La tehzen
95 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
ከዕብ ኢብኑ ማሊክ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና እንዲህ ይላል:-
"ነገር ማዋሰድን ተጠንቀቁ ነገረኛ ሰው ከቀብር ቅጣት አያርፍምና።"
ምንጭ:-📚الموسوعة 405/4
🔰 #የእጁጅ_ወመእጁጅ

🔷 ክፍል #ሰባት 7⃣

ለዙል ቀርነይን፦ አንተ ማነህ!!! እኔ የት ነዉ ያለሁት! እያለ ማዉራት ጀመረ።
ይሁን እንጂ ዙል ቀርነይን የአይጁርን ንግግር አይረዳምና በጥሩ ሁኔታ መሆኑን እንዲገነዘብ ብቻ እጁን በአይጁር ራስ በማሳረፍ አሻሸው፡፡

በመቀጠልም ዙል ቀርነይን ወታደሮቹን ለአይጁር ምግብ እናመጠጥ እንዲያቀርቡለት አዘዛቸው፡፡ አይጁርም የቀረበለትን ምግብ እየተመገበ ማን ነዉ ይሄ ሰዉ እንዲ ሚንከባከበኝ በማለት እያሰላሰለ የቀረበለትን ምግብ መመገብ ጀመረ፡፡
ምግቡን በልቶ እንዳጠናቀቀም ዙል ቀርነይን እንዲያርፍ በእጁ ካመላከተዉ በኀላ አይጁር አረፍ ሲል ዙል ቀርነይንም ከጎኑ ተቀመጠ፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉም በድንገት ከቤተ መንግስት ሰዉ በመምጣት የሀገሩ ዑለማዎች እንደመጡና የመግባት ፍቃድም እንደሚጠይቁ ነገረዉ፡፡ ይህን ጊዜ ዙል ቀርነይን አይጁርን እንዲተኛ በእጁ አመላክቶት ወደ እንግዶቹ በመሄድ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አድርጎላቸዉ ክስተቱን ከመጀመሪያዉ እስከ መጨረሻው ተረከላቸዉ የንጉሱ ገዳይ እና የያእጁጃዉያኑ ወጣትም እዚህ እንደሚገኝ አክሎ ነገራቸዉ፡፡
በመቀጠልም፦ ስለዚህ ፍጥረታት የምታዉቁት ነገር ምን አለ በማለት ጠየቃቸው፡፡
በመካከላቸዉም አንድ እጅግ በእድሜ የገፋና በእዉቀትም የበለፀጉ አዛዉንት ነበሩና እንዲህ በማለት ንግግራቸዉን ቀጠሉ፡፡
አንተ መልካም ንጉስ ሆይ!! እነሱ የእጁጅ እና ማእጁጅ የሚባሉ ነገዶች ሲሆኑ እጅግ አላህን በማምለክ ጥሩ የአላህ ባሮች ነበሩ፡፡
በመሀከላቸዉም ያጁስ እና ማጁስ የተባሉ ከሀዲያን እና ድግምተኛ ወንድማማቾችም ነበሩ፡፡
ያጁስ የተባለው፦ድግምቱን ተጠቅሞ ህዝቦቹን ወደ ፀሀይ አምልኮ በመጥራት ለተከታዩችም ግዙፍ የሆነ ቤተ አምልኮ ገንብቶ በኩፍር ጎዳና አንቧቧቸዉ፡፡
ማጁስ የተባለዉ ደግሞ የወንድሙን መመለክ እና በህዝቡ አንደበትም መቀደስን ሲመለከት ቅናት በልቡ አደረበትና የተቀሩትን ህዝቦች እሳትን እንዲያመልኩ ጥሪ

