌለው።”

➴➴ “አጊሱና ገውሱ፣ አሊዩል ጎንደሪ”
ትርሙም፡- “የጭንቅ ገላጋይ የሆኑት አሊዩል ጎንደሪ ሆይ! ከጭንቀት ገላግሉን።”

◉
◉
◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📚መንዙማ ከሚለው ከሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

አንብብ ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል

➛ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
‏القارئ حمزة معاذ | ما تيسر من سورة الأعراف | رمضان 1440 هـ -…
♦️ تلاوة من سورة الأعراف
♦️ القارئ: #حمزة_معاذ
•••━══❁✿❁══━•••
✅ ማራኪ ቲላዋ
✅ የቁርአን ግብዣ
18 Al-Kahf
Abdul Wadood Haneef
📖سورة الكهف
ሱረቱል ከህፍ ⤴️⤴️⤴️

🎙 ቃሪዕ _አ/ወዱድ ሀኒፍ

📌((قَالَ رَسُولَ اللَّهِ ﷺ من قرأ سورةَ الكهفِ في يومِ الجمعةِ ، أضاء له من النورِ ما بين الجمُعتَين))

💢የአሏህ መልዕክተኛﷺእንዲህ ብለዋል፦ ((የጁምዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን የቀራ ሰው አሏህ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል ብርሃንን ያበራለታል)
1- ክርስቲያን ጎረቤት ቢታመም መጠየቅ ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ነብያችን ﷺ የታመመን የሁዲ ጠይቀዋል። [ቡኻሪ፡ 1356]
2- የክርስቲያንን የግብዣ ጥሪ መቀበል ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ነብዩን ﷺ አንድ የሁዲ ጠርቷቸው ሄደዋል። [አሕመድ፡ 13201]
3- ክርስቲያን የሆነ ሰው ቤተሰብ ቢሞትበት ለተዕዚያ ወይም ለማፅናናት መሄድ ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ከላይ የተጠቀሱት መረጃዎች ለዚህ ድጋፍ መሆን ይችላሉ።
4- ለክርስቲያን ደሃ ሶደቃ መስጠት ይቻላል?
አዎ ይቻላል። [ቡኻሪና ሙስሊም]
5- በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ለክርስቲያን መልካም መዋል ይቻላል?
አዎ ይቻላል። [አልሙምተሒናህ፡ 8-9]
6- ለገና በዓል "እንኳን አደረሳችሁ" ማለት ይቻላል?
በፍፁም!
ከላይ የተዘረዘሩት የሚፈቀዱ ከሆነ ይሄኛው የሚከለክልበት ምክንያት ምንድነው?
የመጀመሪያዎቹ ነገሮች የተፈቀዱት እምነታዊ ሳይሆን ዱንያዊ ጉዳዮች ስለሆኑ ነው። ሃይማኖታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ግን ይሄ የሚፈቀድ አይደለም። በቃልም በተግባርም ማጀብ አይቻልም፡፡ የአላህ ነብይ ዒሳን ጌታ አድርጎ ሲገልፅ፣ ከዚያም "ጌታ ተወለደልኝ ብሎ ሲደሰት" እንኳን ጌታ ተወለደልህ!" ትላለህ? የእምነታችን አንዱ መሰረትኮ "አላህ አልወለደም፣ አልተወለደም" ነው። በሌሎች ሃይማኖታዊ በአላትም ወይም ድግሶችም ላይ እንዲሁ ነው። እና ወንድሜ! የእምነትህን ህግ ለመጠበቅ ፈፅሞ ወኔ አይጠርህ። ጓደኝነት፣ ትውውቅ ሸብቦህ፣ አጉል እፍረት አስሮህ ከጌታህ ጋር አትጣላ። በነገራችን ላይ ይሄ "የጌታ መውሊድ" ብለው የሚያከብሩት የገና በአል መፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኝ በቅድመ-ክርስትና ከነበረው የጣኦታውያን እምነት የተኮረጀ ነው። በዚያ ላይ ዛሬ የጎርጎሮሳዊውን አቆጣጠር የሚከተሉት የሚያከብሩበት December 25ም ሆነ "የኢትዮጵያውን" አቆጣጠር የሚከተሉት የሚያከብሩበት ታህሳስ 29ም በርግጠኝነት ዒሳ (እየሱስ) የተወለዱበት ቀን አይደለም።
-
መነሻ ሃሳቡ ዋትሳፕ ላይ ያገኘሁት 0ረብኛ ፅሁፍ ነው።
==
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲አትራፊ የንግድ ማዕከላት ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➛ክፍል አራት ➻➻➻➻➻➻ ➧“ሙስነድ ኢማም አህመድ” ኪታብ ላይ በራእ ብን ዓዚብ ረድየላህ አንሁ ካስተላለፈው ረጅም ሐዲስ ውስጥ የሚከተለው የረሡል صلى الله عليه وسلم ንግግር ይገኝበታል፡- ▪️"ويأتيه رجل حسن الوجه حسن الثياب طيب الريح، فيقول: أبشر بالذي يسرك هذا يومك الذي…
➲አትራፊው የንግድ ማዕከላት
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል አምስት
➭➭➭➭➭➭➭➭

