የወረቀት ብር ኖት ዘካ
~~~
በጥንትዘመን ሰዎች ግብይት የሚፈፅሙት እቃን በእቃ በመለዋወጥ ነበር። የልውውጥ ገበያ ለአጠቃቀም አስቸጋሪ በመሆኑ የተነሳ ቀስ በቀስ እየቀዘቀዘ ሄዶ አንዳንድ እቃዎችን (ለምሳሌ በሃገራችን አሞሌ ጨው) እንደመገበያያ ገንዘብ በመጠቃቀም ተተካ። ይሁን እንጂ እነዚህ እቃዎች ለአያያዝ አስቸጋሪ በመሆናቸው የተነሳ ሰዎች ወደ ሌሎች አማራጮች ማማተር ይጀምራሉ። በዚህም የተነሳ ነበር ወርቅና ብር ለመገበያያነት መዋል የጀመሩት። ወርቅና ብር ታዲያ በጊዜ ሂደት በአንጣሪዎች አማካኝነት ተመሳሳይ መጠንና ክብደት እንዲይዙ ተደርገው ለአስተማማኝነታቸው ማህተም ዲዛይን ተደርጎባቸው መዘጋጀት ያዙ። እነዚህን ገንዘቦች ለደህንነታቸው በመስጋት ገንዘብ መንዛሪዎችና አንጥረኞች ዘንድ በማስቀመጥ መተማመኛ ደረሰኞችን በምትካቸው ይቀበሉ ነበር። ሰዎች በነዚህ ድርጅቶች ላይ ያላቸው እምነት በጨመረ ቁጥር ደርሰኞቹ በግብይት ላይ ለክፍያ መዋል ያዙ።
የወረቀት ብር ኖት ታሪካዊ አነሳሱ በዚህ መልኩ ነበር። በጊዜው እነዚህ ከገንዘብ መንዛሪ ድርጅቶች የሚመጡ ወረቀቶች ሰውየው በነዚህ የግል ድርጅቶች ዘንድ ወርቅ/ ብር እንዳስቀመጠ በመግለፅ ወረቀቱን የተቀበለ ሰው ሄዶ ወርቁን/ ብሩን መውሰድ እንደሚችል ከመጠቆም ባለፈ ኦፊሴላዊ ይዘትም ሆነ የህግ ከለላ አልነበራቸውም። አገልግሎታቸው በሰፋ ቁጥር ግን በጊዜ ሂደት መንግስታት የህግ ሽፋን ሊሰጡ ግድ ብሏቸዋል። በዚህን ጊዜ የታወቀ ተመን በመስጠት ላምጪው እንዲከፈል አስገዳጅ ህግ ወጣ። የማተሙ/ የማሳተሙ ኃላፊነትም የመንግስታት ሆነ። ይህ ነገር የተጀመረው በ1833 እንደሆነ ድርሳናት ይጠቁማሉ። (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ነው።)
መንግስታት ካላቸው ተቀማጭ የወርቅ መጠን በላይ እነዚህን የወረቀት መገበያያዎች ገበያ ላይ ሲያቀርቡ ጊዜ ግን በነባሩ የወርቅ መገበያያ ላይ ፈተና ተደቀነ። በዚህን ጊዜ የወረቀት መገበያያዎችን ወደ ወርቅ ከመቀየር የሚከለክል ህግ መውጣት ያዘ። በዚህ ረገድ ቀዳሚዋ ብሪታኒያ ስትሆን ይህ የሆነውም በ1931 ነበር። አሜሪካ በ1934 ተከተለቻት። የክልከላው ተግባራዊነት ግን ድንበር ተሻጋሪ ሳይሆን በሃገራቱ ውስጥ የተገደበ ነበር። ሃገራት ከሃገራት ጋር ሲገበያዩ ግን የወረቀት ብሩን ወደ ወርቅ የመቀየር ውላቸውን ይጠብቁ ነበር። ከ1971 ጀምሮ ግን የወርቅ መጠን እያነሰ ስለመጣ አሜሪካ ይህንኛውን አሰራር ጭምር አቆመች። የመጨረሻው ወርቅን ለግብይት ተመን የመጠቀም አሰራር በዚህ መልኩ ተዘጋ።
የወረቀት ብር ኖት እነዚህን ታሪካዊ ለውጦች በማሳለፉ የተነሳ ምንነቱን በመግለፅ ላይ የኢስላም ምሁራን እይታቸው ሊለያይ ችሏል። የብዙሃን ዑለማዎችን አቋም ብቻ ሳሰፍር የወረቀት ብር ማለት እራሱን የቻለ የተለየ መገበያያ ገንዘብ ሲሆን ወርቅና ብርን (ሲልቨር) የሚመለከቱ ህጎች ይመለከቱታል። የየሃገራቱ የወረቀት ኖት እራሱን የቻለ አንዱ ከሌላው የሚለይ ገንዘብ ነው። ለማሳጠር ስል ለዚህ ትርጓሜ የሚውሉ አጋዥ መረጃዎችን አልጠቅስም።
እነዚህ የወረቀት ብር ኖት ሲጀመሩ አካባቢ ዘካ ይወጅብባቸዋል ወይስ አይወጅብባቸውም በሚለው ላይ በኢስላም ምሁራን መካከል ውዝግብ ተከስቶ ነበር። የልዩነቱ መነሻ ለዚህ ገንዘብ ምንነት የተሰጡ ትርጓሜዎች መለያየት ነበር። ነገር ግን ይሄ መገበያያ በከፍተኛ መጠን በመስፋፋቱና የወርቅና የብርን ቦታ በመተካቱ የተነሳ ውዝግቡ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ከስሟል። ስለዚህ ትኩረታችን ይህ የወረቀት ብር ኖት ለዘካ መጠን በሚደርስበት መነሻ ተመን (ኒሷብ) ላይ ይገደባል ማለት ነው።
የወረቀት ብር ኖት ዘካ የሚወጅብበት መነሻው ተመን (ኒሷብ) ስንት ነው? በዚህ ላይ ሶስት የተለያዩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።
አንደኛ:– የወረቀት መገበያያ ኖት መነሻ የዘካ ተመን የብር (ሲልቨር፣ ፊዷ) ኒሷብ ነው ያሉ አሉ። ይህም 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ነው።
ሁለተኛ:– ኒሷቡ የወርቅ ኒሷብ ማለትም 20 ዲናር ውይም 85 ግራም ነው ያሉም አሉ።
ሶስተኛ:– መነሻው መጠን ከወርቅና ከብር መነሻ ተመኖች ዝቅ ያለው ነው ያሉም አሉ።
ከሶስቱ ሃሳቦች ውስጥ ሶስተኛው ሚዛን የሚደፋ እንደሆነ በርካታ ዑለማዎች ደምድመዋል። መነሻቸውም:–
1ኛ፦ ድሃዎቹን የተሻለ ተጠቃሚ ያደርጋል።
2ኛ፦ ለዘካ አውጪውም ከውዝግብ ቀጠና ለመውጣት፣ ከተጠያቂነት ስጋት ለመትረፍ ይበልጥ ሰላማዊ ነው።
3ኛ፦ የመጀምሪያዎቹን ሁለት አቋሞች ያንፀባረቁ ምሁራን የሚያቀርቧቸውን መርጃዎችና ትንታኔዎች አንፃራዊ በሆነ መልኩ የተሻለ የሚያቀራርብ ነው።
4ኛ፦ ለዚህ የወረቀት መገበያያ ኖት የዘካ ተመን ከወርቅና ከብር (ሲልቨር) አንዱን መጠቀም ግድ ከሆነ ከሁለት አንዱ ቀድሞ የደረሰውን ኒሷብ በምን አሳማኝ መነሻ ልንዘለው እንችላለን? እንደሚታወቀው የብር (ሲልቨር) ኒሷብ ዛሬም በነብዩ ﷺ ዘመን ከነበረው አይቀየርም። ዛሬም እንደ ጥንቱ 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ብር ያለው ሰው ዘካ ማውጣት ግድ ይለዋል።
ይህ አቋም የሰዑዲያ የታላላቅ ዑለማእ ምክር ቤት፣ የእውቀታዊ ምርምር ቋሚ ኮሚቴ (ለጅነተ ዳኢማህ)፣ በራቢጦተል ዓለሚል ኢስላሚ ስር ያለው ቀራረል መጅመዒል ፊቅሂይ እና የሌሎችም ምርጫ ነው።
የዘንድሮ የወረቀት ብር ዘካ መነሻ (ሂሳብ) ስንት ነው?