አዛዉንቱ ንግግራቸውን ቀጥለዋል፦ በዚህ ሁኔታ ከፊሎቹ የፀሀይ አምላኪ ሆነዉ ከፊሎቹ የእሳት አምላኪ ሲሆኑ የተቀሩት ጥቂቶቹ ደግሞ በኢማናቸዉ ላይ ፀኑ፡፡
የነዚህ በኢማን መፅናት እረፍት የነሳቸዉ ያጁሳዉያን እና ማጁሳውያን አንድ ላይ በመተባበር በሙእሚኖቹ የድግምት ናዳዎችን ያዘንቡባቸዉ ጀመር፡፡ ይሁን እንጂ ሙእሚኖቹ የድግምቱ መደጋገም ከኢማናቸዉ ፍንክች አላደረጋቸዉም ነበር፡፡
በመጨረሻም የሙእሚኖቹን ልጆች በወላጆቻቸው ፊት እያረዱ ወደ ኩፍር ቢያስገድዷቸዉም እምነታቸዉ ይበልጥ መጠንከር ሲጀምር በዘመኑ የነበሩትን ሙእሚኖች ባጠቃላይ በእሳት አቃጥለዉ ደመሰሷቸዉ በማለት ሽማግሌዉ ንግግራቸዉን ሳይጨርሱም ዙል ቀርነይንም፦ ከዚያስ ምን ተከሰተ? በማለት ጠየቃቸዉ፡፡
እሳቸዉም፦ "ከዚያማ አላህ የእርግማንን አይነት ካወረደባቸዉ በኀላ ከሰዉ ዘር ባጠቃላይ የተገለሉ በማድረግ ጨለማን መቀመጫቸዉ....እሳትን ደግሞ መደንበሪያቸዉ ......ሰውነታቸው ደግሞ ቅርፅ አልባ አድርጎ ፀሀይ ሰውነታቸዉን ቀነካ ቁጥር እንዲያቃጥላቸዉ ወሰነባቸው፡፡ በማለት ነገሩት
ዙል ቀርነይንም ግራ በመጋባት፦እንዴት ይህ ሊሆን ይችላል? በሰሞኑ እኮ 10-11የሚሆኑት ወደ ምድር ወጥተዉ ከኛም ተቀላቅለው ነበር፡፡ ግን ፀሀይ ሲያቃጥላቸው አላየንም ሲል ጥያቄ አቀረበ?
አዛውንቱም ይህማ በጭራሽ አይሆሆንም፡፡ እስቲ እናንተ ዘንድ ያገታችሁትን ወጣት አይጁር አሳዩኝ ብለው ጠየቁ፡፡
ከዚያም ዙል ቀርነይን እና አዛውንቱ ወደ አይጁር ክፍል ሄዱ፡፡ በእንቅልፍ ላይ ያለዉን አይጁርን ሲመለከቱት ይህ እንኳን ያእጁጃዊ አይደለም፡፡ ግን ዘረ ቅይጥ ነው አሉ፡፡
ዙል ቀርነይን ይሄ ወጣት የተያዘ እለት ሰዎች ይዘው በወጡት የጧፍ ብርሀን ምክንያት እራሱን ስቶ ነበር አላቸው፡፡
አዛውንቱም አይ ተመሳስሎበት ነው፡፡ ያእጁጃዉያኑ በብርሀን ሲያስፈራሩት ሴላደጉ ነው፡፡ አሉት
ዙል ቀርነይንም ገባኝ ግን ቋንቋቸው ሊገባኝ አልቻለም አላቸው፡፡
አዛውንቱም እኔ ስለማቀው አስተምርሀለው አሉት፡፡
በመቀጠልም ዙል ቀርነይን ወደተቀሩት ኡለማዎች ዘንድ በመሄድ የሚከተለውን ጊዜያዊ አዋጅ አፀደቀ፡፡
1.እነዚየያን ሰዎች ለምንም አይነት ፀብ አንጋብዛቸውም ምክንያቱም በብልሀት ሆነ በጉልበት ከኛ ይበልጣሉና፡፡
2.ከክህደታቸው እንዲመለሱ ጥሪ ማድረግ፦ ጥሪያችንን ካልተቀበሉ ውሳኔው የኛ ይሆናል፡፡ በማለት ትዕዛዙን ካስተላለፈ በኀላ የመጡት ኡለማኦች ተስማምተው፦ ይህ ጉዳይ መቋጫውን ሳያገኝ ወደ ሀገሮቻችን አንመለስም አሉ፡፡
ዙል ቀርነይንም በመቆየታቸው የተሰማውን ደስታ ገሐፆላቸው ለሦስት ቀናት ግን ከአዛውንቱ ማሳለፍ እንደሚፈልጉ ነግሯቸው ቋንቋቸውን ለመማር ከአዛውንቱ ጋር ሆነ፡፡
አይጁር በክፍሉ ሆኖ ሳለ በወታደሮቹ በሚመጣለት ምግብ እና መጠጥ በጣም በመገረም ለምንድነው እነዚን ህዝቦች ያለ ምክንያት የምጠላቸው???
እነዚ ህዝቦች መጥፎ ቢሆኑ እኮ ለንጉሳቸው በቀል ሲሉ ጭንቅላቴን ይቆርጡት ነበር፡፡
ስለዚህ
ውሳኔ ከመወሰኔ በፊት ቀጥልቀት ማሰብ ይኖርብኛል በማለት ከራሱ ጋር አወራ፡፡
ዙል ቀርነይንም ለተከታታይ ቀናት ቋንቋቸውን በሚገባ ከአዛውንቱ ከተማሩ በኀላ አይጀጁር የተኛበት ክፍል በመግባት አይጁርን በተማረው ቋንቋ ሰላም ባንተ ላይ ይሁን አለው፡፡
አይጁርም በድንጋጤ ዙል ቀርነይንን እያየ፦ ይህ ያእጁጃዊ ነዉ ወይስ አይደለም፡፡ በማለት እያሰበ ሰላምታውን መለሰለት፡፡
ዙል ቀርነይንም፦ ልጄ ሆይ ከአላህ ሌላ ማን አለ?እሱ እኮ አንዱ እና ብቸኛው ነው፡፡ ወገኖችህም እኮ አላህን በብቸኝነት አምላኪ ነበሩ፤ በመጨረሻም የማይጠቅምን ነገር አማልክት አድርገው ያዙ፡፡ አለው
ይህን ጊዜ አይጁር በመገረም ዙል ቀርነይንን እየተመለከተ፦ስለ ህዝቦቼ ምታቀው አለ ሲል ጠየቀው፡፡

