La tehzen
94 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
አሏህ ሱበሀነሁ ወተዓላ በተከበረው ቃሉ እንድህ ይላል፦
۞ وَسَارِعُوا إِلَىٰ مَغْفِرَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا السَّمَاوَاتُ وَالْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡
(ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 133)

ዛሬ በማያልቀው ገዘባችን ለመልካም ስራ እንሽቀዳደም ።።።።።
Channel photo removed
💎ለሌሎች መልካም በመሆንህ ከአንተ ነገር ላይ ምንም አይቀንስም፡፡
🍂ለሌላቸው ሠዎች ካለህ ላይ ቆንጥረህ በመለገስህ ከአንተ ሀብት ላይ ምንም አይቀንስም እጥፍ ድርብ አርጎ ይዞልህ ይመጣል እንጂ፡፡
🍂ምንጊዜም ለሌሎች መልካም ነገሮችን በሰራህ ቁጥር መልካም እና ውብ ነገሮች ወደ አንተ ይመጣሉ፡፡አትጠራጠር
በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጊዜ በተደጋጋሚ አስካሪ መጠጥ እየጠጣ እርሳቸው ፊት በመቅረብ ቅጣት የሚፈጸምበት ሰው ነበር። አንድ ዕለትም እንዲሁ ጠጥቶ በመገኘቱ ግርፋት ፈርደውበት ቅጣቱ ተፈጸመበት። እዚያ ከነበሩ ባልደረቦቻቸው የተወሰኑት “አላህ ያዋርድህ…!” ወዘተ. እያሉ ተራገሙ። ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግን በዚህ አባባላቸው አልተደሰቱም። በመሆኑም፣ “በጓደኛችሁ ላይ ሰይጣንን አታግዙ፤ ከዚያ ይልቅ ‘አላህ ይማርህ፣ አላህ ቅናቻን (መመራትን) ይስጥህ’ ብላችሁ ዱዓእ (ጸሎት) አድርጉለት” በማለት ገሰጿቸው።
ሶደቃ
~
ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
"ወንጀሎችህ ከበዙ ሶደቃ አብዛ። ወንጀሎችን ታጠፋለችና።"
📚 [ሸርሑል አርበዒነ ነውዊያህ፡ 361]
=
ረመዷን ያልተቀየረ መቸ ነዉ የሚቀየረዉ ??
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

📣 ትላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↩️↩️


ጉራጌ ዞን በጉቴ መስጅድ እና በገርቢቻ መስጅድ ነገ የጁመአ እለት በሱና ኡስታዞቻን ደምቀው ይውላሉ


ነገ ጁመአ ቀን 06_08_14 ከጁመዓ ሶላት ከመሰገዱ በፊት ተጀምሮ ቀኑን ሙሉ ዳእዋ ይደረጋል ።

እዛ የሚሄዱ ኡስታዞች

👉ኡስታዝ ሳዳት ከማል ሀፊዙሁሏህ

👉ኡስታዝ አብዱ ናስር ሀፊዙሁሏህ

እንዲሁም ሌሎችም ኡስታዞች ይገኛሉ ሸር አድርጉት
⇛የደስታ ማግኛ መንገዶች ብዙ ናቸው። ከሁለም የሚልቀው ግን የእናት አባት ዱዓ ነው።

⇛ደስታችሁ ይበዛ ዘንድ ዱዓቸውን ፈልጉ። √በተለይ በዚህ በተከበረ ወር…!
➡️ጀግኖች የሰለፍ እንስቶች💎

💎(የዐቂዳን ጉዳይ ከሂወት አስበልጠው የሚያዩ)

➤የታላቁ ሰለፍ (አሲም ኢብኑ ዐሊይ) ሁለት ሴት ልጆቹ ደብዳቤ ፅፈው ወደርሱ ላኩለት ፡

➤ደብዳቤው እንዲህ ይላል ፡- አባታችን ሆይ ! ሙእተሲም የተባለው መንግስት ኢማሙ አህመድን (ቁርአን ፍጡር ነው እንዲል አስገድዶት ስላልተቀበለውና ቁርአን ፍጡር ነው ስላላለለት እንዳሰረውና በጅራፍ እንደገረፈው ዜናው ደርሶናልናልና) ፡ ይህ መንግስት (ሙእተሲም) ልክ እንደ ኢማሙ አህመድ ቁርአን ፍጡር ነው እንድትል ካስገደደህ አላህን ፍራ እንዳትቀበለው ! እሺ እንዳትለው ! ፈፅሞ ቁርአን ፍጡር ነው እንዳትልለት !