````````
[ሀ] የወርቅ ዘካ ኒሷብ የሆነውን 20 ዲናር (85 ግራም) በወቅቱ ዋጋ 3,800 ብር ስናባዛው 323,000 ብር ሲሆን
[ለ] የብር ዘካ ኒሷብ ደግሞ 200 ዲርሃም (595 ግራም) በወቅቱ ዋጋ 120 ብር ሲባዛ 71,400 ብር ይሆናል። ስለዚህ ከሁለቱ ኒሷቦች የብሩ ስለሚያንስ ከላይ በቀረበው 3ኛው አቋም መሰረት ለዚህ አመት (1443 ሂጅሪያ) ይህንን መጠን 71,400 መነሻ እናደርጋለን ማለት ነው። እናም 71,400 ብር እና የበለጠ አመት የቆየ ብር ያለው ሰው ዘካ ማውጣት ግድ ይለዋል ማለት ነው። ስለሆነም ለዘካ መጠን የደረሰ ገንዘብ ኖሮት አመት ከቆየ የገንዘቡን የ1/10ኛውን እሩብ ማለትም 2.5% ዘካ ያወጣል ማለት ነው። ስሌቱን ግልፅ ለማድረግ ጥቂት ምሳሌዎችን ልስጥ፦
1– አመት የዞረ 300,000 ብር ያለው ሰው የ 300,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 300,000 x 0.025=7,500 ብር
2– አመት የዞረ 450,000 ብር ያለው ሰው የ 450,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 450,000 x 0.025=11,250 ብር
3– አመት የዞረ 5 ሚሊዮን ብር ያለው ሰው የ 5,000,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 5,000,000 x 0.025=125,000 ብር ይሆናል ማለት ነው። ወይም ደግሞ አጠቃላይ ገንዘቡን ለ40 ቢያካፍለው ማውጣት ያለበትን የዘካ መጠን ይሰጠዋል። የቀረቡትን ምሳሌዎች ለ40 ቢያካፈል ተመሳሳይ መጠን ያገኛል።
ማሳሰቢያ፦
~
በብሄራዊ ባንክ በኩል የሚወጣውን የወርቅና የብር ዋጋ ያልተጠቀምኩት ህዝብ የሚገባያይበት ትክክለኛ ዋጋ ነው ብየ ስላላመንኩበት ነው። ወሏሁ አዕለም።
(ረመዳን 15/1442፣ ሚያዚያ 20/ 2013)
https://t.me/IbnuMunewor
በጥንት
የወረቀት ብር ኖት ታሪካዊ አነሳሱ በዚህ መልኩ ነበር። በጊዜው እነዚህ ከገንዘብ መንዛሪ ድርጅቶች የሚመጡ ወረቀቶች ሰውየው በነዚህ የግል ድርጅቶች ዘንድ ወርቅ/ ብር እንዳስቀመጠ በመግለፅ ወረቀቱን የተቀበለ ሰው ሄዶ ወርቁን/ ብሩን መውሰድ እንደሚችል ከመጠቆም ባለፈ ኦፊሴላዊ ይዘትም ሆነ የህግ ከለላ አልነበራቸውም። አገልግሎታቸው በሰፋ ቁጥር ግን በጊዜ ሂደት መንግስታት የህግ ሽፋን ሊሰጡ ግድ ብሏቸዋል። በዚህን ጊዜ የታወቀ ተመን በመስጠት ላምጪው እንዲከፈል አስገዳጅ ህግ ወጣ። የማተሙ/ የማሳተሙ ኃላፊነትም የመንግስታት ሆነ። ይህ ነገር የተጀመረው በ1833 እንደሆነ ድርሳናት ይጠቁማሉ። (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ነው።)
መንግስታት ካላቸው ተቀማጭ የወርቅ መጠን በላይ እነዚህን የወረቀት መገበያያዎች ገበያ ላይ ሲያቀርቡ ጊዜ ግን በነባሩ የወርቅ መገበያያ ላይ ፈተና ተደቀነ። በዚህን ጊዜ የወረቀት መገበያያዎችን ወደ ወርቅ ከመቀየር የሚከለክል ህግ መውጣት ያዘ። በዚህ ረገድ ቀዳሚዋ ብሪታኒያ ስትሆን ይህ የሆነውም በ1931 ነበር። አሜሪካ በ1934 ተከተለቻት። የክልከላው ተግባራዊነት ግን ድንበር ተሻጋሪ ሳይሆን በሃገራቱ ውስጥ የተገደበ ነበር። ሃገራት ከሃገራት ጋር ሲገበያዩ ግን የወረቀት ብሩን ወደ ወርቅ የመቀየር ውላቸውን ይጠብቁ ነበር። ከ1971 ጀምሮ ግን የወርቅ መጠን እያነሰ ስለመጣ አሜሪካ ይህንኛውን አሰራር ጭምር አቆመች። የመጨረሻው ወርቅን ለግብይት ተመን የመጠቀም አሰራር በዚህ መልኩ ተዘጋ።
የወረቀት ብር ኖት እነዚህን ታሪካዊ ለውጦች በማሳለፉ የተነሳ ምንነቱን በመግለፅ ላይ የኢስላም ምሁራን እይታቸው ሊለያይ ችሏል። የብዙሃን ዑለማዎችን አቋም ብቻ ሳሰፍር የወረቀት ብር ማለት እራሱን የቻለ የተለየ መገበያያ ገንዘብ ሲሆን ወርቅና ብርን (ሲልቨር) የሚመለከቱ ህጎች ይመለከቱታል። የየሃገራቱ የወረቀት ኖት እራሱን የቻለ አንዱ ከሌላው የሚለይ ገንዘብ ነው። ለማሳጠር ስል ለዚህ ትርጓሜ የሚውሉ አጋዥ መረጃዎችን አልጠቅስም።
እነዚህ የወረቀት ብር ኖት ሲጀመሩ አካባቢ ዘካ ይወጅብባቸዋል ወይስ አይወጅብባቸውም በሚለው ላይ በኢስላም ምሁራን መካከል ውዝግብ ተከስቶ ነበር። የልዩነቱ መነሻ ለዚህ ገንዘብ ምንነት የተሰጡ ትርጓሜዎች መለያየት ነበር። ነገር ግን ይሄ መገበያያ በከፍተኛ መጠን በመስፋፋቱና የወርቅና የብርን ቦታ በመተካቱ የተነሳ ውዝግቡ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ከስሟል። ስለዚህ ትኩረታችን ይህ የወረቀት ብር ኖት ለዘካ መጠን በሚደርስበት መነሻ ተመን (ኒሷብ) ላይ ይገደባል ማለት ነው።