Part ➑
ይቀጥላል....
ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ
~
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጀመሪያ አመት ተማሪዎችን (ፍሬሾችን) እንደ እናትና አባት ሆነው የሚቀበሉ የሱና ወንድምና እህቶችን ስልክ ቁጥርና ሙሉ አድራሻ ለማግኘት ከታች ያለውን ቻናል ይቀላቀሉ !!!

👇

https://t.me/Daewa_selefya_beuniversity

👆አዲስ ለሚገቡ share አድርጉላቸው

Follow the sunnah !!!!!

https://t.me/Daewa_selefya_beuniversity
ክፍት የስራ ቦታ ለኡስታዞች(ሀፊዞች)
ዳሩል አርቀም የቁርዓን ማእከል ወንድ እና ሴት የቁርዓን ሀፊዞችን በኦላይን ቁርዓን አስቀሪነት አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ቁርዓንን የሀፈዛችሁ እንዲሁም የማስቀራት ተስጥዖ ያላችሁ ኡስታዞች ይሄ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን 02/09/2014 ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት የስራ ቀናቶች በተቀመጠው አድራሻ ማመልከት ትችላላችሁ።
መስፈርት
—ቁርዓን የሀፈዘ/ች
—smart phone ያለው/ያላት
—ጥሩ የስራ ተነሳሽነት ያለው/ያላት
—የትምህርት ደረጃ ከ 10 በላይ የሆነ/ች


ለበለጠ መረጃ
0991808935
0904195332

የዳሩል አርቀም የቁርዓን ማዕከል ማኔጅመንት ቦርድ
ከአንደኛው መልካም ነገር ወጥቶ ሌላ መልካም ነገር በመሥራት መካከል ትዕግስት የሚባል አድካሚ ነገር አለ። ግና አላህ ዘንድ ለተሳሰበው በብዙ አጅር የተሞላ ነው።
ታገሉ
ታገሱ
እህቴ ሆይ

ኸይር ሲመጣ አመስጋኝ ሸር ሲመጣ ሶብርን ትዕግስትን ተላበሺ!

ምንም እንኳን ነገራቶች እንዳሰብሻቸው ባይሆኑም ታጋሽና አመስጋኝ እንስት ሁኚ።
→ ክፍል አንድ ←

بــســم الــلــه الــرحــمــن الــرحــيمــ
الحمد الله رب العالمين

↝አስካሪ መጠጥ (ኸምር)↜

ለመጀመሪያ ሰዉ መጠጥን ይወስዳል፡፡ ከዚያም መጠጡ መጠጥን ይወስዳል፡፡ የኋላ ኋላም መጠጡ ሰዉን ይወስዳል፡፡» (ጃፓናዉያን)

«የመጀመሪያው መጠጥ ከውሃ ጋር፣ ሁለተኛው ያለውሃ፣ ሦስተኛው እንደውሃ ይወሰዳል፡፡» (ጃፓናዉያን)


ከዝሙት አበይት መዳረሻ መንገዶች አንዱ ኸምር ነው፡፡ ኸምርን የጠጣ ሰው የአዕምሮ ሚዛኑ ስለሚዛባ ምን እንደሚሠራ በውል አያውቀውም፡፡ ኸምርን የጠጣ ሰው በመጠጡ ተወስዷል፡፡ ከዚህም የተነሳ ማንኛውንም ወንጀል ሊሠራ ይችላል፡፡ በተለይ በመጠጥ ለተወሰደ ሰው ዝሙትን መሥራት የመጀመሪያ ምርጫው ነው፤ ምክንያቱም ልብ በተፈጥሮው ዝሙትን ይፈልጋል፤ ይመኛልም፡፡ በመጠጥ የተወሰደ ሰው ሌላው ቀርቶ ሴት ልጆቹን፣ እናቱንና እህቶቹን ሳይቀር ሊደፍራቸው ይችላል፡፡ አንድ ጊዜ አንዱ ሰካራም ማለዳ ሲነሳ አብረውት የሚኖሩትን እህቶቹን ከቤቱ ያጣቸዋል፡፡ እህቶቹ ግን ትንሽ ቆይተው ወደቤታቸው ተመለሱ፡፡ በዚህን ጊዜ ሰውየው «ከቤት የት ጠፍታችሁ ነው አሁን የምትመጡት?» አላቸው፡፡ እህቶቹም «አንተ እኮ ሌሊት ልትደፍረን ስትመጣብን ሸሽተን ጎረቤት አድረን ነው አሁን የምንመጣው» አሉት፡፡