➠ይህ አትራፊ የሆነው ንግድ እንጅ ተወጋጅ ፣ ከሳሪ ፣ ጸጋዋና መልካሟ የሚቋረጥ ፣ባለቤቷ በቅርብ እርሷን ትቷት የሚጓዝ የሆነችው ዱንያ ንግድ አይደለም፡፡ባሪያው ከዚህ ከሳሪ የንግድ ውልና ቃልኪዳን ባለቤቶች ሊጠነቀቅ ይገባል፡፡

▪️ኢማም አሽ'ሻጢቢይ ረሂመሁላህ ዑለሞች ለዚህ ጉዳይ ምሳሌ እንዳደረጉ ገልጸዋል፡- እድሜ የተሰጠው ሰው “ረእሰል ማል” (አንጡራ ሐብት) አላህ ሰጦታል፡፡ ይህ አንጡራ ሐብት በዱንያ ላይ አንድም የማይመዝነው ወይም አንድም እርሱን የማይተካ እንቁ የሆነ ሐብት ነው፡፡ “የሰው ልጅ አንጡራ ሐብቱ እድሜውና ሰዓታቱ ነው፡፡ ይህ ሐብት ፣ የሰው ልጅ ከተሰጠው ነገር ሁሉ ውድ የሆነው ሐብት ነው፡፡ ይህን ውድ የሆነ
ሐብት አላህ - ሱብሃነሁ ወተዓላ - በከሐዲዎች ላይ እንደሚከተለው ትልቅ ማስረጃ አድርጎ አቅርቦታል፡፡


➧አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

أَوَلَمْ نُعَمِّرْكُم مَّا يَتَذَكَّرُ فِيهِ مَن تَذَكَّرَ

➭“በእርሱ ውስጥ ያስታወሰ ሰው የሚገሰጽበትን ዕድሜ አላቆየናችሁምን?
አስጠንቃቂውም መጥቶላችኋል፡፡” ፋጢር፡37

➲እድሜ የተሰጠው አዋቂና ጮሌ (ብልህ) የሆነ ሰው ይህን አንጡራ ሀብት -እድሜውን ፣ ሰዓቱን ፣ ቀናቶቹን - አላህ ለሚወደው ነገር እንዴት መጠቀም
እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ሰከንዶች ፣ ቀናቶች ፣ ሌሊቶች ፣ ደቂቃዎች በማይረባ
ነገር ወይም ከአላህ ትዕዛዛ ውጭ እንዳይባክኑ ይጠነቀቃል፡፡ ወቅቱን አላህን በመታዘዝላይ ያሳልፋል፡፡