የወረቀት ብር ኖት ዘካ የሚወጅብበት መነሻው ተመን (ኒሷብ) ስንት ነው? በዚህ ላይ ሶስት የተለያዩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።
አንደኛ:– የወረቀት መገበያያ ኖት መነሻ የዘካ ተመን የብር (ሲልቨር፣ ፊዷ) ኒሷብ ነው ያሉ አሉ። ይህም 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ነው።
ሁለተኛ:– ኒሷቡ የወርቅ ኒሷብ ማለትም 20 ዲናር ውይም 85 ግራም ነው ያሉም አሉ።
ሶስተኛ:– መነሻው መጠን ከወርቅና ከብር መነሻ ተመኖች ዝቅ ያለው ነው ያሉም አሉ።
ከሶስቱ ሃሳቦች ውስጥ ሶስተኛው ሚዛን የሚደፋ እንደሆነ በርካታ ዑለማዎች ደምድመዋል። መነሻቸውም:–
1ኛ፦ ድሃዎቹን የተሻለ ተጠቃሚ ያደርጋል።
2ኛ፦ ለዘካ አውጪውም ከውዝግብ ቀጠና ለመውጣት፣ ከተጠያቂነት ስጋት ለመትረፍ ይበልጥ ሰላማዊ ነው።
3ኛ፦ የመጀምሪያዎቹን ሁለት አቋሞች ያንፀባረቁ ምሁራን የሚያቀርቧቸውን መርጃዎችና ትንታኔዎች አንፃራዊ በሆነ መልኩ የተሻለ የሚያቀራርብ ነው።
4ኛ፦ ለዚህ የወረቀት መገበያያ ኖት የዘካ ተመን ከወርቅና ከብር (ሲልቨር) አንዱን መጠቀም ግድ ከሆነ ከሁለት አንዱ ቀድሞ የደረሰውን ኒሷብ በምን አሳማኝ መነሻ ልንዘለው እንችላለን? እንደሚታወቀው የብር (ሲልቨር) ኒሷብ ዛሬም በነብዩ ﷺ ዘመን ከነበረው አይቀየርም። ዛሬም እንደ ጥንቱ 200 ዲርሃም ማለትም 595 ግራም ብር ያለው ሰው ዘካ ማውጣት ግድ ይለዋል።
ይህ አቋም የሰዑዲያ የታላላቅ ዑለማእ ምክር ቤት፣ የእውቀታዊ ምርምር ቋሚ ኮሚቴ (ለጅነተ ዳኢማህ)፣ በራቢጦተል ዓለሚል ኢስላሚ ስር ያለው ቀራረል መጅመዒል ፊቅሂይ እና የሌሎችም ምርጫ ነው።
የዘንድሮ የወረቀት ብር ዘካ መነሻ (ሂሳብ) ስንት ነው?
````````
`````````ወቅታዊን የወርቅና የብር ዋጋ አጣርቶ በራሱ ማስላት ይችላል። በኔ በኩል በተወሰኑ ወንድሞች አማካኝነት ለማጣራት እንደሞከርኩት ወቅታዊ (የ 2014) ወርቅ የሚሸጥበት ዋጋ በግራም ከ 3800 እስከ 4,500 ብር ነው። የብር መሸጫ ዋጋ ደግሞ ከ 120 እስከ 150 ብር ነው። ስለዚህ፡
የሚችል ሰው
[ሀ] የወርቅ ዘካ ኒሷብ የሆነውን 20 ዲናር (85 ግራም) በወቅቱ ዋጋ 3,800 ብር ስናባዛው 323,000 ብር ሲሆን
[ለ] የብር ዘካ ኒሷብ ደግሞ 200 ዲርሃም (595 ግራም) በወቅቱ ዋጋ 120 ብር ሲባዛ 71,400 ብር ይሆናል። ስለዚህ ከሁለቱ ኒሷቦች የብሩ ስለሚያንስ ከላይ በቀረበው 3ኛው አቋም መሰረት ለዚህ አመት (1443 ሂጅሪያ) ይህንን መጠን 71,400 መነሻ እናደርጋለን ማለት ነው። እናም 71,400 ብር እና የበለጠ አመት የቆየ ብር ያለው ሰው ዘካ ማውጣት ግድ ይለዋል ማለት ነው። ስለሆነም ለዘካ መጠን የደረሰ ገንዘብ ኖሮት አመት ከቆየ የገንዘቡን የ1/10ኛውን እሩብ ማለትም 2.5% ዘካ ያወጣል ማለት ነው። ስሌቱን ግልፅ ለማድረግ ጥቂት ምሳሌዎችን ልስጥ፦
1– አመት የዞረ 300,000 ብር ያለው ሰው የ 300,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 300,000 x 0.025=7,500 ብር
2– አመት የዞረ 450,000 ብር ያለው ሰው የ 450,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 450,000 x 0.025=11,250 ብር
3– አመት የዞረ 5 ሚሊዮን ብር ያለው ሰው የ 5,000,000ን 2.5% ያወጣል፡፡ 5,000,000 x 0.025=125,000 ብር ይሆናል ማለት ነው። ወይም ደግሞ አጠቃላይ ገንዘቡን ለ40 ቢያካፍለው ማውጣት ያለበትን የዘካ መጠን ይሰጠዋል። የቀረቡትን ምሳሌዎች ለ40 ቢያካፈል ተመሳሳይ መጠን ያገኛል።
ማሳሰቢያ፦
~
በብሄራዊ ባንክ በኩል የሚወጣውን የወርቅና የብር ዋጋ ያልተጠቀምኩት ህዝብ የሚገባያይበት ትክክለኛ ዋጋ ነው ብየ ስላላመንኩበት ነው። ወሏሁ አዕለም።
(ረመዳን 15/1442፣ ሚያዚያ 20/ 2013)
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Deleted Account
ለራሳችሁ መልካም እንደምትመኙ ሁሉ ለሌሎችም የምትመኙ ሁሉ፣ አላህ ዱንያ አኺራችሁን ያሳምርላችሁ።
Forwarded from Deleted Account
ረመዷን
(3)
አምና በማዕዳችሁ ላይ ከነበረ ሰው መካከል በሆነ ምክንያት የጎደለ ይኖር ይሆን?