በኢስላም አስተምህሮት ኸምር የወንጀሎች ሁሉ እናት ናት፡፡ ኸምርን የጠጣ ሰው ማንኛውንም ወንጀል ሊሠራ ይችላል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአንድ ቂሳ(ታሪክ)እንደተወራው አንድ ጊዜ አንዲት መጥፎ ሴት አንድ ሃይማኖተኛ ወንድን አግባብታ ወደቤቷ አስገባችውና ከዚያም «ወይ ከኔ ጋር ዝሙትን ሥራ፤ ወይም ይህንን ሕፃን ልጅን ግደለው፤ አልያም ይህንን ኸምር ጠጣው፤ ነገር ግን ከነዚህ መካከል አንዱንም እምቢ ካልክ እኔ ወዲያው ሊደፍረኝ ወደቤቴ ገባ ብዬ እጮኽብሃለሁ፤ የዛኔ አንተ በሕዝቡ መካከል ትዋረዳለህ፤ ስምህም ይጠፋል» አለችው፡፡

ሃይማኖተኛው ሰውዬም አስቦ አስቦ «ከሦስቱ ወንጀሎች አደገኛነት አንፃር ቀለል ያለው ኸምርን መጠጣት ስለሆነ ኸምሩን ጠጥቼ በዚሁ ልፋታት በሚል ሳቤው ኸምሩን ለመጠጣት ወሰነ፡፡ ከዚያም መጠጡን ቅጂልኝ አላት መጠጡንም ወሰደ፡፡ ሴትዮዋንም ደፈራት፡፡ በስተመጨረሻም ሕፃኑንም ገድሎ ሄደ፡፡ ይህም ነብዩ(ﷺ)ኸምር የወንጀሎች ሁሉ እናት መሆኗን ያስረዱበት ቂሳ ነው፡፡

በጥቅሉ አንዱ ሰው መጠጥን የሚወስድ ከሆነ የኋላ ኋላ በመጠጡ ይወሰዳል፡፡ ከዚህ በኋላ እርሱን የምትመራውና የምትገዛው ኸምሩ ናት፡፡ እርሷም የወንጀሎች ሁሉ እናት በመሆኗ የወሰደችውን ሰውዬ የትኛውም ወንጀል ውስጥ ልትዘፍቀው ትችላለች፡፡ ለዚህም ነው ኢስላም ኸምርን አጥብቆ የከለከለውና ራቁት ያለው፡፡ በቁርኣኑ ውስጥ አላህ(ﷻ)ኸምርን «ሪጅዝ» ማለትም(እርኩስ፣ በካይ፣ ቁሻሻ ብሏታል፡፡ አላህ(ﷻ)እንዲህ ይላል፡-

Surah Al-Ma’idah verses: 90-91

يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّمَا ٱلْخَمْرُ وَٱلْمَيْسِرُ وَٱلْأَنصَابُ وَٱلْأَزْلَٰمُ رِجْسٌ مِّنْ عَمَلِ ٱلشَّيْطَٰنِ فَٱجْتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ إِنَّمَا يُرِيدُ ٱلشَّيْطَٰنُ أَن يُوقِعَ بَيْنَكُمُ ٱلْعَدَٰوَةَ وَٱلْبَغْضَآءَ فِى ٱلْخَمْرِ وَٱلْمَيْسِرِ وَيَصُدَّكُمْ عَن ذِكْرِ ٱللَّهِ وَعَنِ ٱلصَّلَوٰةِ فَهَلْ أَنتُم مُّنتَهُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም ጣዖታትም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፡፡(እርኩስን)ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡ ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል አላህን ከማውሳትና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ(ከእነዚህ)ተከልካዮች ናችሁን(ተከልከሉ)፡፡

በመሆኑም አላህ(ﷻ)ኸምር መጠጣትን እርም አድርጓል፡፡ ወደርሱ ከመቅረብም አስጠንቅቆናል፡፡ ነብዩ(ﷺ)እንዲህ ብለዋል፡-......