➤ከዚያም እንዲህ አሉ፡- በአላህ ስም እንምላለን ! አንተ ቁርአን ፍጡር ነው ብለሃል የሚለው ዜና ከሚመጣልን ቁርአን ፍጡር አይደለም በማለትህ ቢገድልህና የሞትህ ዜና ቢመጣልን ይሻለናል ፡፡

ምንጭ፡- ተህዚቡል ከማል ( 514-13 )
ያንን ቀን ( አኺራን ) እንፍራ

በጣም አጭር ማስታወሻ
ዑመር ኢብኑልኸጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ይላሉ፦ "ከሰማይ 'እናንተ ሰዎች ሆይ! ሁላችሁም ሙሉ ለሙሉ ጀነት ትገባላችሁ አንድ ሰው ሲቀር' የሚል ተጣሪ ቢጣራ ያ አንዱ ሰው እኔ እንዳልሆነ እሰጋለሁ፡፡"
(አልሒልያህ፡ 1/73)
የጃሒል ክብረትና የቁልቋል ፍሬ አንድናቸው !!!!

ሳይነኳቸው ይረግፋሉ!!!
በቀን አምስት ጊዜ ከሚሕራብ የሚተላለፍ አዛን ጥሪው እኮ ላንተ ነው። ጠርቶህም በቤቱ እንድታገኘው እየጠበቀን ነው። ስለምን እገሌ አልደወለልኝም ብለህ ታለቅሳለህ?
መጀመሪያ ለአዛኑ ጥሪ ምላሽ ስጥ።

ረመዷን 14
❝ሶላት- የወደቀን ሰው ልብ ታነሳለች። ኑ ወደሶላት•••❞

#ሰላትን በመስጂድ


High copy😁
“አሰላቱ ኸይሩን ሚነ ነውም” “ሰላት ከእንቅልፍ ትበልጣለች”
“አሰላቱ ኸይሩን ሚነ ነውም” “ሰላት ከእንቅልፍ ትበልጣለች”

#የፈጅርንሶላት_በመስጂድ
❝ወደፈጅር ሶላት የሚደረግ የጨለማ ጉዞ፤ ቀንን ብሩህ ያደርጋል።•••❞ ቀናቸው ብሩህ፣ የፈካ፣ በደስታ የተዋበ ከሚደረግላቸው ባሮች አሏህ(ሱ.ወ) ያካተን። አሚን።

#የፈጅርንሶላት_በመስጂድ
ዛሬ ቀኑ ጁመዓ ነው ወሩ ደሞ ረመዷን ነው።

⇛ለኛ ሲሉ ብዙ የተሰቃዩ እና ለተቸገሩት በሆኑት በ ውዱ ነብያችን ﷺ ላይ ሰለዋትን አብዙ…!!
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ
· ➪ ጁመዓ!!!
--------------------==>

۞ የጁምዓ እለት የሳምንቱ
ምርጥ ቀን ነው።

የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አላህ ዘንድ ከቀናቶች ሁሉ በላጩ የጁምዓ እለት ነው።» ብለዋልና በዚህ እለት ስራዎቻችንን ይበልጥ ማሳመር ይገባናል።
#صححه الألباني في
السلسلة الصحيحة - رقم: (1502)
صحيح الجامع -  رقم: (1098)

➪የጁምዓ እለት በጀማዓ (በህብረት) የተሰገደ የፈጅር ሰላት ከየትኛውም ወቅት ሰላት በላጭ ነው።

𑁍 የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አላህ ዘንድ በላጩ ሰላት በጁምዓ እለት በጀማዓ የተሰገደ የሱብህ ሰላት ነው።» ብለዋልና ከየትኛውም እለት በበለጠ ቀድሞ ለመገኘት መጣር ይበልጥ ያስመነዳል።
#السلسلة الصحيحة -
الألباني صحيح - رقم: 1566

۞የጁምዓ እለት ከሌሎች ቀናት በበለጠ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋት የማውረጃ ቀን ነው።

︎ የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ። በኔ ላይ አንዴ ሰለዋትን ላወረደ አላህ በሱ ላይ አስር ያወርዳል።» ብለዋልና ትንሽ ሰርተን ከአስር እጥፍ በላይ ለማግኘት ከወዲሁ እድሉን እንጠቀም።
#صحيح الجامع 
الألباني حسن - رقم: 1209