አስታውሱና ዱዓ አድርጉለት።
(3)
አምና በማዕዳችሁ ላይ ከነበረ ሰው መካከል በሆነ ምክንያት የጎደለ ይኖር ይሆን?
አስታውሱና ዱዓ አድርጉለት።
Forwarded from Deleted Account
ረመዷን (3)
አሥራ አንድ ወራት ያበላሸነዉን አንድ ወርሀ ረመዷን ያስተካክልናል። ረመዷን የለውጥ ወር ነው፣ የተዘበራረቀ ሕይወታችንን መስመር ያስይዝልናል። ከአላህ የተሰጠን ችሮታ ነውና ዕድሉን በአግባቡ እንጠቀምበት።
አሥራ አንድ ወራት ያበላሸነዉን አንድ ወርሀ ረመዷን ያስተካክልናል። ረመዷን የለውጥ ወር ነው፣ የተዘበራረቀ ሕይወታችንን መስመር ያስይዝልናል። ከአላህ የተሰጠን ችሮታ ነውና ዕድሉን በአግባቡ እንጠቀምበት።
Forwarded from Deleted Account
የደከሙ አካላት፣ የዛሉ ሰዉነቶች፣ የደረቁ ከንፈሮች፣ የተራቡ አንጀቶች፣ የተጠሙ ጅማቶች፣ … በተለይ ከዐስር በኋላ እዚህም እዚያም ተዝለፍልፈው ይታያሉ፡፡ በተስፋ እና በትዕግስት የፀሐይን መጥለቅ ይጠባበቃሉ፡፡ ጌታዬ አንተኑ ፍራቻ ነዉና ባሮችህን ተቀበላቸው፣ እዘንላቸው፣ ማራቸው ጀነትህንም አስገባቸው፡፡
Forwarded from Deleted Account
ረመዷን
(4)
*
“ወደ ዙሁር ሶላት ስትሄድ የሚወጣህ ላብ በተራዊሕ ሶላት ላይ ከሚፈስህ እንባ ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም ዙሁር ግዴታ ሲሆን ተራዊሕ ግን ሱንና ነው፡፡ ዙሁርን እና ዐስር ሳይሰግዱ ለመግሪብ መንቃት፤ ተኝተው ዉለው ለተራዊሕ እና ለተሀጁድ ሶላት መውደቅ መነሳት ትልቅ መጃጃል ነው፡፡ አንዲት የግዴታ ሶላት መፈፀም ሙሉዉን ረመዷን ከመቆም ይበልጣል፡፡” ይላሉ ሸይኽ ሙሐመድ ሙኽታር አሽ-ሸንቂጢ።
(4)
*
“ወደ ዙሁር ሶላት ስትሄድ የሚወጣህ ላብ በተራዊሕ ሶላት ላይ ከሚፈስህ እንባ ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም ዙሁር ግዴታ ሲሆን ተራዊሕ ግን ሱንና ነው፡፡ ዙሁርን እና ዐስር ሳይሰግዱ ለመግሪብ መንቃት፤ ተኝተው ዉለው ለተራዊሕ እና ለተሀጁድ ሶላት መውደቅ መነሳት ትልቅ መጃጃል ነው፡፡ አንዲት የግዴታ ሶላት መፈፀም ሙሉዉን ረመዷን ከመቆም ይበልጣል፡፡” ይላሉ ሸይኽ ሙሐመድ ሙኽታር አሽ-ሸንቂጢ።
Forwarded from Deleted Account
ይህ ወር ልብን ሕያው በማድረግ ወደ አላህ የሚደረገውን ጉዞ ምቹ ለማድረግ ወርቃማ አጋጣሚ ነው። የተለያዩ አምልኮዎች በወሩ ላይ ይሰባሰባሉ። ከነዚህ መካከል ጾም፣ ሶላት፣ ቁርኣንን ማንበብ፣ ሰደቃ (ምጽዋት)፣ ኢዕቲካፍ (መስጂድ ውስጥ መቀመጥ)፣ ዚክር (አላህን ማስታወስ)፣ ዑምራ ይጠቀሳሉ።
ረመዳን በርካታ አምልኮዎች የሚሰባሰቡበት ወር ነው። እነዚህን አምልኮዎች በትክክል ለማከናወን በሞከርን ቁጥር ልቦና ሕያው የመሆን ተጽእኖው ግዙፍ ነው። ወደ አላህ የሚደረገውን ጉዞ በብርሃን ፍጥነት ለማመንጠቅ ይረዳል። በቅርጻቸው ብቻ ለማከናወን የሞከርን ጊዜ ግን ባሕሪው ብቻ እኛ ላይ ይቀራል። አምልኮዎቹ ቅርጻቸው ብቻ እኛ ላይ ቀሪ ሆነው የሚፈለገው ውስጣዊ ለውጥ ሊመጣ አይችልም። በመሆኑም ከረመዳን በኋላ ስንፍናውና ደካማነቱ ይቀጥላል።
ጥቂት የረመዷን ቀናት
ረመዳን በርካታ አምልኮዎች የሚሰባሰቡበት ወር ነው። እነዚህን አምልኮዎች በትክክል ለማከናወን በሞከርን ቁጥር ልቦና ሕያው የመሆን ተጽእኖው ግዙፍ ነው። ወደ አላህ የሚደረገውን ጉዞ በብርሃን ፍጥነት ለማመንጠቅ ይረዳል። በቅርጻቸው ብቻ ለማከናወን የሞከርን ጊዜ ግን ባሕሪው ብቻ እኛ ላይ ይቀራል። አምልኮዎቹ ቅርጻቸው ብቻ እኛ ላይ ቀሪ ሆነው የሚፈለገው ውስጣዊ ለውጥ ሊመጣ አይችልም። በመሆኑም ከረመዳን በኋላ ስንፍናውና ደካማነቱ ይቀጥላል።
ጥቂት የረመዷን ቀናት
قال الإمام علي بن أبي طالب رضي الله عنه : " ما لابن آدم والفخر أوله نطفة وآخره جيفة ، لا يرزق نفسه ولا يدفع حتفه "
ኢማሙ ዓልይ ብን አቢ ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ አሉ፦【የአደም ልጅ ጅማሪው መንይ(የዘር ፈሳሽ) መጨረሻው ሬሳ ሆኖ ለምኑ ነው ሚኮራው እራሱን መቀለብ የማይችል ከራሱም ሞትን ማራቅ የማይችል ነው】
ኢማሙ ዓልይ ብን አቢ ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ አሉ፦【የአደም ልጅ ጅማሪው መንይ(የዘር ፈሳሽ) መጨረሻው ሬሳ ሆኖ ለምኑ ነው ሚኮራው እራሱን መቀለብ የማይችል ከራሱም ሞትን ማራቅ የማይችል ነው】
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት "ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ?" በሚል
የታሰሩ ተማሪዎችን "ይፈቱልን "ብለው በጠየቁ ወላጆች ላይ የተኩስ ሩምታ
መከፈቱን እና ወላጆችም ላይ ድብደባ መድረሱ ታወቀ
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ተብለው ያለ
አግባብ የታሰሩባቸውን ልጆቻቸውን ፍቱልን ብለው የሄዱ ወላጆች ላይ ከፖሊስ
የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸዋል። በርካታ ወላጆች ተደብድበው መታሰራቸው