➧ ወቅቱን ለሶላት ፣ ለሐጅ እና ለመሳሰሉ አላህ ለሚወዳቸው ተግባራት ባማረ ሁኔታ ያውለዋል፡፡ ክፍት የሆኑ ወቅቶችን ሀራም ነገሮችን ከመፈጸም ይቆጠባል፤ በእነዚህ ወቅቶች አላህን ይፈራል፡፡ በቻለው ያክል መልካም ነገሮችን ያበዛል፡፡

➧ይህን አንጡራ ሐብቱን በመልካም ነገር በመጠቀም ከዓለማት ጌታ ጋር አትራፊ ንግድ ከነገደ የማይጠፋና ዘውታሪ የሆነ ሀብት ባለቤት ይሆናል፡፡ ሁረል አይንን ያተርፋል ፤ ጀነቶችን ያተርፋል ፤ የጀነት አገልጋይ ወጣቶችን (ዊልዳኖችን) ያተርፋል ፤ ያለቁጣ ከጌታው መጎራበትን ያተርፋል ፤ የተከበረውን የአላህን ፊት መመልከትን ያተርፋል፡፡

➧ይህን አንጡራ ሐብት ማንቀሳቀስን አላህ - ሱብሃነሁ ወተዓላ - (በይዕ) ፤
(ሽራእ) ፤ (ቲጃራ) እና (ቀርድ) በሚሉ ስያሜዎች ሰይሞታል፡፡ምክንያቱም የዚህ አንጡራ ሀብት ባለቤት -የእድሜውን ቀናቶች- ባማረና በተስማማ ሁኔታ አንቀሳቅሶታል፡፡


▪️በዚህ ምክንያት አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا هَلْ أَدُلُّكُمْ عَلَىٰ تِجَارَةٍ تُنجِيكُم مِّنْ عَذَابٍ أَلِيمٍ

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከአሳማሚ ቅጣት የምታድናችሁ የሆነችን ንግድ
ላመላክታችሁን?”
(በላቸው) አስ ሶፍ፡10

➧ይህ ከአላህ ጋር የሚደረግ ንግድ እንደሆነ ግልጽ አደረገ፡፡

يَرْجُونَ تِجَارَةً لَّن تَبُورَ

“በፍጹም የማትከስርን ንግድ ተስፋ ያደርጋሉ፡፡” ፋጢር፡29

۞ فَاسْتَبْشِرُوا بِبَيْعِكُمُ الَّذِي بَايَعْتُم بِهِ ۚ وَذَٰلِكَ هُوَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ

“አላህ ከምእመናን ነፍሶቻቸውንና ገንዘቦቻቸውን ገነት ለእነርሱ ብቻ ያላቸው በመሆን ገዛቸው… በዚያም በተሻሻጣችሁበት ሽያጫችሁ ተደሰቱ፡፡ ይህም እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡” አት ተውባ፡111

مَّن ذَا الَّذِي يُقْرِضُ اللَّهَ قَرْضًا حَسَنًا فَيُضَاعِفَهُ لَهُ أَضْعَافًا كَثِيرَةً ۚ

“ያ ለአላህ መልካም ብድርን የሚያበድርና ለእርሱ (አላህ) ብዙ እጥፎች
አድርጎ የሚያነባብርለት ማነው?
” አል በቀራህ፡245
◉
◉
◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📚ዓብዱረዛቅ ብን ዓብዱልሙህሲን አል ዓባድ ኪታብ የተወሰደ በየሱፍ አህመድ የተተረጎመ

➧አንብብ! ያነበበ ተጠቀመ ።በጣም ቆንጆ መፅሃፍ ናት አብባችሁ ተጠቀሙበት ሀቂቃ እውነተኛ ንግድ ማለት በዱኒያ ላይ ያለው ሰይሆን ሀያል ከሆነው ጌታችን ጋር ያለን ግንኙነት ምን አይነት ነው? ሁላችንም እራሳችንን እንጠይቅ!? ✍

ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ ይጠቀማሉ ለሌሎችም ሺርርር አድርጉላቸው
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Audio
◾️ዘረኝነት ጥምብ ናት ተዋት

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲መንዙማ ➫➫➫➫➫ ➭ክፍል ሰላሳ አምስት ➛➛➛➛➛➛➛➛ ➧ይኸው ለምነናል በቴሌ ግራሙ ግቡልን” ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➻ከደካማ ፍጡር ዘንድ የሚያፈጥ አካል ከለማኝ ፊት እንደቆመ ለማኝ ነው።ተለማኙ የማይሰማ የማይለማ፣ በቀብር ያውም በሩቅ ያለ ሙት ሲሆንስ? አሳዛኝ ነው።ጥሪን የሚሰማ፣ ተማፅኖን የሚቀበል ጌታ እያለ ይህን ያክል ከደካማ ፍጡሮች ያውም ከማይሰሙ ጋር ይህን ያክል…
➧መንዙማ
➬➬➬➬

➲ ክፍል ሰላሳ ስድስት

➩አንዳንዶች የዚህ ስንኝ መልእክቱ “በቂያማ ቀን ስለሚኖረው ትልቁ ሸፈዐ እንጂ እነሱ በአሁኑ ሰዓት ድረሱልን እያሉ አይደለም” ይላሉ፡፡ ለዚህ የሚሰጠው መልስ፡-

➲በመጀመሪያ ነገር የሚሉት ነገር ውሸት ነው፡፡ እንኳን ነብዩን እና ሌሎች ስንት ፍጡሮችን እየተማጸኑ አይደለምን?

➧እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ፍጡሮችን ለዱንያዊ ጭንቅና ችግሮች የሚማፀኑባቸው በርካታ ስንኞችን እዚሁ መፅሐፍ ላይ ተመልክተናል፡፡

3. በተረፈ ሸፈዐውም ቢሆን ዛሬ ዱንያ ላይ እያለን የምንጠይቀው አላህን ብቻ ነው፡፡

➳ገውሱን ተድራ ገውስ ወልዳ ነገሰች፣
ኑሩን በኑሩ ላይ ደራርባ ለበሰች”
በመጀመሪያው ላይ ገውስ ተብለው የተገለፁት (የቃጥባሪ ሸይኽ) ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ አቡል ጀበልን ነው። ገውስ ማለት የጭንቅ ገላጋይ ማለት ነው። የጭንቅ ገላጋይ ደግሞ አላህ ብቻ ነው።
ኢስቲጋሳ ማለት ደግሞ በጭንቅ ጊዜ የሚደረግ ፀሎት ማለት ነው። በጣም የሚያሳዝነው ነሷራዎች እንኳን መርየምን “የጭንቅ አማላጇ” እንጂ የጭንቅ ገላጋዩዋ አላሏትም።

➧ነብዩ (صلى الله عليه وسلم) በድር ዘመቻ ላይ በጠላት ተከበው ጭንቅ ብሏቸው የጭንቀት ዱኣ አላህን ለመኑት። አላህም መልስ ሰጣቸው፡-

إِذْ تَسْتَغِيثُونَ رَبَّكُمْ فَاسْتَجَابَ لَكُمْ أَنِّي مُمِدُّكُم بِأَلْفٍ مِّنَ الْمَلَائِكَةِ مُرْدِفِينَ

➩ ከጌታችሁ ርዳታን በፈለጋችሁ ጊዜ «እኔ በሺህ መላእክት ተከታታዮች ሲኾኑ እረዳችኋለሁ» ሲል ለናንተ የተቀበላችሁን (አስታውሱ)፡
፡ [አልአንፋል፡ 9]