👉ኢንሻ አላህ በክፍል ሁለት ይጠብቁን👈

👉 ይ ቀ ጥ ላ ል👈

በግሩፖች ሼር በማድረግ ግዴታችንን እንወጣ
ለመልካም ነገር እንሽቀዳደም በጀነትም ቀዳሚዎች እንድንሆን በአላህ ፍቃድ።

ለኢስላም መስራት ክብር ነው❗️
ለናንተም ክብራችሁ የሆነ ሼር በማድረግ በተግባር ግለፁልን

👉ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር👈


ቀጣዩንና ሌሎችን ተጨባጭ የሆኑ አዳዲስ ደስ ሚሉ ምክሮችን ለማግኜት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
Join us on
telegram channel
👇👇 👇👇👇 👇👇

https://t.me/httpsLatahzen
"ያሱብሀነሏህ" 🎧


وَلَقَدْ زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِمَصَابِيحَ وَجَعَلْنَاهَا رُجُومًا لِّلشَّيَاطِينِ ۖ وَأَعْتَدْنَا لَهُمْ عَذَابَ السَّعِيرِ
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:-
አላህን የሚፈራ ባለው ነገር ላይ የሚብቃቃና
እራሱን የሚደብቅ (ዝቅ የሚያደርግ) ሰው አላህ ይወደዋል።

📚ሙስሊም ዘግቦታል
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የዛሬው የመጅሊስ ስብሰባ ተቋርጧል።
ዶ/ር ጀይላን «ስብሰባው በገለልተኛ አካል ይጣራ!» በማለታቸው ብቻ በቦክስ ተመተው ማይኩን ተነጥቀዋል። ቦክሱ የ"ሙፍቲ" ነው! ይሄ ትልቅ ነውርና ውንብድና ነው።
ኧረ "ሐጂ"! እኔ ጋቢዎን ሲደራርቡ ጊዜ እንኳን በቦክስ በቁንጥጫ የሚማቱ ሁላ አይመስለኝም ነበር! ስንት አመት ቢሰለጥኑ ነው በአላህ? አታለውናል የምር¡
«አገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል!» እንዲሉ፤

እነ "ሐጂ" ሙሐመድ ሣኒ ሐቢብ እና እነ "ሐጂ" ሙሐመድ ወሌ የነበሩበት መድረክ ዑለማን በቦክስ የሚማታ ሰው ተፈጠረበት ማለት ነው? ምን አይነት ዘመን ላይ ደረስን በአላህ?
ዶ/ር ጀይላን ያሉት «ስብሰባው የህግ ጉዳይ ስለሆነ ሰነዱን ያዘጋጁ የህግ ባለሙያው ይምሩት!» ነው። ይህ እንደት በቦክስ ያስመታል? ዑለማእ ይከበር ማለት እንዲህ ነው? Enough is enough!
አላህ አልቀደረልንም ብለን በዉዴታ የምንቀበለው ነገር እንጂ አለፈን ብለን የምንቆጭበት ዕድል የለም።
ጌታዬ ሆይ እኛ የጓጓንለትን ሳይሆን አንተ የተሻለ ነው ያልከዉን ነገር ፃፍልን።
Channel photo updated
    ለምን ተገለበጥሽ እህቴ?
አንቺ ቅኑን መንገድ አውቀሽ የተስተካከልሽ ከዛም መንገዱን ለቀሽ የጠመምሽ ሁኔታሽም የተቀየረ ክልክል በሆነ መንገድ ደስታን እየፈለግሽ ያለሽ እህቴ
ሃቁን ካወቅሽ በኋላ ለምን ዱንያ ልብሽን ቀየረችው ?
  እህቴ ምን አግንቶሽ ነው ምንስ ነው ምክንያትሽ!?

ለምንድን ነው ለሊቱም ቀኑም እኩል የሆነብሽ
ለምንድን ነው ደስታ በጣፋጭ ነገርና በስሜት ውስጥ እየፈለግሽ ያለሽው?
ለምን ለምን እህቴ እስኪ ራስሽን ጠይቂውና መልሽልኝ

እስኪ ንገሪኝ ምንድን ነው ምክንያትሽ ለምን ይሆን በዚህ ርካሽ ዱንያ የተታለልሽው
የዱንያን ፈተና መውጣት የከበደሽ ለምንድን ነው ???

