💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
14.3K subscribers
4.79K photos
2.21K videos
164 files
13.1K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ
↓↓↓↓↓↓
@Ass_selefyaa_bot
@Ass_selefyaa_bot
Download Telegram
~ አላህ ሆይ ችግረኛ በጠራህ ጊዜ ምላሽ ሰጪው አንተ ነህ፤ ነገሮች ሲጠቡብንና መውጫ ሲጠፋን ተስፋችን አንተ ነህ! አላህ ሆይ! ጥራት ይገባህ፤ የምንከጅለውም ካንተ የምሰማንም አንተ ነህ፤ በደጅህ መመላለስ (ለአንተ መስገድ) ለነፍስ ዕርገታ (ልዕልና) ነው!
የንግስና ሁሉ ባለቤት ሆይ! ፍላጎቶቻችን ወደ አንተ ከፍ አሉ፤ ከአንተ በቀር መላ እንዲሰጠን የምንለምነው ሌላ ማንም የለም!”

=
t.me/https_Asselefya1
~ አንዳንድ ጊዜ ወደ አላህ የሚያቃርብህ ‘ሀዘን’፤ አላህን ከሚያስረሳህ ‘ደስታ’ ይበልጣል❗️”

“ፀጋ ሲበዛልህ ሰጪውን ከረሳህ፣ ፀጋው ላንተ ‘ፈተና’ እንጂ ‘ስጦታ’ አይደለም።”

“ወደ ትክክለኛው መስመር የመለሰህ ‘ስህተት’፤ በትዕቢት ካሳበጠህ ‘መልካም ስራ’ የተሻለ ነው።”

“ልብህ ሲሰበር ወደ አላህ የምትሸሽ ከሆነ፣ ያ ስባሪ ላንተ ትልቅ እርምጃ ነው።”

~ ትልቁ ኪሳራ በፀጋ ተከቦ አላህን መርሳት ሲሆን፣ ትልቁ ትርፍ ደግሞ በችግርም ሆነ በስህተት ውስጥ ሆኖ ወደ አላህ መመለስ ነው።”

=
t.me/https_Asselefya1
#رســـائل_قــرآنية💭
«ቁርአናዊ መልእክት

﴿كَلَّا لَوْ تَعْلَمُونَ عِلْمَ الْيَقِينِ ۝٥ لَتَرَوُنَّ الْجَحِيمَ ۝٦ ثُمَّ لَتَرَوُنَّهَا عَيْنَ الْيَقِينِ ۝٧﴾

اللهم انا نسألك الجنة وما قرب اليها من قول او عمل ونعوذ بك من النار وما قرب اليها من قول او عمل🤲🏻

=
«مُخيفٌ جدًا
«በጣም አስፈሪዉ ነገር ....

«أن يقبض ملك الموت روحك وأنت تُقلّب نظرك في الحرام!»

«የተከለከለ(ሀራም)ነገሮች እያየህ (እየተመለከትክ)የሞት መላእክ ነፍስያህን ሲይዘዉ....!»

=
t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
• የአላህ ባሪያ ሆይ እረሳህን ?
•ለብቻህ ትቀበራለህ!
•ለብቻህም ትጠየቃለህ!
•አላህ ፊት ለብቻህ ትቆማለህ!
~ለዚህቀን ምን አዘጋጅተሀል ?
«ሶላትህን በወቅቱ ሰግደሀልን ?
«ልብህ ከሀሜት እና ከሪያእ(አዩልኝ ስሙልኝ) የጠራ ነዉን ?
~ ምላስህ አላህን በማዉሳት የታዘዘህ ነዉን ከሙዚቃ ተቃራኒ ! ስልክህ የሚመሰክርልህ ወይስ የሚመሰክርብህ ነዉን ? ሌላም..ሌላም... በአላህ ስም እምላለሁ ትጠየቃለህ... ጊዜ ያልፋል.. አላህ በማይወደዉ ነገር ላይ ቢዚ አትሁን! ወደ አላህ ተመለስ.....!

=
t.me/https_Asselefya1
•ይቺን ወደ መጥፎ የምታዘኝን
ነፍሴን ቀጥ እንድትል አሁንም ድረስ እታገላታለሁ
፤ አንዴ ታሸንፈኛለች፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ አሸንፋታለሁ። ይህ ትግል ንጹህ
በሆነ ልብ አላህን እስከማገኝ ድረስ ይቀጥላል።
”

=
t.me/https_Asselefya1
ሰዉኮ ይኮምታል ....! ፈገግ በሉ እና ዋሉልኝ
• ሕይወት ማለት አጋጣሚዎች ናት፤ አጋጣሚዎች ደግሞ አይረሱም። ሰው አስቸጋሪ ቀኖቹን ሊረሳቸው ይችል ይሆናል፤ ነገር ግን በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ለብቻው ጥሎት የሄደውን ሰው እና ሁኔታውን ያቀለለለትን ያገዘውን ሰው በፍጹም አይረሳም።”

