La tehzen
95 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
አንዱ አላህን ፈሪ ወንድማችን በጣም የሚወዳትን ልጅ እንዲህ ሲል ተሰናበታት

አስተማሪ ነው ኢንሻ አላህ እንደምንጠቀምበት ተስፋ አደርጋለሁ።

📨 እንዲህ እየናፈቅሽኝም ቢሆን ላገኝሽ አልፈልግም
ምክንያቱም እኔ ጌታየን ተገናኝ መሆኔን አውቃለሁ
አውቃለሁም ላስተዳድርሽ አልችልም እንዲሁም ላገባሽ ሀቅም ስለሌለኝ ውበትሽ መፈተኛየ ነው
ስለዚህ ወዳንቺ እየተሳብኩ አንችን ወደኔ አላቀርብሽም ሀራም በሆነ መልኩ ቀርቤሽ ባገኝሽ ተሸናፊው እኔ ነኝ ታዲያ ለምን እቀርብሻለሁ
እናም ወደ ጌታየ ስደትን ስጀምር ስንቄ ተቅዋ(አላህን ፍራቻ) እንዲሆን ፈላጊ ነኝ።
አየሽ አንዳንዱ በገንዘቡ ወዳጆቹን ያቀርባል ሌላው በቁንጅናው ቁንጅናዎችን ይጠራል
እኔ ግን ላንቺ ያለኝን ፍቅር ሰውቼ የጌታየን ፍቅር ማግኜት እፈልጋለሁ
  ብቀርብሽ እንደምትጠጊኝ እርግጠኛ ሁኜ ሳለ እርቅሻለሁ ምክንያቱም እኔ ጌታየን የበለጠ በጥሩ ስራ መቅረብ እፈልጋለሁ
አዎ የእርሱ ፍቅር የእርሱ እርዳታ አንችን እንደሚያስረሳኝ አምኜም ደህና ሁኚ እልሻለሁ
ደህና ሁኚ እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ መንገዴንም ይመራኛል
የአላህ ፍቃድ ከሆነ ዘለዓለማዊ በሆነው ሀገር (ጀነት) እንገናኛለን።
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
አላሁ አክበር❗️

አየህ አንተ የአኼራ ጓደኛየ ስማሽ እህቴ ዱንያ አላታለለችውም ሴት ልጅም አልፈተነችውም

ስማሽ ሰማህ ይሄ ወንድማችን ስሜቱን እንዴት ለአላህ ብሎ መቆጣጠር እንደቻለ
እንማርበት ካለፈው ያልተማረ ሌላ በምን ሊማር ይችላል።
እንደዚህ ወንድማችን ወደ ትዳር መግባት ካልቻልን ከሀራም ፍቅር መራቅ አለብን ለሚያልፍ ስሜት አላህን አናምፀው።
ወላሂ የስሜት ጥፍጥናው ሳያልቅ ምሬቱ ያደፈርሰዋል ማለትም ስሜታችንን ተቆጣጥረን ፈተናውን መወጣት ካልቻልን ባጭር ጊዜ አላህ ብቻ የሚያውቀው ጭንቀትና ቁጭት ነው ሚለቅብን እና ስሜታችንን እናሸንፈው።
አንተ ወንድሜ አንቺም እህቴ ዱንያ ናት አውቃለው ወጣትነት ፈተናው ከባድ ነው ግን ከአላህ ያለውን ውድ ሀገር ጀነት ለሚፈልግ ፈተናዎቹ ቀላል ናቸው ምክንያቱም ክፍያው ውድ እንደሆነ ያውቃል ክፍያዋም ጀነት ናት። ይህቺ እድሜ ደግሞ ተመልሳ አትመጣም።
ደስታ በሃራም ፍቅር ውስጥ ትንሽና ጊዜያዊ ነው እኛ ግን ትልቅ ደስታ እንዳለ ነው ምናስበው ግን በጣም ትንሽ ነው ከግዜ በኋላ አላህ ብቻ የሚያውቀው ጭንቀትና ቁጭት ነው ሚለቅብን ለምን ይሄን አደረኩ ለምን ለምን እያልን እራሳችንን መውቀስ እንጀምራለን ምክንያቱም የሸይጧን መንገድ ነው።
ወላሂ ምንም ኸይር ነገር የለውም
ልብ ማድረቅ ግዜን መግደል ገንዘብ ማጥፊያ አላህን ማመፅ ብቻ ነው ትርፉ።
ግን ይሄን ፈተና አላህ ካዘነላቸው በቀር ፈተናውን ይወድቃሉ ሸይጧንም ይስቅባቸዋል።