ታውቋል
ተማሪዎቹ ከግቢያቸው ውጭም ሆነ በትምህርት ቤት ግቢ እንዳይሰግዱ
ተደርገዋል::
https://t.me/islam_in_school
የታሰሩ ተማሪዎችን "ይፈቱልን "ብለው በጠየቁ ወላጆች ላይ የተኩስ ሩምታ
መከፈቱን እና ወላጆችም ላይ ድብደባ መድረሱ ታወቀ
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ተብለው ያለ
አግባብ የታሰሩባቸውን ልጆቻቸውን ፍቱልን ብለው የሄዱ ወላጆች ላይ ከፖሊስ
የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸዋል። በርካታ ወላጆች ተደብድበው መታሰራቸው
ታውቋል
ተማሪዎቹ ከግቢያቸው ውጭም ሆነ በትምህርት ቤት ግቢ እንዳይሰግዱ
ተደርገዋል::
https://t.me/islam_in_school
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት "ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ?" በሚል
የታሰሩ ተማሪዎችን "ይፈቱልን "ብለው በጠየቁ ወላጆች ላይ የተኩስ ሩምታ
መከፈቱን እና ወላጆችም ላይ ድብደባ መድረሱ ታወቀ
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ተብለው ያለ
አግባብ የታሰሩባቸውን ልጆቻቸውን ፍቱልን ብለው የሄዱ ወላጆች ላይ ከፖሊስ
የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸዋል። በርካታ ወላጆች ተደብድበው መታሰራቸው
ታውቋል
ተማሪዎቹ ከግቢያቸው ውጭም ሆነ በትምህርት ቤት ግቢ እንዳይሰግዱ
ተደርገዋል::
https://t.me/islam_in_school
https://t.me/islam_in_school
የታሰሩ ተማሪዎችን "ይፈቱልን "ብለው በጠየቁ ወላጆች ላይ የተኩስ ሩምታ
መከፈቱን እና ወላጆችም ላይ ድብደባ መድረሱ ታወቀ
በለሚ ኩራ እድገት ጮራ ትምህርት ቤት ሶላት ለምን ሰገዳችሁ ተብለው ያለ
አግባብ የታሰሩባቸውን ልጆቻቸውን ፍቱልን ብለው የሄዱ ወላጆች ላይ ከፖሊስ
የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸዋል። በርካታ ወላጆች ተደብድበው መታሰራቸው
ታውቋል
ተማሪዎቹ ከግቢያቸው ውጭም ሆነ በትምህርት ቤት ግቢ እንዳይሰግዱ
ተደርገዋል::
https://t.me/islam_in_school
https://t.me/islam_in_school
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መስገድ የሚያሳስርበት ጊዜ ላይ ደርሰናል ህፃናትን ለምን ሰገድክ ብሎ ማሰር
በታዳጊው ስነልቦና ላይ ሊፈጥር የሚችለው ጫና ከባድ ነው
-እድገት ጮራ ትምህርት ቤት
-ትምህርት ቢሮ
-ለሚኩራ ክፍለከተማ
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድ ያዳርሱ ‼
https://t.me/islam_in_school
https://t.me/islam_in_school
በታዳጊው ስነልቦና ላይ ሊፈጥር የሚችለው ጫና ከባድ ነው
-እድገት ጮራ ትምህርት ቤት
-ትምህርት ቢሮ
-ለሚኩራ ክፍለከተማ
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድ ያዳርሱ ‼
https://t.me/islam_in_school
https://t.me/islam_in_school
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
(3)ከረመዷን ጋር ተያያዥ የሆኑ ፈታዋ በዛዱል መዓድ በኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም@ዛዱል መዓድ
Forwarded from Deleted Account
أَفَحَسِبْتُمْ أَنَّمَا خَلَقْنَاكُمْ عَبَثًا وَأَنَّكُمْ إِلَيْنَا لَا تُرْجَعُونَ
[ ሱረቱ አል-ሙእሚኑን - 115 ]
«የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» (ለከንቱ የፈጠርናችሁ መሰላችሁን)
[ ሱረቱ አል-ሙእሚኑን - 115 ]
«የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» (ለከንቱ የፈጠርናችሁ መሰላችሁን)
Forwarded from Deleted Account
#ታጥቦ ጭቃ አንሁን*
*أعمال تفسد ثواب الصوم*
አንድ ፆመኛ ሰው በመፆሙ ምክንያት ወንጀሉ ይሰረዝለታል ዳሩ ግን ከእነዚህ ወንጀሎች ካልተጠነቀቀ ታጥቦ ጭቃ ነው ሚሆነው :—
— መዋሸት በቃላትም ሆነ በተግባር
— ክህደት በቃልም ሆነ በተግባር
— ቀጠሮን አለማክበር
— ሀሜት ሰው ሲታማ ጆሮ ሰጥቶ ማድመጥ
— ነገር ማዋሰድ (ሰዎችን ማጣላት)
— ማታለል ፣ማጭበርበር
— ሙዚቃ ማድመጥ ፣ መልእክቱ ምንም ያህል ሸጋ ቢሆንም በሙዚቃ መሣሪያ ከታጀበ የሸይጣን ድምጽ ነው ተጠንቀቀው
— የተቃራኒ ፆታን ስሜት የሚቀሰቅሱ ነገራትን መተግበር
— በሰው ማፌዝ፣ ማላገጥ፣ መጠቃቀስ
— መሳደብ ፣ ማንጓጠጥ
— መራገም ፣ ሰውንም ሆነ እንስሳን ወይም ንብረትን ከመራገም ተቆጠብ
— ከሰው ጋር መጋጨት ፣ መጣላት
— የሰውን ክብርና ንብረት መንካት
*በሆዳችን ብቻ ሳይሆን በመላው አካላችን የምንጾም አላህ ያድርገን !