=
t.me/https_Asselefya1
«በእኛ መኖር ደስ የሚሰኙ  ሰዎችን አላህ ያቆይልን፤ እነርሱ ለልባችን ትርታ፣ ለመንገዳችንም ምርጥ ጓደኛ ናቸው።»

=
t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
• ከሴቶች ራሱን አርቆ የሚኖር ወጣት ከመልካም ነገር ላይ አይወገድም። ያላገባ ወጣት የሚደክመዉ እና መጥፎ ነገር ላይ የሚወድቀዉ ያልተፈቀዱ ሴቶች ጋር ሲቀርብ ነዉ። እናተ የወጣት ስብስቦች ሆይ ማሕበራዊ ሚድያን ተጠንቀቁ ! " በእህትነት ብቻ ነዉ የሚልንም ተጠንቀቁ ይች የመጥፊያ መንገድ ነች ። የሸር መንገድ ነች። መጥፎ ነገር ላይ መወደቂያ መንገድ ነች። ሸይጧን ወጣትን ቀስ በቀስ ወደ መጥፎ ነገር ይጎትተዋል። ከሴቶች የራቀማ! አይኑን፣ ምላሱን ይጠብቃል። ያልተፈቀዱ ሴቶች ጋር የማይገናኝ ከሆነ ! ለመታገስ ቀላል ይሆንለታል።

=
t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
• ጓደኛ ጎታች ነዉ! ወደ ጀነት ወይም ወደ እሳት !

الْأَخِلَّاءُ يَوْمَئِذٍ بَعْضُهُمْ لِبَعْضٍ عَدُوٌّ إِلَّا الْمُتَّقِينَ)

=
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
«የዲን ባለቤት የሆነች ሴት ወደ እሷ ስታይ ትደሰታለህ፣ በምታዛት ጊዜ ትታዘዛለች ከሷ ስትርቅም ነፍሷንም ንብረትህንም ትጠብቃለች።
በሁለት ነገሮች ላይ ታግዝሀለች
አንደኛዉ አላህን በመታዘዝ ላይ፣ ታግዝሀለች ታነሳሳሀለች፣ ታጀግንሀለች። ብዙ ወንዶች አሉ በሚስቶቻቸዉ ሂድያ ያገኙ (የተመሩ)! ቁርአን ስትቀራ ሲያይ እሱም ይቀራል። ከቁርአን ባለቤቶችም ይሆናል። አንዳንድ ወንዶች ቂያም ለይል አያቁም ፣ ሚስቱ ሌሊት ስትቆም አይቶ እሱም መቆም ይጀምራል።

📍 የዲን ባለቤት የሆነች ሴት አግባ !

=
t.me/https_Asselefya1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
¶ ቴክኖሎጅያ ፈገግ ብላችሁ አምሹልኝ.......በሳቅ ደከምን እኮ¡ እናንተም ድከሙ....✋
«ሙሳ አላህ ባሕሩን እንደሚከፍልለት  አያውቅም ነበር፤ ነገር ግን የሚያውቀው አላህ በጭራሽ እንደማይተወው ብቻ ነበር።»

«አላህ ችግርህን እንዴት እንደሚፈታው ባታውቅም፣ መንገድ በሌለበት መንገድን እንደሚያበጅልህ ግን እወቅ የቂን ብቻ!»

=
t.me/https_Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
«የዲን ባለቤት የሆነች ሴት ወደ እሷ ስታይ ትደሰታለህ፣ በምታዛት ጊዜ ትታዘዛለች ከሷ ስትርቅም ነፍሷንም ንብረትህንም ትጠብቃለች። በሁለት ነገሮች ላይ ታግዝሀለች አንደኛዉ አላህን በመታዘዝ ላይ፣ ታግዝሀለች ታነሳሳሀለች፣ ታጀግንሀለች። ብዙ ወንዶች አሉ በሚስቶቻቸዉ ሂድያ ያገኙ (የተመሩ)! ቁርአን ስትቀራ ሲያይ እሱም ይቀራል። ከቁርአን ባለቤቶችም ይሆናል። አንዳንድ ወንዶች ቂያም ለይል አያቁም…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
• ለጋብቻ የመልካም ወንድ ባህሪ  መገላጫዎች  «ዲን እና መልካም ስነ _ምግባር» ናቸዉ ።   አንዳንዴ   አንድ ሰዉ  ዲን ሊኖረዉ ይችላል ነገር ግን መልካም ስነ ምግባር ላይኖረዉ ይችላል። ለምሳሌ፦  ቸርነት፣አይናፋርነት ።  አንድ ሰዉ  ሶላት ሰጋጅ ሊሆን ይችላል  ጁሙአ  ጀመአ  ሊሳተፍ ይችላል ነገር ግን ስስታም ነዉ ።  ለስስታም ሰዉ እንዴት ይዳራል ? ለምሳሌም  ሀያእ አይናፋርነት ላይኖረዉ ይችላል።  በስ_ነምግባር  ዙሪያ  ገደብ የሌለዉ ሊሆን ይችላል።   ለዚህም የአላህ መልእክተኛ ﷺእንዲህ ይላሉ፦ ዲኑን እና ስነ ምግባሩን የምትወዱለት ሰዉ ከመጣ ዳሩት ያሉ ።