እና ስሜታችንን ያዝ አድርገን ጀነትን በማሰብ ወጣትነታችንን እንጠቀምበት አላህን የበለጠ ለማወቅና ለመገዛት ጀነትንም ለመውረስ እንቻኮል።
  ፍቅር ወዳቂ ነው የአላህ ፍቅር ግን ሁሌም ህያው ነው በሁለቱም ሀገር አይወድቅም።
ወላሂ በሃራም ተነካክተህ ተነካክተሽ ትዳር ውስጥ ብትገቢም አላህ ለትዳርሽ ጥፍጥና አይሰጥሽም እና እንዴት ነው ልጆችሽን በንፁህ መንፈስ ማሳደግ ምትችይው
ልጆችሽ ያንችን በሀራም ያሳለፍሽውን አይነት ጊዜ እንዲያሳልፉ ትፈልጊያለሽ አትፈልጊማ እና እራስሽን ሳታስተካክይ እንዴት ነው ልጆችሽን ማስተካክል የምትችይው አንተስ ወንድሜ እንዴት ነው ቁጥብ የሆኑ የዚህ ዲን የበላይነት የሚያስመልሱ ልጆችን ማፍራግ ምትችለው በዚህ በሀራም መንገድ ተገናኝተህ።

  እስኪ ጠንካራ እንደሆንሽ ለውስጥሽ አሳምኝውና ከዚህ የሃራም ፍቅር ውጪ ወይም ባስቸኳይ ወደ ትዳር ቀይሪው።
ወላሂ አላህ ያግዝሻል እስካሁን የሰራሽውንም ወንጀል አላህ ይምርሻል ወደ አላህ ከተመለሽ። አስታውሽ እህቴ አስታውስ ወንድሜ ከወንጀል የተመለሰ ልክ ወንጀል እንደሌለበት ነው ኧረ እንደውም አላህ ይደሰትበታል።
አላህ ተመላሾችንና ተጥራሪዎችን ይወዳል።

👉 ጓደኛሽ ወይም በሃራም ፍቅር አብሮሽ ያለው ሰው ጠንካራ ሁኖ እራሱን አሸንፎ ከዚህ የሃራም ፍቅር ሊያስወጣሽ ካልቻለ አንቺ ጠንካራ ሁነሽ ለመራቅ ሞክሪ
ይሄን ስታደርጊ ጓደኛሽ ከተቃወመሽ ከጠላሽ ከመጀመሪያውም አይወድሽም ማለት ነው ግን ይሄን ስታደርጊ ደስተኛ ሁኖ ወደ ሀላል(ትዳር) ለመቀየር ከቻለ የእውነት ይወድሻል ማለት ነው።
ወይም ሊያገባሽ ሳይችል ቀርቶ ግኑኝነቱን ካቆመ ይወድሻል ማለት ነው ምክንያቱም ወደ አላህ እያቃረበሽ ነው።
እና በዚህ ማረጋገጥ ትችያለሽ ግን ብዙዎች ለሀራም ነገር እስከሚያመቻቹሽ ድረስ ነው አብረውሽ ያሉት።
☞ የቀረውን እናስተካክል ያለፈውን ይምረናል ካልሆነ ግን ባለፈውም በቀረውም እንያዛለን።
  እንቻኮል ወደ አላህ ባረከላሁ ፊኩም።

ወሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ


ለምንድን ነው ኢስላማዊ መልዕክቶችን ሼር ለማድረግ የምናፈረው በሀይማኖታችን እናፍራለን እንዴ
አናፍርማ ስለዚህ ይሄን መልዕክት ብቻ ሳይሆን የምናገኘውን ጠቃሚ የምንለውን መልዕክቶች ሼር ማድረግ እንልመድ።