أَمَّن يُجِيبُ الْمُضْطَرَّ إِذَا دَعَاهُ وَيَكْشِفُ السُّوءَ وَيَجْعَلُكُمْ خُلَفَاءَ الْأَرْضِ ۗ أَإِلَـٰهٌ مَّعَ اللَّهِ ۚ قَلِيلًا مَّا تَذَكَّرُونَ

➲ ወይም ያ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል፣ መከራንም የሚያስወግድ፣ በምድርም ላይ ምትኮች የሚያደረጋችሁ፤ (ይበልጣልን ወይስ የሚያጋሩት) ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን ጥቂትንም አትገሰፁም።
” [አንነምል፡ 62]

➳ምልጃን ከማን እንጠይቅ?
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

በቅድሚያ ሊታወቅ የሚገባው ነገር ቢኖር ምልጃ ሁሉ የአላህ መሆኑ ነው። በመቀጠል አማላጆች ለተማላጆች ማማለድ የሚችሉት አላህ ለአማላጅ እንዲያማልድ ሲፈቅድለት ለተማላጅም እንዲማለድለት ሲወድለት ብቻ ነው። ይህን ምልጃ ዱንያ ላይ የሚጠየቀው በቀጥታ አላህ ብቻ ነው። ከአላህ ውጭ ያለን አካል ነብይም ይሁን መላኢካ ምልጃን መጠየቅ ሺርክ ነው። ምክንያቱም ይሄ እነሱን መለመን ነውና። ልመና ወይም ዱዓእ ደግሞ ዒባዳ ነው። ዒባዳን ለሌላ መስጠት ደግሞ ሺርክ ነው።

➲ ከዚህ በታች የምታነቡት የአገራችን መንዙማዎች ይሄው ከአላህ ሌላ በቀጥታ ነብዩ ሙሐመድን (صلى الله عليه وسلم) አማላጅ ሁኑን ሲሉ በአላህ ላይ የሚያጋሩበት ነው።"ያረሱለላሂ ሸፈዐ ይሁኑና፣ የቢላል እኮ ነን በዲኑ የፀና” እባኮት ሙሂየ:ሁኑልኝ ሸፈአየ።”

➲ ከአላህ ውጭ መመኪያ አለን?
በአላህ ላይ መመካት የአምልኮ ቁንጮው ነው። አላህ የሁሉ መጠጊያ ነው።

رَّبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَاتَّخِذْهُ وَكِيلًا
➳ (እርሱም) የምሥራቅና የምዕራብ ጌታ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ መጠጊያ (መመኪያ) አድርገህም ያዘው።
” [አልሙዝዘሚል፡ 9]

ባለመንዙማዎች ጋር ያለው ግን ሌላ ነው። ጥቂት ምሳሌ እንመልከት፡-

➩አንቱ የገደፉት ማን ነው የወደቀው?” ያቀመረል መካ አሰላሙ አለይካ፣ልቤ ባንቱ በእርሶ ተመካ”
ነብዩ صلى الله عليه وسلم በጠላት ተከበው ከፊታቸው ብዙ አደጋ በተደቀነበት ሰኣት እንዲህ ሲሉ መለሱ:-

الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ

➳እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው «በቂያችንም አላህ ነው ምን ያምርም መጠጊያ!» ያሉ ናቸው
፡፡[ሱረቱ አሊ-ዒምራን -173]

وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ وَسَبِّحْ بِحَمْدِهِ ۚ وَكَفَىٰ بِهِ بِذُنُوبِ عِبَادِهِ خَبِيرًا

በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ ከማመስገንም ጋር አጥራው፡፡ በባሮቹ ኀጢኣቶችም ውስጠ ዐዋቂ በእርሱ በቃ።” [አል ፉርቃን፡ 58]