📍ዲን ብቻ ሳይሆን መልካም ስነ_ምግባር ያለዉን ወንድ አግቢ
!

=
t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔖 ወንጀልን በነፍስህ ላይ አታሳምር።

✓ ታያለህ ታያለህ ልብህ እስኪበላሽ ድረስ!
✓ ትሰማለህ ትሰማለህ ልብህ እስኪበላሽ ድረስ!
✓ በሀሜት እና ነገር በማሰድ ታወራለህ ልብህ እስኪበላሽ ድረስ !

🔖 አንድ ባሪያ ከወንጀል ጋር ሁኔታ አለዉ፦ መጀመሪያዉን ቀለል ያደርጋል። ከዚያም ሌላ ጉዳይ ላይ ይወድቃል። ለዚህም እይታ ተከለከለ ። ምክንያቱም እይታ ትልቁ ወንጀል ዝሙት ላይ ይጥላል እና ! ከዚያም እያለ እያለ ሌሎችም ትላልቅ ወንጀሎች ላይ ይወድቃል ! ለዚህ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ አንድን እይታ ሌላ 2 ኛ እይታ አታስከትል። የመጀመሪያዉ አለልህ ሁለተኛዉ ላይ ግን የለም ። ሁለተኛዋ እይታ በአንተ ላይ ነች። ለአንተ አይደለችም። ደጋግሞ በማየት ላይ የሚዘወትር ሰዉ እንዴት ነዉ ? ልብ ይገለበጣል ብሎ አይፈራምን ? በወንጀል ከተፈተንክ ኢስቲግፋርን አብዛ ! ወደ አላህ መመለስን አብዛ! ልብ እና የሰዉነት ክፍል መስተካከልን ከአላህ ጠይቅ !

=
t.me/https_Asselefya1
DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ]
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات ሸዋል   24/1447 ሚያዚያ  4/2018 አፕሪል   12/2026
بَارَكَ الله لَكُما، وَبَارَكَ عَلَيْكُما، وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ !

አላህ ትዳራችሁ ያማረ የሰመረ ያድርግላችሁ!

=
«አላህ የቀልባችንን አዋቂ ነዉ
ከምንፈልገዉ በላይ እሱ የመረጠልንም የተሻለ ነዉ።
Âť

=
t.me/https_Asselefya1
ወንድማዊ ምክር፤

ፎቶ መነሳት ይፈቀዳል ብለዉ ከሚሟገቱት ብትሆን እንኳ፣ የራስህን፣ የልጆችህን ወይም በጣም የምትወዳቸውን ሰዎች ፎቶ አንስተህ አትለጥፍ

روى ابن عباس رضي الله عنهما عن النبي ﷺ:

​«العَيْنُ حَقٌّ، ولو كانَ شيءٌ سابَقَ القَدَرَ سَبَقَتْهُ العَيْنُ» (رواه مسلم).

ዐብደሏህ ኢብኑ ዐባስ ከመልክተኛዉ ይዘዉ በነገሩን ሐዲስ ላይ እሳቸዉ እንዲህ ብለዋል

ዓይን እውነት ናት፤ ቀደርን የሚቀድም ነገር ቢኖር ኖሮ የሰው ዓይን በቀደመችው ነበር።

የሰው ዓይን በሰውነት ላይ ብቻ የሚታይ በሽታ እንዳይመስልህ የነቢዩ (ﷺ) ሐዲሶች እና የዑለማዎች ንግግር እንደሚያረጋግጡት፤ የሰው ዓይን በሰውነት ላይ ብቻ ሳይሆን በእዉቀት፣ በንብረት፣ በትዳር እና በልጆች ስነ-ምግባር ላይም ጉዳት ያደርሳል።

አላህ ሆይ! በሰጠኸን ነገር ላይ በረካህን አውርድልን፤ ከክፉ ነገርም ጠብቀን። በሙሉእ ቃላቶችህም ከክፉ ዓይንና ከሸይጣን ተንኮል በአንተ እንጠበቃለን