እስኪ በውጥ መስመር ለምናውቃቸው ለምንወዳቸው ሼር እናድርግላቸው አይታወቅም ወደ አላህ የመመለሳቸው ሰበብ ልንሆን እንችላለን።
የፈለገውም የሚመራው የፈለገው የሚያጠመው አላህ ብቻ ነው ከኛ ሼር በማድረግ ሰበቡን ማድረስ ብቻ ነው ሚጠበቀው።


coment ⇝ @Nur4843
ይቀላቀሉን ባለንበት ተጨባጭ በሆኑ ነገሮች ላይ እንመካከር
👇👇👇👇
https://t.me/httpsLatahzen
ያስጨነቀንና የከበደን ነገር ሁሉ ወንጀላችንን ጠርጎልን ይሄዳል።
ይህንንም እያሰባችሁ
አልሐምዱ ሊላህ በሉ።
ድል ማለት ዉስጥህ ብዙ ጦርነት እየተካሄደ ቀና ብለህ የምትሄደው፣ በጎ መስለህ የምታየው ነገር ነው።

ደግሞ ለዱንያ
ቲ።
° ዝሙት በባህሪው እንስሳዊ ወንጀል ነው፡፡ ግለሰቡም ዝሙት ላይ የሚወድቀው ሥጋዊ ፍላጎቱ
ከሕሊናው መሪነት ውጭ ሲሆንበት፣ ፆታዊ ርሀቡ አያሎበት ሲገኝና እራሱን መቆጣጠር ሲያቅተው ነው፡፡ በውጤቱም በዝሙት ጊዜ የግለሰቡ መንፈሳዊና አዕምሯዊ ጎኖች በሥጋዊ (እንስሳዊ) ጎኑ ይሸነፋሉ፤ ይደፈጠጣሉ፡፡ አላህ (ሱብሃነ ወተዓላ) ያስቀመጣቸው የወሲብ ሕግጋት ይጣሳሉ፡፡ የወሲብ ዓላማና ግቡ ይቀለበሳል፡፡ ልክ ግለሰቡ አምላካዊውን ድንበር መተላለፍ ሲጀምር መንፈሳዊ ጎኑና ሕሊናዊ
ምሪቱ ዕረፍት ይወጣሉ፤ እንስሳዊ ባህሪው ግን እርሱን ይቆጣጠረዋል፡፡ በዚህን ጊዜ ግለሰቡ የሕሊና እስረኛ ይሆናል። ለዚህም ነው ዝሙት ለሕሊና እስራት ያጋልጣል፤ ብሎም ዚና እንስሳዊ ኃጢአት ነው የሚባለው፡፡ እናም ዝሙትን ሠርተው የሕሊና እስረኛ ከመሆን በግፍ ዘብጥያ ወርደው አካላዊ እስራትን መቀበል ይሻላል። ምክንያቱም እንደ ንጹሕ ሕሊና ሰላም የሚሰጥ ነገር የለምና፡፡




#ለወዳጀዎ_ያካፍሉ

Join us on
telgram channel ↷⇙
https://t.me/httpsLatahzen
ወቃሽቷ ነፍስ

ዛሬ ገብተህ ከሙስሊሞች ተጎራብተህ
ሶላት ይዘህ ከጎናቸው ተጎናብሰህ
ረሃብ ጥማት በፆም ሰበብ ተጎንጭተህ
ሙስሊም ሁነህ በተግባርህ አስመስክረህ
እንዳትወጣ ከዚህ ኒዕማ ነክሰህ ያዘው
ልፋት ጥረት ውጤትህን አታራክሰው
የትናንቱን አምላክህን ነው ዛሬ ደርሰህ ያመለከው
ነገም ከርሞም የነበረው የሚኖረው ሁሌ ህያው
እጅ እንዳትሰጥ ለስሜትህ አታስቀጣኝ በስህተትህ ወቅስሃለሁ እኔ ነፍስህ
አታስወጣም ከራህመቱ ሰልችቶኛል መወስለቱ
ከኢባዳ መራቆቱ ከዋጅባት መጣላቱ ከሱና ጋር መጋጨቱ እስከመቼ ልሁን ከንቱ ጠቅሞኝ ሳለ መመራቱ
አሻፈረኝ ብየሃለው እኔ ነፍስህ  አታስቀጣኝ በመታዘዝ ለስሜትህ
ነገም ዛሬም የምቀጣው እኔ ሳለሁ ስለምንስ አትሰማኝም ወቅስሃለው
እኔ ወቃሽ ነፍስህ ይሄው ይዤሃለው
ከገሃነም ከቀብር ውስጥ ከዱንያም ፈተናዎች አታስቀጣኝ ራህመት ፈልግ ከአረህማን አትሰላች ዛሬ ገብተህ ሰጋጅ ሁነህ ጷሚ ሁነህ ከሷሊሆች ተጎራብተህ በዚህ ቀጥል አንተ በኔ ትድናለህ