እኔ የአኼራ ወንድምሽ ልረዳሽ እፈልጋለሁ ማለትም ከአላህ በታሽ ሰበብ ልሆንሽ... የአላህም ፍቃድ ከሆነ ያንቺም ፍላጎት ከሆነ

መልዕክቴና ጥያቄየ ከአላህ ርቃችሁ(የአላህን ትዕዛዝ ጥሳችሁ)ሃራም በሆነ ምንገድ ደስታን እየፈለጋችሁ ላላችሁ እህቶች ነው።

Inbox☞ @Nur4843



Join us on
telegram channel
https://t.me/httpsLatahzen
ሴት ልጅ
'''''''''''''''''''
አላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ሴት ልጅን ልዩ አድርጎ ነው የፈጠራት ለመልካም ሴት
ምንም ነገር ስጣተ እሷ አንተ ከስጠሀት የበለጠውን ትስጥሃለች
ቤት ብትስጣት ምቹ መኖሪያ አድርጋ ትስጥሃልች
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ፍቅርን ብትስጣት ንፁህ ልቧን ያለ ስስት ሙሉ ለሙሉ ትስጥሃለች አትክልት
ገዝተህ ብትስጣት ጣፋጭ ምግብ አድርጋ ትስጥሃለች ባልነትህን ብትስጣት
የዐይን ማረፍያና የህይወት ማጣፈጫ የሆኑትን ልጅች ትስጥሃለች እዝነትን
ርህራሄን ብትስጣት ወኔ እና ጥንካሬን በአጥቃለይ የህይወትህን ሙሉነት
ትስጥሃለች የተስጣትን ሁሉ አብዝታና አትረፍርፋ የምትጥ ልዩ የአላህ ቁድራ
መገለጫ <ሴት ልጅ>
""""""""""""
ሴት ልጅን የሚያከብር የለም አላህ ያከበረዉ ቢሆን እንጂ ሴት ልጅን
የሚያዋርድ የለም አላህ ዘንድ የትዋርደ ቢሆን እንጂ አው ከማ ቃለ ረሱሉላህሂ
ስለላሁ አለይሂ ዉስላም (ታላቁ የዕዝነቱ ነብይ ነብዩ ሙሃመድ ስለላሁ አለይሂ
ወስላም)መልካም የሆኑ ዕሴቶች ተጠብቀዉ ጠንካራ ማሃበርስብ እንዲያብብ
ትልቁን አስተዋፅኦ ለምታበረክትው መልካሚቱ እንስት አላህ ራህምቱን ያብዛላት
አሚን



https://t.me/httpsLatahzen
🔥በሚዲያ ፎቶ የመልቀቅ መዘዝ🔥

بــســم الــلــه الــرحــمــن الــرحــيمــ
الحمد الله رب العالمين

አንዲት በእድሜ አነስ ያለች ወጣት እህታችን ነበረች የውሸት ፎቶ ተላከላት ከዛ በፊት አንድ ፕሮግራም ላይ የተነሳችው ፎቶ ነበረ ከዛም አንዱን የሷን ፎቶ ይዘው ከሌላ ከራቁት ፎቶ ጋር አቀናበሩት ማለትም የልጅቱን ፊት ቀርፀው በማውጣት። ከዚያም እነዛ ልጆች ያንን ያቀናበሩትን ፎቶ ወደሷና ወደ ቤተሰቦቿ ላኩት ከዛም ቤተሰቧ ያንን ፎቶ ሲያዩ ልጅቱን አዋረድሽን አሏት አላመኗትም አሰረዳቻቸው ግን አላመኗትም ልጅቱም ማስረዳቱን ቀጠለች እናቴ ሆይ ይሄ የኔ ፎቶ አይደልም ይሄ የተቀናበረ ፎቶ ነው የኔ አይደልም አለቻት ይሄ ፎቶ ተቆርጦ የተቀናበረ ነው አለቻት ግል ልትሰማት ዝግጁ አልነበረችም
የሚገርመው ልጅቱ እድሜዋን ሙሉ ለቤተሰብ ታዛዥ ልጅ ነበረች ግን ሊያምኗት አልቻሉም።
ከዛም ልጅቱ አጭር ደብዳቤ ፃፈችና ከቤት ወጣች

  እንዲህ ይላል እናቴ ሆይ ወላሂ በአላህ ይሁንብኝ እኔ ጨዋ ጥብቅ ነኝ የተመለከታችሁት ፎቶ በፍፁም የኔ አይደለም። ይሄን ፅፋ ከቤት ወጣች
ከሁለት ቀናት በኋላ ራሷን አጠፋች!!
   ሱብሃናላህ!

ውድ እህቶቼ ይህ ዘመን እጅግ በጣም አሰፈሪ ነው የሰው ህይወት እየተቀጠፈ ነው ከዚህ ቀላል የሚመስል ስህተት ልንርቅ ይገባል ስህተት ብቻ ሳይሆን ክልክላትም አለው ለአስፈላጊ( ለመታወቂያ)የመሳሰሉት ነገር ካልሆነ ፎቶ መነሳት አይፈቀድልንም አላህን እንፍራ።

