💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
💦አል-ሓሪስ ኢብን ዓሲም አል-አሽዓሪይ እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ።

▪️“ጡሃራ (ንጽህና)የኢማን ግማሽ ነው።
▪️ አልሓምዱሊላህ (ምስጋና ለአላህ ነው)ሚዛን ትሞላለች።
▪️ ሱብሓነላህ ወልሓምዱሊላህ (አላህ የጠራ ነው እና ምስጋና ለአላህ ነው)በሰማይና በምድር መካከል ያለውን ይሞላሉ ወይ ትሞላለች።

▪️ሶላት ብርሃን ነው።
▪️ሰደቃ ማስረጃ ነው።
▪️ትእግስትም ብርሃን ነው።
▪️ቁርአንም ላንተ ወይንም ባንተ ላይ ማስረጃ ይሆናል።
↪️ሁሉም ሰዎች ይማልዳሉ ነፍሶቻቸውን ይሸጣሉ አንዳንዶቹ ነፍሶቻቸውን ነጻ ያወጣሉ፥ አንዳንዶቹ ደግሞ ነፍሶቻቸውን ያጠፋሉ።

📚(ሙስሊም ዘግቦታል።)

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
የሰለፍያ ጎዳና ትክክለኛው ጎዳና ናት
ኢብኑ ተይሚያ ረሂመሁሏህ

መጅሙዕ አል ፈታዋ 99/10
➲ያኦኽቲል ጋሊያህ ባለቤትሽን ስለ መልካምነቱ ማመስገንሽ ፍቅራችሁን ከማጎልበቱና እሱን ለበለጠ መልካምነት ከማበረታታቱ ባሻገር አላህን ማስደሰት ነው!!

قال صلى الله عليه وسلم : (لا ينظر الله إلى امرأة لا تشكر لزوجها و هي لا تستغني عنه) رواه النسائي و صححه الألباني في الصحيح 289

➧የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል

«ከባሏ የማትብቃቃ ስትሆን ባሏን የማታመሰግን ሴት፣ አላህ በእዝነት አይኑ አይመለከታትም።”
➳ኢማሙ ነሳኢ ዘግበውታል፤ አልባኒም ሰሒህ ብለውታል

➧እናማ ኦኽታየ ባለሺ ነገር ተብቃቂ የዱኒያ ጥቅማ ጥቅም አያታልሺ የሙዕሚን ሀገር ዱኒያ አይደለችም!!! ለዲኒያ ብለሺ አኼራሺን እንዳታበላሺ እንትብሂ!

🖊የፋሩቅ ማም

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➢ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ" ➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯ ➳ክፍል አስር ➽በቀደር የማመን ደረጃዎች የሚለውን ቀጣዩን ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➧ሰማያትና ምድር ከመፈጠራቸው አምሳ ሽ አመት በፊት አንድም ሳይቀር ውሳኔዎች ሁሉ “ለውሀል መህፉዝ” ላይ ተዘግቧል፡፡ ሁሉም ነገር በለውሀል መህፉዝ የተጻፈ መሆኑ በትክክለኛ ሀዲስ ተዘግቧል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርዓናዊ አንቀጽ…
➠ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ"
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
➖➖➖
➧ ክፍል ⓫

➲የተወሰኑ ቡድኖች ለቀደር የሚሰጡት ትንታኔ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➼ቀደርን አስመልክቶ የተለያዩ አንጃዎች ከትክክለኛው መንገድ ባፈነገጠ ሁኔታ
የተሳሳቱ ትርጉሞችን ሰጠዋል፡፡ ከነዚህ መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡-

➀ ጀህምያ እና ጀብሪያ
➵➵➵➵➵➵➵➵➵

➮እነዚህ ቡድኖች ባሪያው ተገዶ እንጅ በሚሰራው ስራ ምንም ዓይነት ምርጫ ፣ ችሎታ ፣ እቅድ እና ፍላጎት የለውም ይላሉ፡፡ የሰውን ልጅ ልክ በነፋስ እንደሚወዛወዝ ላባ ወይም ያለፍላጎቱ በነፋስ ሐይል እንደሚንቀሳቀስ የዛፍ ቅጠል ይመስሉታል፡፡ ይህ ከጀህምያ የሆኑ ጀብርያዎችና ሌሎችም የሚሉት ነው፡፡