አሁን አወክ የስሜትና የአቅልህን ማንስ ወዴት ምስን ወዴት ሚመራህን ንቃ ተከተለው ዛሬ ለዚህ ያበቃህን ወደ እውቀት ወደ ተውሂድ የመራህን ወደ ሶላት ወደ ሲያም ያቅጣጨህን የአረህማን ትዕዛዛትን የረሱልን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ፈለጎችን ተቀብሎ በተግባር ላይ ያዋለውን የረካውን በዚክሪላህ ተከተላት ወቃሽ ነፍስህን

share share share
join us on
telegram channel

https://t.me/httpsLatahzen
አዲስ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባቹ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ:
-- @kjumj_official_bot--
Barattota haaraa UNIVERSITY JIMMA isin gahee hunda:-
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

እንደሚታወቀው ዩኒቨርሲቲያችን ግንቦት 04 እና 05 መጥራቱ ይታወቃል ስለዚህ ወደ ግቢ ስትመጡ ያለምንም መንገላታት ለመቀበል ሙስሊም ተማሪዎች ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቀው እናንተ በጉጉት እየጠበቁ ነው።
በነዚህ ስልክ ቁጥሮች ወንድሞች ማግኝት ትችላላቹ።
Akkuma beekamu Yuunivarsitiin Jimmaa Barattoota haaraa bara 2014 MoE irra gara JU tti ramadamtaniif waamicha kan taasisee Caamsaa 04 fi 05 tahu isaa kan beekamudha kanaaf JAMA'AN BARATTOTA UNIVERSITY JIMMA isiin simachuf qophii isaa xumuratee haawwiin isiin egaa jira .
®Main campus®
~ማዕሩፍ ሰዒድ-MARUF SAID - 0945020813
~አወል ኸድር ~AWOL KADIR-0910502916
~አብዱልአዚዝ ኢድሪስ~ABDULAZIZ IDRIS - 0949916760
ሙሀመድ ጀማል ~MOHAMMED JEMAL- 0910857885
®JIT CAMPUS ®
~አንዋር መሀመድ ~ANWAR MOHAMMED - 0920886879
~ሲቶሌ አባስ ~SITOLE ABAS- 0972180276
~አብደላህ ሸምሰዲን ~ ABDALLAH SHAMSUDIN- 0948780414
®AGRI CAMPUS ®
-ሚፈታህ ጀማል ~MIFTAH JAMAL- 0930474983
-ጁድ አህመድ ~JUD AHMAD - 0960238991
ስለየትኛውም መረጃ ትብብር ለምትፈልጉ
ወንድም እህቶች በነዚህ ስልክ ቁጥር ደውሉ።
*ለበለጠ መረጃ ይህን ቦት ተጠቀሙ
*fresh ተማሪዎች በዚህ bot መመዝገብ ትችላላችሁ
*Barattonni #Fresh taatan Bot ii jama'a kanaan #galmaa'u ni dandessan.
--------------
@kjumj_official_bot
--------------
*Main campus ለምትመጡ ተማሪዎች جماعة طلاب المسلمين بجامعة جما JUMJ ተብሎ የተፃፈበት ነጭ ቲሸርት አርገን እንቀበላችሁዋለን።
*Main campus barattota galtaniif T-shirt جماعة طلاب المسلمين بجامعة جما JUMJ kan jedhu, uffannaa kanaan kan isiin simannu ta'u isiin beksifna.
*Yeroo dhuuftan odeffannoo barbaaddan argachuufi akka hin rakkaneef bilbila Amiroota Jama'a kana fayyadamaa.

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ
JAMA'A BARATTOOTA YUNIVERSITII JIMMA

#Share #Share waliif godhaa!
@jumjofficialpage
https://t.me/JUMJk_Da3wa
https://t.me/KjumjVoice
①) አሶሳ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀማዓህ የአዲስ ተማሪዎች ተቀባይ አድራሻ
1)Esmael Abdulbaki
0925030233
2)Mehamednur Hussen
0989528016
3)Abdusemed Teka
0930652939
4)Nureye Hussen
0942752791
5)Akeml Rebumachalla
0934185499
የትኛውም አይነት ጥያቄ ስለ አሶሳ ግቢ /ከተማ ከላይ ባሉት ስልኮች መጠየቅ ይቻላል!
*
②) ጎንደር ዩኒቨርስቲ ጀማዓህ (ደግሞ እናንተንም እንዳይገድሏችሁ ተጠንቀቁ!)
TEWEDROS CAMPUS
1 seid abinew 0989370406
2 Ahmed hassen 0941960801
3 Abdussomed 0941204863