*أعمال تفسد ثواب الصوم*
አንድ ፆመኛ ሰው በመፆሙ ምክንያት ወንጀሉ ይሰረዝለታል ዳሩ ግን ከእነዚህ ወንጀሎች ካልተጠነቀቀ ታጥቦ ጭቃ ነው ሚሆነው :—
— መዋሸት በቃላትም ሆነ በተግባር
— ክህደት በቃልም ሆነ በተግባር
— ቀጠሮን አለማክበር
— ሀሜት ሰው ሲታማ ጆሮ ሰጥቶ ማድመጥ
— ነገር ማዋሰድ (ሰዎችን ማጣላት)
— ማታለል ፣ማጭበርበር
— ሙዚቃ ማድመጥ ፣ መልእክቱ ምንም ያህል ሸጋ ቢሆንም በሙዚቃ መሣሪያ ከታጀበ የሸይጣን ድምጽ ነው ተጠንቀቀው
— የተቃራኒ ፆታን ስሜት የሚቀሰቅሱ ነገራትን መተግበር
— በሰው ማፌዝ፣ ማላገጥ፣ መጠቃቀስ
— መሳደብ ፣ ማንጓጠጥ
— መራገም ፣ ሰውንም ሆነ እንስሳን ወይም ንብረትን ከመራገም ተቆጠብ
— ከሰው ጋር መጋጨት ፣ መጣላት
— የሰውን ክብርና ንብረት መንካት
*በሆዳችን ብቻ ሳይሆን በመላው አካላችን የምንጾም አላህ ያድርገን !
Forwarded from Deleted Account
🛑 ተራዊህ በመስገድ ከሚገኙ ጥቅሞች
📌 ቀኑን በጾም ሌሊቱን በሰላት በማሳለፋችን ከደጋግ የአላህ ባሪያዎች እንመደባለን
📌 ቁርኣን በብዛት በማድመጣችን የአላህን እዝነት እናገኛለን
📌 ተራዊሕ ብዙ ሩኩዕና ሱጁድ ስላለበት ሰፊ የዱዓና የዚክር እድል እናገኛለን
📌 ከወንጀል ርቀን ጊዜያችንን በመልካም ስራ እናሳልፋለን
📌 ዒባዳ ላይ ትዕግስትን እንማራለን
📌 ሰላተል-ለይል እንለማመዳለን
📌 በተደጋጋሚ ከኢማሙና ማእሙሞች ጋር "አሚን" በማለታችን ወንጀላችን ይማራል
📌 መስጂድ ስንሄድና ስንመለስ በእርምጃችን ልክ ወንጀሎች ተራግፈው መልካም ስራዎች ይጻፉልናል
📌 ሰላት እየጠበቀን በምናሳልፋቸው ጊዜያቶች መላኢካዎች ምህረት ይጠይቁልናል
📌 የሙስሊሞችን ጀማዓ በማብዛት ሸይጣንና አጋዦችን እናስቆጫለን
📌 ከመልካም ሰዎች ጋር በመቀላቀላችን መልካም ስራዎቻችን ወደ ሰማይ እንዲወጡና ተቀባይነት እንዲያገኙ እድል ይፈጥራል
📌 ከአልባሌ ነገሮች ለመራቅ ለወጣቱ መልካም አርዓያ እንሆናለን
📌 ካመኑበትና ጥቅሙን ካወቁት ሁሉም ነገር ቀላልና የሚቻል መሆኑን በተጨባጭ እናይበታለን
📌 ቁርኣንን በብዛት በመስማት የአላህን እዝነት እናገኛለን እንዲሁም ብዙ በመስማት ትክክለኛውን የቁርኣን አቀራርም እንማራለን
📌 በቁኑት ዱዓ ወቅት ብዙ እኛ ያላሰብናቸውና መግለጽ የማንችላቸው ነገሮች ዱዓ ተደርጎ "አሚን" በማለታችን ትርፋማ እንሆናለን
📌 ከኢማሙ ጋር እስከሰላቱ ፍጻሜ ድረስ አብረን እየሰገድን ከቆየን ሌሊቱን በሙሉ ሲሰግድ ያደረን ሰው እጅር /ምንዳ እንሸምታለን
📌 የቂያማ ቀን መቆምን ያቀልልናል፥ዱኒያ ላይ ለጌታው ብሎ ረጅም ሰዓት የቆመ የቂያማ ቀን መቆም አይከብደውም
📌 ሰግደን ስንመለስ የውስጥ ደስታና እፎይታና ሌሎችንም የዲንም የዱኒያ በርካታ ጥቅሞችን እናገኛልንና ተራዊህን ሳንሰለች እንስገድ።
አላህ ያግራልን
📌 ቀኑን በጾም ሌሊቱን በሰላት በማሳለፋችን ከደጋግ የአላህ ባሪያዎች እንመደባለን
📌 ቁርኣን በብዛት በማድመጣችን የአላህን እዝነት እናገኛለን
📌 ተራዊሕ ብዙ ሩኩዕና ሱጁድ ስላለበት ሰፊ የዱዓና የዚክር እድል እናገኛለን
📌 ከወንጀል ርቀን ጊዜያችንን በመልካም ስራ እናሳልፋለን
📌 ዒባዳ ላይ ትዕግስትን እንማራለን
📌 ሰላተል-ለይል እንለማመዳለን
📌 በተደጋጋሚ ከኢማሙና ማእሙሞች ጋር "አሚን" በማለታችን ወንጀላችን ይማራል
📌 መስጂድ ስንሄድና ስንመለስ በእርምጃችን ልክ ወንጀሎች ተራግፈው መልካም ስራዎች ይጻፉልናል
📌 ሰላት እየጠበቀን በምናሳልፋቸው ጊዜያቶች መላኢካዎች ምህረት ይጠይቁልናል
📌 የሙስሊሞችን ጀማዓ በማብዛት ሸይጣንና አጋዦችን እናስቆጫለን
📌 ከመልካም ሰዎች ጋር በመቀላቀላችን መልካም ስራዎቻችን ወደ ሰማይ እንዲወጡና ተቀባይነት እንዲያገኙ እድል ይፈጥራል
📌 ከአልባሌ ነገሮች ለመራቅ ለወጣቱ መልካም አርዓያ እንሆናለን
📌 ካመኑበትና ጥቅሙን ካወቁት ሁሉም ነገር ቀላልና የሚቻል መሆኑን በተጨባጭ እናይበታለን
📌 ቁርኣንን በብዛት በመስማት የአላህን እዝነት እናገኛለን እንዲሁም ብዙ በመስማት ትክክለኛውን የቁርኣን አቀራርም እንማራለን
📌 በቁኑት ዱዓ ወቅት ብዙ እኛ ያላሰብናቸውና መግለጽ የማንችላቸው ነገሮች ዱዓ ተደርጎ "አሚን" በማለታችን ትርፋማ እንሆናለን
📌 ከኢማሙ ጋር እስከሰላቱ ፍጻሜ ድረስ አብረን እየሰገድን ከቆየን ሌሊቱን በሙሉ ሲሰግድ ያደረን ሰው እጅር /ምንዳ እንሸምታለን
📌 የቂያማ ቀን መቆምን ያቀልልናል፥ዱኒያ ላይ ለጌታው ብሎ ረጅም ሰዓት የቆመ የቂያማ ቀን መቆም አይከብደውም
📌 ሰግደን ስንመለስ የውስጥ ደስታና እፎይታና ሌሎችንም የዲንም የዱኒያ በርካታ ጥቅሞችን እናገኛልንና ተራዊህን ሳንሰለች እንስገድ።
አላህ ያግራልን
#ሱብሀነክ
#ጥበቃህ_አልተለየኝም__!!