➮ የጀህምያና የጀብሪያ ተቃራኒ የሆኑት ሙዕተዚላዎች ናቸው ማንኛውም ሰው የአላህ ፍላጎት ሳይደበለቅ የራሱን ስራ የመፍጠር ችሎታ አለው ይላሉ፡፡የባሪያው ስራ ከእራሱ ምርጫና ችሎታ ጋር እንጅ ከአላህ መሽአ ጋር ምንም አይነት ቁርኝት የለውም ይላሉ
፡፡

➳አንዳንዶች ወሰን በማለፍ ፡ አላህ - ሱብሃነሁ ወተዓላ - ነገሮች ከተከሰቱ በኋላ እንጅ ቀድሞ አያውቀውም ይላሉ፡፡ ነገሮችን የሚያውቃቸው ባሪያው አሁን ስራውን እንዳስገኘው ነው ይላሉ፡፡ እነዚህ “አልቀደርየቱ አንኑፋት” በመባል የሚጠሩት የሙዕተዚላ ድንበር አላፊዎቸ ናቸው፡፡

➲የመጀመሪያው ቡድን ጀብሪያ ወይም ቀደርያ አንኑፋት በመባል ይጠራል፡፡ ይህ ቡድን ቀደርን ወይም የአላህን ውሳኔ ቢያጸድቁም በቀደር ላይ ወሰን ያልፋሉ፡፡ ከባሪያው ላይ ኢራዳን ወይም ፍላጎትን ያራቁታሉ፡፡ በዚህ አመለካከት ተቃራኒ ሁለተኛው የሙዕተዚላ ቡድን የአላህን መሽአ እና ኢራዳ ውድቅ በማድረግ የባሪያውን መሽአ በማጽደቅ ላይ ድንበር አልፈዋል፡፡ ሁለቱም ቡድኖች ጠማማና ታላቅ ስህተትን የፈጸሙ ናቸው፡፡

➼አህለሱና ወልጀማዓህ በኢማን ፣ በቀደር ያላቸው መካከለኛ አቋም
➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮➮

✅ተገቢ የሆነ ጥላቻና ውግዘት ለቀደርዮች

➵የአህለሱና ወልጀማዓህ መካከለኛ አቋም፡ ለባሪያው ችሎታን ፣ ምርጫን እና ኢራዳን ያጸድቃሉ፡፡ ይሁን እንጅ የባሪያው መሽአ ፣ ችሎታ ፣ ምርጫ እና ኢራዳ ለአላህ መሽአ ፣ ችሎታ ፣ ምርጫ እና ኢራዳ ተከታይ መሆኗን ያምናሉ፡፡ አንድ ሰው በአላህ ኢራዳ እና በእርሱ መሽአ ካልሆነ በቀር ስራን መስራት አይችልም፡፡

➧ቀደርያ ውግዘትና ጥላቻ ይገባቸዋል
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➠ቀደርያ ፡ ከአላህ ጋር ሁለት ፈጣሪዎችን በማረጋገጣቸው የዚህ ኡመት መጁስ በመባል ተጠርተዋል፡፡ እነዚህ ቡድኖች “ሁሉም ሰው ያለአላህ መሽአና ፍላጎት የራሱን ስራ ፈጥሮ መስራት ይችላል” ይላሉ፡፡ በዚህ ታላቅ የኢማን መሰረት - የቀደር እምነት ላይ ትክክለኛውን ጎዳና በመልቀቃቸውና ነገሮችን በማደባለቃቸው ከሐቅ ባለቤቶች ከፍተኛ የሆነ ውግዘት እና ጥላቻ ደርሶባቸዋል።

➠ኢንሻአላህ
ይቀጥላል
ام فاروق

=
https://t.me/https_Asselefya1
➧አልሼይኽ አብድረዛቅ አልበድር ሀፊዘሁላህ እንዲህ ይላል

➲ሴት ልጅ አይኗን ሀራም ፈሳድ ከሆኑ ነገሮች ዝቅ ሰበር የማተደርግ ከሆነች እራሷን ለአደጋ ታጋልጣለች

ምክንያቱም ሸይጣን ቀስ በቀስ ይወሰውሳታል

➻ይህም ነው ሴቶች እንዲበላሹ ወደ ክፉ ነገር እንዲያመሩ የስነ ምግባር መበላሸት የመጀመርታው ይህ ነው

#ምንጭ
📚((مَـوعِظة النّـسَاء - صـ 41))