FASIL CAMPUS
1 Hassen yusuf 0936434810
2 Ahmed habib 0980269031
*
③) ጂማ ዩኒቨርስቲ ጀማዓህ
አዲስ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባቹ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ:—

አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ።እንደሚታወቀው ዩኒቨርሲቲያችን ግንቦት 04 እና 05 መጥራቱ ይታወቃል ስለዚህ ወደ ግቢ ስትመጡ ያለምንም መንገላታት ለመቀበል ሙስሊም ተማሪዎች ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቀው እናንተ በጉጉት እየጠበቁ ነው።
በነዚህ ስልክ ቁጥሮች ወንድሞች ማግኝት ትችላላቹ።
Main campus
ማዕሩፍ ሰዒድ 0945020813
አወል ኸድር 0910502916
አብዱል አዚዝ ኢድሪስ 0949916760
ሙሀመድ ጀማል 0910857885
JIT CAMPUS
አንዋር 0920886879
ሲቶሌ አባስ 0972180276
አብደላህ ሸምሰዲን 0948780414
AGRI CAMPUS
ሚፈታህ ጀማል 0930474983
ጁድ አህመድ 0960238991
ስለየትኛውም መረጃ ትብብር ለምትፈልጉ
ወንድም እህቶች በነዚህ ስልክ ቁጥር ደውሉ።
*ለበለጠ መረጃ ይህን ቦት ተጠቀሙ @kjumj_official_bot
*Main campus ለምትመጡ ተማሪዎች جماعة طلاب المسلمين بجامعة جما
JUMJ ተብሎ የተፃፈበት ነጭ ቲሸርት አርገን እንቀበላችሁዋለን።


የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ




ያልላካችሁ ላኩ!
لا تنظر إلى صغر المعصية ، ولكن انظر من عصيت .

『የወንጀሏን ትንሽነት አትመልከት ይልቁንስ ማንን እንደወነጀልክ ተመልከት』እህቴ አንቺም እንደዛው
ከዕብ ኢብኑ ማሊክ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና እንዲህ ይላል:-
"ነገር ማዋሰድን ተጠንቀቁ ነገረኛ ሰው ከቀብር ቅጣት አያርፍምና።"
ምንጭ:-📚الموسوعة 405/4
🔰 #የእጁጅ_ወመእጁጅ

🔷 ክፍል #ሰባት 7⃣

ለዙል ቀርነይን፦ አንተ ማነህ!!! እኔ የት ነዉ ያለሁት! እያለ ማዉራት ጀመረ።
ይሁን እንጂ ዙል ቀርነይን የአይጁርን ንግግር አይረዳምና በጥሩ ሁኔታ መሆኑን እንዲገነዘብ ብቻ እጁን በአይጁር ራስ በማሳረፍ አሻሸው፡፡