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
መጥፎነቴ ገዝፎብኝ፤
በሰወች የሀሳብ ሚዛን፡
ክፋቴ ከመጠን አልፎ፤
ተሰምቶ በአለም እንደ አዛን፡
ሁሉም በአይን ጫፍ አይቶኝ፤
በመኖሬ አጥቼ ለዛን፡
መላ ቅጡ ጠፍቶብኝ፤
የመፈጠር ጣዕሙ፡
ድንግርግር ምርር ብሎኝ፤
ጠፍቶኝ የመኖር ትርጉሙ፡
ችግር መከራ ወሮኝ፤
ጉስቁልናውም ህመሙ፡
የሀሳብ ረጂም መንገድ፤
ውጣ ውረዱ ድካሙ፡
ምን እንደሆነ ሳላውቀው፤
ማጣፈጫ ቅመሙ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
እጂግ ብዙ ዳከርኩኝ በጣም በብዙ አመፅኩኝ፡
በስሜት ባለማወቅ ብዙ ወንጀልን ፈፀምኩኝ፡
የመፈጠሬን አላማ እኔ ብዘነጋውም፡
የአምላክነትህን እዝነት በፍፁም አላጣሁም፡
በሽተኛ ነው ብሎ የሰው ዘር ቢፀየፈኝም፡
መጥፎ መገለጫወችን ቀምሞ ቢጭንብኝም፡
ያለስሜ ስም ሰጥቶ በግፍ ቢያንቋሽሸኝም፡
በሌለሁበት ዋሽቶ እጂግ ብዙ ቢለኝም፡
እኔ እየወነጀልኩህ፤
አንተ መች አዋረድከኝ፡
ሰወች ጠላት ሲሆኑኝ፤
አምላኬ አንተ መች ተውከኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
በተደጋጋሚ ደፍሬህ፤
ከእዝነትህ መች አራቅከኝ፡
አምፀኸኛልና እኔ አላውቅህም መች አልከኝ፡
ተመለስ እና ወደኔ፤
ተውበት አድርግ እንጂ ያልከኝ፡
የበደልኩህን ቆጥረህ፤
እስረኛ መች አደረከኝ፡
መመሪያህን እየጣስኩ
እያመፅኩህ መች ተውከኝ፡
ባሪያዬ ብለህ በመጥራት
ይበልጥ ነው ያቀረብከኝ፡
እኔን ፍራ ብለህ ገስፀህ፤
ብዙ ፀጋ ነው ያደልከኝ፡
እመነኝ ጀነት አለህ፤
ብለህ ነው የነገርከኝ፡
ጥራት ይገባህ ላንተ፤
እኔን ስላከበርከኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
የቀረቡኝ ሲርቁ ያበላኋቸው ሲበሉኝ፡
ትላንት የረዳኋቸው ዛሬ ላይ ሲያታልሉኝ፡
መልካም ያደረኩላቸው በሌለ ስንት ሲሉኝ፡
ወዳጆች የነበሩ ሁሉ ተከርብተው ሲጠሉኝ፡
ከገደል ያወጣኋቸው፤
ወደ ገደል ሲገፉኝ፡
በእዝነት የዳበስኳቸው፤
እሾህ ጨብጠው ሲያቅፉኝ፡
አብሮ አደግ ጓደኞቼ፤
ኮርተው በንቀት ሲያልፉኝ፡
ሚስጥሬን የነገርኳቸው፤
እቀደዱ ሲሰፉኝ፡
ያመንኳቸው ሁሉ ጓደኞች፤
በቅፅበት ውሳኔ ሲያኮርፉኝ፡
እየተከረባበቱ በወጥመድ ሲማጎ ሲጠልፉኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
ወንድምም ሆነ ዘመድ ሞኝ ነህ ብሎ ቢለኝም፡
ጠላት በሩቅ እየሳቀ በበደል ቢወርፈኝም፡
ከፈጠርከኝ ጀምሮ፤
ባሳለፍኳቸው አመታት፡
ጥበቃህ አልተለየኝም፤
ለሰከንድ እንኳን ሰአታት፡
አንተን ማመኔ ብቻ፤
ለኔ ሆኖኛል ብርታት፡
የእውነትም አምላክ ነህና፤
የሚሆኑልህ ሰማዕታት፡
አንድ ብቸኛ ጌታ የአለማት ሁሉ ፈጣሪ፡
የፈለገውን አድራጊ የፈለገውን ሰሪ፡
የፈለገውን ቀጥቶ የፈለገውን መሀሪ፡
ሁሉንም ነገር አጥፍቶ ከኋላ ብቻውን ቀሪ፡
ሞተ የማይባል ጌታ የዘላለም ዘውታሪ፡
ድካም እንቅልፍ የማያውቅ ህያውና ታታሪ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
የሰውነት ቅርፅ የሰጠኸኝን፤
የተዋበ አድርጎ መልኬን፡
ሙሉ አካልን ለግሶኝ፤
አንድም ሳይቀንስ ልኬን፡
በብርሀን የቀየረልኝን፤
ያንን ጨለማ ታሪኬን፡
ከአርሹ በላይ ያለውን፤
መገዛት አልተውም አምላኬን፡
ያለማንነቴ እየዘለፈ ማንም ምንም ቢያወራ፡
ብቻየን እንኳን ብቀር በምድረ-በዳ ጠራራ፡
ቃል እገባለሁ ወላሒ እኔ አንተን ብቻ ልጣራ፡
አንድነትህን እያዜምኩ በማንም ላላጋራ፡
ፈፅሞ እኔ ላልተወው የፈጠርክብኝን አላማ፡
ማንም ቢለፈልፍብኝ ማንም ድምፅ ቢያሰማ፡
ከናፍሮቼ ቢዘጉ እጀ ቢታሰር በካስማ፡
ቃል ገብቻለሁ በአንተ ፊት፤
ካንተ ውጭ ሌላ ላልሰማ፡
በመጨረሻው ነብይ፤
በሙሀመድ አበል ፋጢማ፡
በዚያ በጣፋጭ ቅመም፤
በላከው ለአለም ረህማ፡
በመካው የቀትር ፀሀይ፤
በመድና ላይ ጨረቃ፡
መልካምነቱ በአላም፤
ተጉዞ በማያበቃ፡
በተነገረ ቁጥር፤
ፍቅሩ የሚያሲዝ ሲቃ፡
በርሱ መንገድ ከመጓዝ፤
በፅሞ እኔ አልቦዝንም፡
አንተን አንድ አምላክ አምኘ፤
በፍፁም እኔማ አላዝንም፡
ስህተቴን እያስተካከልኩ፤
እስክሞት አመልክሀለሁ፡
አንተን በማምለኬ ላይ፤
ፅናትን እማፀናለሁ፡
አምላኬ በመሆንህ፤
ከልቤ ደስተኛ ነኝ፡
ግና በወንጀል ተለውሻለሁ
በዕዝነትህ ከዕሳት አድነኝ፡
የጀነት ነህ ብለህ አስደሳኝ፤
በስራዬ ሳይሆን በዕዝነትህ፡
ከዱንያ መከራም አውጣኝ፤
ጠብቀኝ በበረከትህ፡
እወድሀለሁ አምላኬ
የምገልፅበት ቃል የለኝም፡
በባርነቴ አምኛለሁ፤
ለማንም ግድ አይሰጠኝም፡
የሰወች ወቀሳ ትችን፤
ምንም አይሰማኝም፡
አንተን ባላወቅኩበት ዘመን፤
ብዙ ጥፋቶችን ብመኝም፡
በመሀይምነት ታውሬ፤
ግዙፍ ስህተት ብቀኝም፡
ወንጀለኛ ሆኘ እንኳን፤
ጥበቃህ አልተለየኝም፡
#አምላኬ______እወድሀለሁ።
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
✍️በኑረዲን
#ጥበቃህ_አልተለየኝም__!!