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
Audio
◾️አዝካር ወል አዳብ
➖➖➖➖➖➖
🔻الأذكار وا
لآداب

➡️ የምላስ ጣጣ
➡️ እውነትና ውሸት
➡️ ውሸትና አደጋው
➡️ መልካምና መጥፎ ንግግር

↪️ ክፍል 3⃣9⃣ ↩️
〰〰〰〰〰〰

🎙 አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
➧አብደላህ ኢብኑ ኡመር رضي الله عنه እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል።

➠ነፍሱን የበላይ ያደረገ (እላይ የሰቀለ)፤ በአካሄዱ የተንጠባረረ ሰው አላህ በሱ ላይ የውመል ቂያማ የተቆጣ ሆኖ ይገናኘዋል።

📚(ኢማሙ አህመድ ዘግቦታል)
➧ውዷ እህቴ

➲አርቀሽ በሀሳብ አትጓዢ
ህይወት አጭር ናት
።

➳አንድ እርምጃ ሳትራመጅ ከቆምሽበት ታበቃለች።

➳በጅሽ ለመጎረስ ያዘጋጀሽውን ምግብ መጉረስ እስኪያቅትሽ ደረስ እንደዚህ ናት ህይወት።

➳እናም ዛሬ ላይ ብቻ ወስኝ ዛሬ ላይ ብቻ ስራሽን በኢኽላስ አጥርተሽ ስሪ።

➳ነገን ሳትይ ዛሬውን በፍጥነት ቶብች ወደ ጌታሽ ገስግሽ ።

https://t.me/Asselefya1
https://t.me/Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➠ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ" ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ➧ ክፍል ⓫ ➲የተወሰኑ ቡድኖች ለቀደር የሚሰጡት ትንታኔ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➼ቀደርን አስመልክቶ የተለያዩ አንጃዎች ከትክክለኛው መንገድ ባፈነገጠ ሁኔታ የተሳሳቱ ትርጉሞችን ሰጠዋል፡፡ ከነዚህ መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡- ➀ ጀህምያ እና ጀብሪያ ➵➵➵➵➵➵➵➵➵ ➮እነዚህ ቡድኖች ባሪያው…
➽"ጥቅል የቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ዓቂዳ"
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➻ክፍል አስራ ሁለት

➲በቀደር ማመን ከኢማን መሰረቶች ነው
➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯➯

በቀደር ማመን ከኢማን መሰረቶች አንዱ እንደሆነ በጅብሪል ሐዲስ ላይ ግልጽ ተደርጓል፡፡ ጅብሪል ነብዩን صلى الله عليه وسلم ስለኢማን በጠየቃቸው ጊዜ የሚከተለውን ምላሽ ሰጠውታል፡-

◆الإيمان أن تؤمن بالله ومالئكته وكتبه ورسله واليوم الآخر وتؤمن بالقدر خيره
وشره"

➠“ኢማን በአላህ ፣ በመላኢካዎች በመጽሐፎች ፣ በመልእክተኞች ፣ በመጨረሻው ቀን ማመን ፤ መልካም ይሁን መጥፎ በአላህ ውሳኔ (የሚከናወን መሆኑን) ማመን” (ቡኻሪ፡ 4499, ሙስሊም፡ 10)

➧አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

●إِنَّا كُلَّ شَيْءٍ خَلَقْنَاهُ بِقَدَرٍ

“እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው፡፡” ቀመር፡ 49

➧የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم የሚከተለውን ተናግረዋል፡-

◆"الحرص على ما ينفعك، واستعن بالله ، فإن أصابك شيء فلا تقل: لو أني فعلت كذا كان كذا ولكن قل قدر الله وما شاء فعل، فإن لو تفتح عمل الشيطان"