➧እነዚህ መንዙማ ባዮች ህያውን ፈጣሪን ትተው የሞቱት ነብዩ ሙሐመድን(صلى الله عليه وسلم)በአላህ ላይ ባላንጣ አድርገው ታላቁን መመካት የተባለውን አምልኮ አሳልፈው ይሰጧቸዋል። ይህ ታላቅ በደል ነው። አሳዛኙ ይህ አጥፊ መንዙማ በብዙ ሙስሊም ቤት የኢስላም አካል እየመሰላቸው ህፃናት ሳይቀሩ ሲያቀነቅኑት ይታያል።
◉

◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📚መንዙማ ከሚለው ከሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

አንብብ ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል

➛ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️ተከታታይ የቂርአት ፕሮግራም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➡️ ሸርህ አቂደቱል ዋሲጥያ የፈውዛን

➰ክፍል ③⑨➰
〰〰〰〰〰

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
አርበዒን 43ኛ ሐዲሥ
ኢብኑ/ሙነወር
↪️አድስ ተከታታይ የኪታብ ደርስ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖

↪️ አልአርበዑነ ነወዊያህ ከኢብኑ ረጀብ ጭማሬ ጋር

↪️ ሐዲሥ ቁጥር – 4⃣3⃣

🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
ወጣቶች ሆይ!
"አግቡ፣ አግቡ፣ አግቡ
"

#ትዳርን የመሰለ ነገር የለም!
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➧መንዙማ ➬➬➬➬ ➲ ክፍል ሰላሳ ስድስት ➩አንዳንዶች የዚህ ስንኝ መልእክቱ “በቂያማ ቀን ስለሚኖረው ትልቁ ሸፈዐ እንጂ እነሱ በአሁኑ ሰዓት ድረሱልን እያሉ አይደለም” ይላሉ፡፡ ለዚህ የሚሰጠው መልስ፡- ➲በመጀመሪያ ነገር የሚሉት ነገር ውሸት ነው፡፡ እንኳን ነብዩን እና ሌሎች ስንት ፍጡሮችን እየተማጸኑ አይደለምን? ➧እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ፍጡሮችን ለዱንያዊ ጭንቅና ችግሮች የሚማፀኑባቸው…
➲መንዙማ
➫➫➫➫➫

➧ክፍል ሰላሳ ሰባት

➲ስንታመም የሚያድነን ማን ነው?
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➠የሚከተለው የሺርክ መንዙማ ደግሞ በጉራጊኛ ቋንቋ ከአላህ ውጭ አቡል ጀበል የሚባለው ግለሰብ የእግርም ሆነ የእጅ ቁስላችንን ያድነናል ብለው የሚያምኑበት እና እሱን ሰውየውን በቀጥታ የሚለምኑበት ነው።

➴➴“አቡል ጀበል ሺሊላህ አቡል ጀበል ሺሊላህ፣
አሁን ትሆኝ እና መላ፣

➧የእግርም ጭዛ የእጅም ጭዛ (የእግርም የእጅም ቁስላችንን አዳኝ) አሁን ትሆኝ እና መላ (እናንተ ናችሁ የምታሽሩኝ
)”

➭የሚከተሉትም በአማርኛ መንዙማ ስንኞች ከአላህ ውጭ በሺታን ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲያድኑ አድርገው ያቀረቡበት ነው ።

➴➴ “መሻር ባንቱ ነው ያደዋኡና፣
ያምስኪ መዲና ጋየተል ሙና”።
“የጀሊል ባለሟል የሆኑት ሃቀኛ፣
ምነው ብታሽረው ያንን በሽተኛ፣
ሙሃባው ተነጥቆ የሆነ ደመኛ፣ ሀቢቢ ሀቢቢ ሀቢቢ”