በመቀጠልም ዙል ቀርነይን ወታደሮቹን ለአይጁር ምግብ እናመጠጥ እንዲያቀርቡለት አዘዛቸው፡፡ አይጁርም የቀረበለትን ምግብ እየተመገበ ማን ነዉ ይሄ ሰዉ እንዲ ሚንከባከበኝ በማለት እያሰላሰለ የቀረበለትን ምግብ መመገብ ጀመረ፡፡
ምግቡን በልቶ እንዳጠናቀቀም ዙል ቀርነይን እንዲያርፍ በእጁ ካመላከተዉ በኀላ አይጁር አረፍ ሲል ዙል ቀርነይንም ከጎኑ ተቀመጠ፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉም በድንገት ከቤተ መንግስት ሰዉ በመምጣት የሀገሩ ዑለማዎች እንደመጡና የመግባት ፍቃድም እንደሚጠይቁ ነገረዉ፡፡ ይህን ጊዜ ዙል ቀርነይን አይጁርን እንዲተኛ በእጁ አመላክቶት ወደ እንግዶቹ በመሄድ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አድርጎላቸዉ ክስተቱን ከመጀመሪያዉ እስከ መጨረሻው ተረከላቸዉ የንጉሱ ገዳይ እና የያእጁጃዉያኑ ወጣትም እዚህ እንደሚገኝ አክሎ ነገራቸዉ፡፡
በመቀጠልም፦ ስለዚህ ፍጥረታት የምታዉቁት ነገር ምን አለ በማለት ጠየቃቸው፡፡
በመካከላቸዉም አንድ እጅግ በእድሜ የገፋና በእዉቀትም የበለፀጉ አዛዉንት ነበሩና እንዲህ በማለት ንግግራቸዉን ቀጠሉ፡፡
አንተ መልካም ንጉስ ሆይ!! እነሱ የእጁጅ እና ማእጁጅ የሚባሉ ነገዶች ሲሆኑ እጅግ አላህን በማምለክ ጥሩ የአላህ ባሮች ነበሩ፡፡
በመሀከላቸዉም ያጁስ እና ማጁስ የተባሉ ከሀዲያን እና ድግምተኛ ወንድማማቾችም ነበሩ፡፡
ያጁስ የተባለው፦ድግምቱን ተጠቅሞ ህዝቦቹን ወደ ፀሀይ አምልኮ በመጥራት ለተከታዩችም ግዙፍ የሆነ ቤተ አምልኮ ገንብቶ በኩፍር ጎዳና አንቧቧቸዉ፡፡
ማጁስ የተባለዉ ደግሞ የወንድሙን መመለክ እና በህዝቡ አንደበትም መቀደስን ሲመለከት ቅናት በልቡ አደረበትና የተቀሩትን ህዝቦች እሳትን እንዲያመልኩ ጥሪ