➠“በሚጠቅምህ ነገር ላይ ፍላጎቱ ይኑርህ ፤ በአላህ ታገዝ ፤ አንድ ነገር ከደረሰብህ “በዚህ መልኩ ብሰራው ኖሮ እንዲህ ይሆን ነበር፡፡” አትበል ፤ ነገር ግን “አላህ የወሰነውና እርሱ የሻው ሆነ” በል፡፡ “ለው” (ይህ ቢሆን ኖሮ) የምትለው ቃል ለሰይጣን ተግባር (በር) ትከፍታለች፡፡” ሙስሊም፡በዚህ ዙሪያ የመጡ ግልጽ ሐዲሶች በርካታ ናቸው፡፡ ይህ የታወቀ መሰረት ነው፡፡

➠ምስጋና ለአላህ ይገባው በዚህ ዙሪያ የአህለሱና ወልጀማዓ ዓቂዳ የሆነው ሐቅ በኪታብና በሱና መረጃዎች ተብራርቶ ግልጽ ሆኗል፡፡ ከዚህ መሰረት የተንሻፈፈ ከቁርኣንና ከሱና አፈንግጧል፡፡መንሻፈፉን ያመጣው ከራሱ ነፍስ ወይም ከስሜቱ በኩል ያመጣው መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ከቁርኣንና ከሐዲስ መረጃዎች ለማፈንገጥ ሙከራ ያደረገ አካል ሁሉ ከጥፋት ላይ መውደቁ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡

➧አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

●وَأَنَّ هَٰذَا صِرَاطِي مُسْتَقِيمًا فَاتَّبِعُوهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعُوا السُّبُلَ فَتَفَرَّقَ بِكُمْ عَن سَبِيلِهِ ۚ ذَٰلِكُمْ وَصَّاكُم بِهِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ


“ይህም ቀጥተኛ ሲሆን መንገዴ ነው ፤ ተከተሉትም፡፡ (የጥመት) መንገዶችንም
አትከተሉ፡፡ ከ (ቀጥተኛው) መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና፡፡ እንሆ ትጠነቀቁ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ፡፡” አል አንዓም፡153


➯ኢንሻአላህ
ይቀጥላል


=
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️አዝካር ወል አዳብ
➖➖➖➖➖➖
🔻الأذكار والآداب


➡️ ሙስሊምን መስደብ
➡️ የእርግማን አደገኝነት
➡️ ሀሜት መዘዞቹና ክፋቱ
➡️ ሀሜት የሚፈቀድባቸው ቦታዎች


↪️ ክፍል 4⃣0⃣ ↩️
〰〰〰〰〰〰

🎙 አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
➠ወሳኝ ጥንቃቄ
➫➫➫➫➫➫➫

➲አንዱ ላይ መሆንህ የግድ ነው አይቀርም

➧ሀቅን የተወ ሰው ባጢል ይቀበላል
➧ከእውቀት የራቀ በጅህልና ይኖራል
➧ከተውሂድ ያፈነገጠ በሽርክ ይጨማለቃል
➧ከሱና የሸሸ ቢድአ ላይ ይወድቃል
➧የዱንያ ህይወትን የመረጠ አሄራን ያጣል
➧ከጀነት የሸሸ ጀሀነም በደስታ ይቀበለዋል
➧መልካም ስራ አሻፈረኝ ያለ ወንጀል ይቀለዋል
➧በሀቅ ላይ ያልፀና በውሸት እንዲፀና ይደረጋል
➧የጀነት መንገድ የተወ በጀሀነም መንገድ ይጓዛል
➧ለሀቅ ሰዎች ጀርባ የሰጠ በባጢል ሰዎች ይጎተታል
➧አላህን ከመታዘዝ የዞረ ሸይጧንን ለመታዘዝ ይገደዳል
➧ቁርአንና ሀዲስ አልከተልም ያለ ስሜቱ እንዲከተል ይደረጋል
➧የሰለፎች (የሶሀቦች) መንገድ ያልያዘ የጥመት ቡድኖች ይቀራመቱታል


✅ ስለዚህ እራሳችንን በመመርመርና በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን ላይ ከሀቅ ላለመውጣት እሾህ ላይ እንደሚራመድ ሰው ጥንቃቄ ማድረግን ይሻል።

https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w