የጁምዓ እለት መኖሩም መሞቱም ለሙስሊሙ ፀጋ ነው።
,

📝 የአላህ መልእክተኛ ﷺ
ማንኛውም ሙስሊም የጁምዓ ቀን ወይም የጁምዓ ሌሊት የሞተ እንደሆን አላህ ከቀብር ፈተና ሳያድነው አይቀርም።» ብለዋል።
 ስለዚህ በመጀመርያ የዚህ እድል ተጠቃሚ ለመሆን

☞︎︎︎አርካኑል ኢስላምን በስርዓቱ የተገበረ ሙስሊም እንሁን።

በማስከተልም አላህ በራህመቱ ከቀብር ፈተና እንዲጠብቀንና ለዚህ ሰበብም እንዲያበቃን ሁሌም እንለምነው።

#حسنه الألباني في صحيح الترمذي - رقم: (1074) ، تخريج مشكاة المصابيح - رقم: (1316) الألباني :إسناده حسن أو صحيح لغيره

➪የጁምዓ እለት የሳምንቱ ከኃጢኣት መንፂያ ቀን ነው።


የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«ከባባድ ኃጢኣቶች ኖረው ካልጋረዱት በስተቀር አምስቱ ሰላቶች እንዲሁም ከጁምዓ እስከ ጁምዓ በመሃከላቸው ያለውን ኃጢኣት ያብሳሉ።»¹ በሌላ ዘገባም «ከባባድ ኃጢኣቶች ኖረው ካልጋረዱ በስተቀር ከጁምዓ እስከ ጁምዓ በመሃከላቸው ላለው ማበሻ ናቸው።»² ብለዋል።
,
 
ስለዚህ ከከባባድ ወንጀሎች በመራቅ ወይም ተውበት በማድረግ፣ አምስቱን እለታዊ ሰላቶች ጠብቆ በመስገድና የሳምንቱን ልዩ የስብስብ ቀን የጁምዓን ሰላት በመስገድ ተጨማሪ ግድፈቶቻችንን እንረም።

¹صحيح مسلم - رقم: (233)
²الألباني - صحيح الجامع رقم: (3110)

➪ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የመከባበርያ
ቀን ነው።

ሁሉም ሙስሊም ክቡር ነው። ሀብታም ከድሃ ታላቅ ከታናሽ፣ ገዢ ከተገዢ የሚለይበት ቦታ አየደለምና መስጂድ ሲደርስ ያገኘበት ክፍት ቦታ ሊቀመጥ ይገባዋል እንጂ ማንንም አስነስቶ ወይም እንዲነሳ አስደርጎ ሊቀመጥ አይገባውም። 


የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አንዳችሁ በጁምዓ ቀን ወንድሙ የተቀመጠበት ቦታ ሊቀመጥ ብሎ እንዳያስነሳው። ነገር ግን ሰፋ ሰፋ አድርጉ ይበል።» ብለዋልና ኢማሙ ኹጥባ ያልጀመሩ እንደሆነ ሰዎችን እንዲጠጋጉለትና እንዲሸጋሸጉለት በስርዓት ማግባትም ይችላል።
صحيح مسلم - رقم: (2178)

☞︎︎︎ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የፅዳት ቀን ነው።

የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አንዳችሁ ወደ ጁምዓ ሲሄድ ይታጠብ።» ማለታቸው ተዘግቧል።
صحيح البخاري - رقم: (882)


ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የቁርኣን ቀን ነው።

✉️ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ቀጣዩን
ብለዋል፣

☞︎︎︎በጁምዓ ቀን ሱረቱል ካህፍን ለቀራ ሰው በሁለቱ ጁምዓዎች መሃል ያለውን ያህል ከብርሃን ያበራለታል።»
حسنه الألباني في
تخريج مشكاة المصابيح - رقم:(2116)
•⊰✿📖✿⊱•

በሌላም ዘገባ እኛ በተለምዶ ሐሙስ ማታ በምንለው የጁምዓ አጥቢያ ምሽቱን ሱረቱል ካህፍን ለቀራ ሰው አጅሩ እጅግ በጣም ሰፊ ነው።
,
▪️ለይለቱል ጁምዓ ሱረቱል ካህፍን ላነበበ ሰው በሱ እና በበይተል ዐቲቅ (በካዕባ) መካከል ያለውን ያህል ከብርሃን ያበራለታል።» ብለዋል።
صححه الألباني في
صحيح الترغيب -رقم: (736)
 
اللهم صل وسلم على نبينا محمد وعلى آله وأصحابه أجمعين

•⊰✿📖✿⊱•