በልጅቱ የተከሰው በጣም ልብ የሚሰብር ነገር ነው አላህ ይጠብቅልን እህቶቻችንን በእውነቱ በጣም ከባድ ፈተና ነው። ይሄ ነገር በኛ ላይ ቢከሰት ተጨናንቀን አላስፈላጊ እርምጃ በራሳችን ላይ እንደምንወስድ ግልፅ ነው ልጅቱ ራሷን ማጥፋቷ ትልቅ ስህተት ቢሆንም ታግሳ ሁሉንም ለአላህ ሰጣ አላህ ለቤተሰቦቿ እውነታውን እስኪያውቃቸው ብትታገስ ጥሩ ነበር ግን አልሆነም! ራስን በኢማን ማነፅ ለዚህ ነው ሚጠቅመው በፈተና ጊዜ ጥንካሬ ይሆነናል ግን በተቃራኒው ጠንካራ ኢማን ከሌለን በትናንሽ ፈተናዎች እንወድቃለን። እናም አላህን ፍርተን ፎቶ ምንነሳ ለአላህ ብለን እንተወው የበለጠ ወንጀልነቱን የሚያብሰው ደግሞ በየ ሚዲያው መልቀቅ ነው።
እናም ፎቷችሁን በየሚዲያው ለቃችሁ ባለ ትዳር ወንድሞችና ያላገቡ ወንድሞቻችንን ፈተና ላይ ከመጣል እንራቅ። ፎቷችን ሚዲያ ላይ በቆየ ቁጥር ወንጀልነቱም ይለጠጣል ምክንያቱም አንዱ አውርዶ ሌላ ሚዲያ ላይ ይለቀዋል ያኔ ያን ፎቶ አይቶት በሚፈተነው ሰው ሁሉ ተጠያቂ ትሆኛለሽ ይሄ ወላሂ በጣም ከድ ነገር ነው ሞተሽ እንኳ ወንጀሉ አይለቅሽም።! እናም ውድ እህቴ ለአላህ ብለሽ የለቀቅሽውን ፎቶ አጥፊ ከጓደኞቻችን ላይ ያለውንም ፎቶ እናስጠፋ አላህን አጥብቀን መያዝ ለራሳችን ነው ሚጠቅመን። ነገር ግን አይ አላህን አንፈራም ካልን አላህ እንደልጅቷ ያለን ክስተት እንዲከሰትብን ማድረግ በጣም ቀላሉ ነው።
እናም ከልጅቱ ህይወት እንድንማር አደራ እላለሁ።

በተቃራኒው ምንለቃቸውን ፎቶዎች ወይም ፕሮፋይላችንን አጫጭር ቁርዓን ሃዲስ የተፃፉ ማስታወሻዎችን ብናደርግ ሰዎች ባዮያቸው ቁጥር አጅር ይኖረናል። እና ይሄ ቀላል ንግድ ነውንዴ ለምን ይሄ ትልቅ አኼራዊ ንግድ ይቀርብናል። ሚዲያን ለዲናችን ብቻ እንጠቀም።

ወንዶችም በሚዲያ ፎቷችሁን ከመልቀቅ ተቆጠቡ ወንዶች በሴቶች ላይ ደካማ እንደሆኑት ሁሉ ሴቶችም በወንዶች ደካማ ናቸው እናም ፎቷችንን ልናጠፋ ይገባል።

ኒቃብ የለበሽ እህቴም ብትሆኚ አንድ ሰው የለበሽው የኒቃብ ፎቶ አይቶ አንቺን ለማናገር ስለሚሞክር ሰዎችን ወደ ፈተና መቀስቀስ ነውና ላይሽን ቁጥብ እንዳረግሽ በሚዲያም ወጠሽ ልታይ ልታይ ማለቱን ልታቆሚ ይገባል።

ወደ ዋናው ርዕሳችን ስንመለስ
ወላሂ የናንተን የፊት ፎቶ ቀርፆ አውጥቶ ሌላ ፎቶ ላይ አድርጎ ማቀናበር በጣም ቀላል ነገር ነው እናም የማንም መጫወቻ ከመሆናችን በፊት ለአላህ ብልን ከዚህ ስራ እንራቅ። ምን አልባት እንደዛ አይነት ክስተት ቢከሰትብን አልሰራነው ብልን ላንጨነቅ እንችላለን ነገር ግን በሰዎች ፊት መጠቋቆሚያ መሆን ሰዎችንም ወደ መጥፎ ጥርጣሬ ገብተው በሃሜት እንዲዘፈቁ ማድረግ ወንጀል ነው። ባጭሩ መዘዙ በጣም ብዙ ስለሆነ ልንርቀው ይገባል ራሳችንን ቁጥብ ማድረግ ሚጠቅመው ለራሳችን ነው ለቤተሰብም ክብር ነው። ውድ እህቴ ቤተሰቦችሽን በመጥፎ ነገር ስማቸውን ማስነሳት ላንቺ ክብር ነውንዴ? ተንከባክበው ያሳደጉሽን ቤተሰቦች የሚገባቸው ይሄ ነው?
ወላሂ አይደለም እምነትሽንም ራስሽንም ቤተሰብሽንም ነው በመጥፎ ምታስጠሪው።
  እናም ውድ እህቶቼ ከዚህ ቀላል መስሎ ወደ መጥፎ መጨረሻ ከሚወስደን ወንጅል ልንርቅ ይገባል ካለፈችው እህታችን ትምህርት እንውሰድ።!!