➧አላህ ፍጹም ወዳጅ አድርጎ የያዛቸው ኢብራሂም (ዐለይሂ-ስሰላም) ግን አላህን አስመልክተው ለአጋሪያን ሲየስረዱ እንዲህ ይላሉ


الَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهْدِينِ⓼⓻وَالَّذِي هُوَ يُطْعِمُنِي وَيَسْقِينِ ⓽⓻وَإِذَا مَرِضْتُ فَهُوَ يَشْفِينِ ⓪⓼وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ ⓵⓼وَالَّذِي أَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لِي خَطِيئَتِي يَوْمَ الدِّينِ⓶⓼رَبِّ هَبْ لِي حُكْمًا وَأَلْحِقْنِي بِالصَّالِحِينَ⓷⓼

“(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው። እርሱም ይመራኛል። ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው። በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል። ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው። ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው። ጌታዮ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ።”

[አሽሹዐራእ፡ 78 _83]

➧ በአላህ እና መልክተኛው ላይ መዋሸት
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➭በአላህ እና በመልክተኛው ላይ መዋሸት ከባድ ወንጀል ነው። እስልምና ሃይማኖት የተገነባው ከአላህ ቃል ቁርኣን፣ ከነብዩ ሙሐመድ صلى الله عليه وسلم ሀዲሶች ነው። ስለዚህ አላህ እና መልክተኛው صلى الله عليه وسلم ያላሉትን ብለዋል ብሎ ማውራት በተለይ እንዲህ
የሀይማኖት ሰዎች ናቸው እየተባሉ አላህ እና መልክተኛው صلى الله عليه وسلم ላይ መዋሸት ኢስላምን መናድ እና ሙስሊሞችን ማወናበድ እና እምነታቸውን ማጭበርበር ነው።

➠ጥቂት ለትዝብት ያክል፡-
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴

“መጀን በኑር ሁሴን በአሩሲው ኑር፣
የአውሉያዎቹ ሻምበል የበርም የባህር፣
ከራማው ይፋ ነው አይደለም መስቱር
እጣው እንደ ነቢይ በርዳዳው ገበር፣
የሪጃሎች አባት የነዚያ ያብራር፣
የነአህመድ ኑረላህ ዚልፈይዲል ሚድራር፣
ተብሏል አላህ ዘንዳ በሻሀው አብሽር፣
ጌታየ ኑር ሁሴን በለኝ የኔ አሽከር፣
በዱንያ በአኼራም እንዳልቸገር፣
በናንተ የሸሸ እንዲሁም አይቀር፣
አላህ ሰጥቷቸኋል ሳይሰፍር ሳይቆጥር
።”

➴➴“ሸህ መሀመድ ፈቂህ ባለመነጠር፣
የታደለው ገበር ከአላህ ዘንዳ ሲር”
“ለካ ገረዋ ላይ አብርቷል ጀምበር፣
ሲፈቱ መለኪይ ዛቱ የበሸር፣
ተብሎ አላህ ዘንዳ በሺር ወአንዚር፣
ጎራ እማይጋርደው ይዟል መነጠር፣
ይናገር ነበረ የዟሂር የሲር፣
ይገልጠው ነበረ የኸልቁን ኸጢር”
“ለገሂዳም ጃማ ስንቱ ጉድ ነበር፣
እነ ነብዩ ሀድራ የተባሉ አብሽር፣
ባልከው ይሁን ያለው ገና ሲፈጠር
።
◉
◉
◉
◉✍ኢንሻአላህ ይቀጥላል

📚መንዙማ ከሚለው ከሳዳት ከማል ኪታብ የተወሰደ

አንብብ ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል


➛ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀሉ
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
قُل لَّن يُصِيبَنَا إِلَّا مَا كَتَبَ اللَّهُ لَنَا هُوَ مَوْلَانَا ۚ وَعَلَى اللَّهِ فَلْيَتَوَكَّلِ الْمُؤْمِنُونَ

«አላህ ለኛ የጻፈልን (ጥቅም) እንጂ ሌላ አይነካንም፡፡ እርሱ ረዳታችን ነው፡፡ በአላህ ላይም ምእመናን ይመኩ» በላቸው፡፡አል ተውባህ 51