አዛዉንቱ ንግግራቸውን ቀጥለዋል፦ በዚህ ሁኔታ ከፊሎቹ የፀሀይ አምላኪ ሆነዉ ከፊሎቹ የእሳት አምላኪ ሲሆኑ የተቀሩት ጥቂቶቹ ደግሞ በኢማናቸዉ ላይ ፀኑ፡፡
የነዚህ በኢማን መፅናት እረፍት የነሳቸዉ ያጁሳዉያን እና ማጁሳውያን አንድ ላይ በመተባበር በሙእሚኖቹ የድግምት ናዳዎችን ያዘንቡባቸዉ ጀመር፡፡ ይሁን እንጂ ሙእሚኖቹ የድግምቱ መደጋገም ከኢማናቸዉ ፍንክች አላደረጋቸዉም ነበር፡፡
በመጨረሻም የሙእሚኖቹን ልጆች በወላጆቻቸው ፊት እያረዱ ወደ ኩፍር ቢያስገድዷቸዉም እምነታቸዉ ይበልጥ መጠንከር ሲጀምር በዘመኑ የነበሩትን ሙእሚኖች ባጠቃላይ በእሳት አቃጥለዉ ደመሰሷቸዉ በማለት ሽማግሌዉ ንግግራቸዉን ሳይጨርሱም ዙል ቀርነይንም፦ ከዚያስ ምን ተከሰተ? በማለት ጠየቃቸዉ፡፡
እሳቸዉም፦ "ከዚያማ አላህ የእርግማንን አይነት ካወረደባቸዉ በኀላ ከሰዉ ዘር ባጠቃላይ የተገለሉ በማድረግ ጨለማን መቀመጫቸዉ....እሳትን ደግሞ መደንበሪያቸዉ ......ሰውነታቸው ደግሞ ቅርፅ አልባ አድርጎ ፀሀይ ሰውነታቸዉን ቀነካ ቁጥር እንዲያቃጥላቸዉ ወሰነባቸው፡፡ በማለት ነገሩት
ዙል ቀርነይንም ግራ በመጋባት፦እንዴት ይህ ሊሆን ይችላል? በሰሞኑ እኮ 10-11የሚሆኑት ወደ ምድር ወጥተዉ ከኛም ተቀላቅለው ነበር፡፡ ግን ፀሀይ ሲያቃጥላቸው አላየንም ሲል ጥያቄ አቀረበ?
አዛውንቱም ይህማ በጭራሽ አይሆሆንም፡፡ እስቲ እናንተ ዘንድ ያገታችሁትን ወጣት አይጁር አሳዩኝ ብለው ጠየቁ፡፡
ከዚያም ዙል ቀርነይን እና አዛውንቱ ወደ አይጁር ክፍል ሄዱ፡፡ በእንቅልፍ ላይ ያለዉን አይጁርን ሲመለከቱት ይህ እንኳን ያእጁጃዊ አይደለም፡፡ ግን ዘረ ቅይጥ ነው አሉ፡፡
ዙል ቀርነይን ይሄ ወጣት የተያዘ እለት ሰዎች ይዘው በወጡት የጧፍ ብርሀን ምክንያት እራሱን ስቶ ነበር አላቸው፡፡
አዛውንቱም አይ ተመሳስሎበት ነው፡፡ ያእጁጃዉያኑ በብርሀን ሲያስፈራሩት ሴላደጉ ነው፡፡ አሉት
ዙል ቀርነይንም ገባኝ ግን ቋንቋቸው ሊገባኝ አልቻለም አላቸው፡፡
አዛውንቱም እኔ ስለማቀው አስተምርሀለው አሉት፡፡
በመቀጠልም ዙል ቀርነይን ወደተቀሩት ኡለማዎች ዘንድ በመሄድ የሚከተለውን ጊዜያዊ አዋጅ አፀደቀ፡፡
1.እነዚየያን ሰዎች ለምንም አይነት ፀብ አንጋብዛቸውም ምክንያቱም በብልሀት ሆነ በጉልበት ከኛ ይበልጣሉና፡፡
2.ከክህደታቸው እንዲመለሱ ጥሪ ማድረግ፦ ጥሪያችንን ካልተቀበሉ ውሳኔው የኛ ይሆናል፡፡ በማለት ትዕዛዙን ካስተላለፈ በኀላ የመጡት ኡለማኦች ተስማምተው፦ ይህ ጉዳይ መቋጫውን ሳያገኝ ወደ ሀገሮቻችን አንመለስም አሉ፡፡
ዙል ቀርነይንም በመቆየታቸው የተሰማውን ደስታ ገሐፆላቸው ለሦስት ቀናት ግን ከአዛውንቱ ማሳለፍ እንደሚፈልጉ ነግሯቸው ቋንቋቸውን ለመማር ከአዛውንቱ ጋር ሆነ፡፡
አይጁር በክፍሉ ሆኖ ሳለ በወታደሮቹ በሚመጣለት ምግብ እና መጠጥ በጣም በመገረም ለምንድነው እነዚን ህዝቦች ያለ ምክንያት የምጠላቸው???
እነዚ ህዝቦች መጥፎ ቢሆኑ እኮ ለንጉሳቸው በቀል ሲሉ ጭንቅላቴን ይቆርጡት ነበር፡፡
ስለዚህ
ውሳኔ ከመወሰኔ በፊት ቀጥልቀት ማሰብ ይኖርብኛል በማለት ከራሱ ጋር አወራ፡፡
ዙል ቀርነይንም ለተከታታይ ቀናት ቋንቋቸውን በሚገባ ከአዛውንቱ ከተማሩ በኀላ አይጀጁር የተኛበት ክፍል በመግባት አይጁርን በተማረው ቋንቋ ሰላም ባንተ ላይ ይሁን አለው፡፡
አይጁርም በድንጋጤ ዙል ቀርነይንን እያየ፦ ይህ ያእጁጃዊ ነዉ ወይስ አይደለም፡፡ በማለት እያሰበ ሰላምታውን መለሰለት፡፡
ዙል ቀርነይንም፦ ልጄ ሆይ ከአላህ ሌላ ማን አለ?እሱ እኮ አንዱ እና ብቸኛው ነው፡፡ ወገኖችህም እኮ አላህን በብቸኝነት አምላኪ ነበሩ፤ በመጨረሻም የማይጠቅምን ነገር አማልክት አድርገው ያዙ፡፡ አለው
ይህን ጊዜ አይጁር በመገረም ዙል ቀርነይንን እየተመለከተ፦ስለ ህዝቦቼ ምታቀው አለ ሲል ጠየቀው፡፡

Part ➑
ይቀጥላል....
ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ
~
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጀመሪያ አመት ተማሪዎችን (ፍሬሾችን) እንደ እናትና አባት ሆነው የሚቀበሉ የሱና ወንድምና እህቶችን ስልክ ቁጥርና ሙሉ አድራሻ ለማግኘት ከታች ያለውን ቻናል ይቀላቀሉ !!!

👇

https://t.me/Daewa_selefya_beuniversity

👆አዲስ ለሚገቡ share አድርጉላቸው

Follow the sunnah !!!!!

https://t.me/Daewa_selefya_beuniversity