አላህን እንፍራ ሊያገባሽ የሚፈልግ ሰው እንኳ ቢሆን ፎቶ እንድትልኪ አልተፈቀደልሽም እውነተኛ ሊያገባሽ ከሆነ በቤተሰቦችሽ ፊት ነው ሊያይሽ የሚገባው።

ሌላው ማስታወስ ምፈልገው በፌስቡክም ሆነ በሌሎች ሚዲያዎች ፎቷቸውን ለሚለቁትን እህቶቻችንን ላይክ (like)የምናደርግ ሰዎች አላህን እንፍራ የወንጀለኛ ተባባሪ አንሁን ላይክ ምናደርግ ሰዎች አላህ ይጠይቀናል። ምክንያቱም በመጥፎ ነገር እንዲዘወትሩ እያበረታታናቸው ነው። እስካሁን ላይክ ያደረግን ሰዎች ካለን ከቻልን(አን ላይክ) እናደርግ ከዛም እስካሁን ላይክ ላደረግነው ተውበት ልናደርግ ይገባል።
  ስለዚህ በተቃራኒው በሚዲያ የእህቶቻችንን ፎቶ ስናይ ስለ መጥፎነቱ ወደ አላህንም እንዲመለሱ በጥበብ እንፃፍላቸው።

ውድ እህቴ ለወንድሞችሽ እዘኝ ባንቺ አይፈተኑ! መልክሽን ውበትሽን አይቶ ሚመጣ ወንድ ላንቺ እንደማይጠቅምሽ ማወቅ አለብሽ! ሊዝናናብሽ ሊደበርብሽ ብቻ ነው ሚፈልገው።!ምክንያቱም አላህን አስከፍተሽ መቼም ጥሩ ነገር አይሆንም መጨረሻው። እናም ፎቷችንን ለቀን የሸይጧን ተላላኪ ከመሆን እንቆጠብ ምክንያቱም የሸይጧንን ስራ እያቃለልንለት ነው እና የመጣንበት አላማ ይሄ ነውንዴ እንንቃ እስከመቼ እንዘናጋለን።

(አላህ የበለጠ ያውቃል)
እንመለስ ወደ አላህ
ባረከላሁ ፊኩም

(ወሰለላሁ ዓላ ነብይና ሙሃመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ አጅመዒን)

መልዕክቱን ሼር በማድረግ ብዙ እህቶቻችን አደጋ ላይ ስላሉ  ሼር በማድረግ ሃላፊነታችንን እንወጣ
ቢያንስ ፎቶ ሚለቁ የምናውቃቸው ሰዎች ካሉ ፁሁፍን በመላክ እናስታውሳቸው ከኛ ሚጠበቀው ማድረስ ብቻ ነው አላህ የፈለገው ይመራል የፈለገውን ያጠማል።

Comment↝ @Nur4843

በዱዓችሁ አትርሱኝ

Please
→ ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር←


https://t.me/httpsLatahzen
ኢማም አሕመድ ኢብኑ ሐንበል እንዲህ ይላሉ፦
" ገና በአሥር ዓመቴ ነው እናቴ ቁርኣን ያስሐፈዘችኝ። ለሱብሒ ሶላት ትቀሰቅሰኝ፣ ለከባድ የባግዳድ ብርድ ብላም የዉዱእ ዉሃ ታሞቅልኝ ነበር። መስጊዱ ከቤታችን እሩቅ ስለነበርና ጨለማዉም ስለሚያስፈራ ልብስ አልብሳኝ ሒጃቧን ለብሳ እና በደንብ ተሸፋፍና ወደ መስጊድ ትወስደኝ ነበር።" (አብኑል ቀይም እንዳወሩት።)
ብዙዎቹ የዓለማችን ትላልቅ ሰዎች በእናት እጅ ብቻ ያደጉ ናቸው።
ከራሳቺን ቤት ውጭ ሌላ ሰው ቤት ሰንገባ ከመግባታቺን በፊት ሰላምታ ማቅረብ አለብን !

ልምድ ሆኖብን ዘው ብለን የምንገባ ካለን መታረም ያለበት ተግባር ነው ።

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይለናል

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَدْخُلُوا بُيُوتًا غَيْرَ بُيُوتِكُمْ حَتَّىٰ تَسْتَأْنِسُوا وَتُسَلِّمُوا عَلَىٰ أَهْلِهَا ۚ ذَٰلِكُمْ خَيْرٌ لَّكُمْ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّرُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከምታስፈቅዱና በባለቤቶቿ ላይ ሰላምታን እስከምታቀርቡ ድረስ ከቤቶቻችሁ ሌላ የኾኑን ቤቶች አትግቡ፡፡ ይህ ለእናንተ መልካም ነው፡፡ እናንተ ትገነዘቡ ዘንድ (በዚህ ታዘዛችሁ)፡፡