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
መጥፎነቴ ገዝፎብኝ፤
በሰወች የሀሳብ ሚዛን፡
ክፋቴ ከመጠን አልፎ፤
ተሰምቶ በአለም እንደ አዛን፡
ሁሉም በአይን ጫፍ አይቶኝ፤
በመኖሬ አጥቼ ለዛን፡
መላ ቅጡ ጠፍቶብኝ፤
የመፈጠር ጣዕሙ፡
ድንግርግር ምርር ብሎኝ፤
ጠፍቶኝ የመኖር ትርጉሙ፡
ችግር መከራ ወሮኝ፤
ጉስቁልናውም ህመሙ፡
የሀሳብ ረጂም መንገድ፤
ውጣ ውረዱ ድካሙ፡
ምን እንደሆነ ሳላውቀው፤
ማጣፈጫ ቅመሙ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
እጂግ ብዙ ዳከርኩኝ በጣም በብዙ አመፅኩኝ፡
በስሜት ባለማወቅ ብዙ ወንጀልን ፈፀምኩኝ፡
የመፈጠሬን አላማ እኔ ብዘነጋውም፡
የአምላክነትህን እዝነት በፍፁም አላጣሁም፡
በሽተኛ ነው ብሎ የሰው ዘር ቢፀየፈኝም፡
መጥፎ መገለጫወችን ቀምሞ ቢጭንብኝም፡
ያለስሜ ስም ሰጥቶ በግፍ ቢያንቋሽሸኝም፡
በሌለሁበት ዋሽቶ እጂግ ብዙ ቢለኝም፡
እኔ እየወነጀልኩህ፤
አንተ መች አዋረድከኝ፡
ሰወች ጠላት ሲሆኑኝ፤
አምላኬ አንተ መች ተውከኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
በተደጋጋሚ ደፍሬህ፤
ከእዝነትህ መች አራቅከኝ፡
አምፀኸኛልና እኔ አላውቅህም መች አልከኝ፡
ተመለስ እና ወደኔ፤
ተውበት አድርግ እንጂ ያልከኝ፡
የበደልኩህን ቆጥረህ፤
እስረኛ መች አደረከኝ፡
መመሪያህን እየጣስኩ
እያመፅኩህ መች ተውከኝ፡
ባሪያዬ ብለህ በመጥራት
ይበልጥ ነው ያቀረብከኝ፡
እኔን ፍራ ብለህ ገስፀህ፤
ብዙ ፀጋ ነው ያደልከኝ፡
እመነኝ ጀነት አለህ፤
ብለህ ነው የነገርከኝ፡
ጥራት ይገባህ ላንተ፤
እኔን ስላከበርከኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
የቀረቡኝ ሲርቁ ያበላኋቸው ሲበሉኝ፡
ትላንት የረዳኋቸው ዛሬ ላይ ሲያታልሉኝ፡
መልካም ያደረኩላቸው በሌለ ስንት ሲሉኝ፡
ወዳጆች የነበሩ ሁሉ ተከርብተው ሲጠሉኝ፡
ከገደል ያወጣኋቸው፤
ወደ ገደል ሲገፉኝ፡
በእዝነት የዳበስኳቸው፤
እሾህ ጨብጠው ሲያቅፉኝ፡
አብሮ አደግ ጓደኞቼ፤
ኮርተው በንቀት ሲያልፉኝ፡
ሚስጥሬን የነገርኳቸው፤
እቀደዱ ሲሰፉኝ፡
ያመንኳቸው ሁሉ ጓደኞች፤
በቅፅበት ውሳኔ ሲያኮርፉኝ፡
እየተከረባበቱ በወጥመድ ሲማጎ ሲጠልፉኝ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
ወንድምም ሆነ ዘመድ ሞኝ ነህ ብሎ ቢለኝም፡
ጠላት በሩቅ እየሳቀ በበደል ቢወርፈኝም፡
ከፈጠርከኝ ጀምሮ፤
ባሳለፍኳቸው አመታት፡
ጥበቃህ አልተለየኝም፤
ለሰከንድ እንኳን ሰአታት፡
አንተን ማመኔ ብቻ፤
ለኔ ሆኖኛል ብርታት፡
የእውነትም አምላክ ነህና፤
የሚሆኑልህ ሰማዕታት፡
አንድ ብቸኛ ጌታ የአለማት ሁሉ ፈጣሪ፡
የፈለገውን አድራጊ የፈለገውን ሰሪ፡
የፈለገውን ቀጥቶ የፈለገውን መሀሪ፡
ሁሉንም ነገር አጥፍቶ ከኋላ ብቻውን ቀሪ፡
ሞተ የማይባል ጌታ የዘላለም ዘውታሪ፡
ድካም እንቅልፍ የማያውቅ ህያውና ታታሪ፡
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
የሰውነት ቅርፅ የሰጠኸኝን፤
የተዋበ አድርጎ መልኬን፡
ሙሉ አካልን ለግሶኝ፤
አንድም ሳይቀንስ ልኬን፡
በብርሀን የቀየረልኝን፤
ያንን ጨለማ ታሪኬን፡
ከአርሹ በላይ ያለውን፤
መገዛት አልተውም አምላኬን፡
ያለማንነቴ እየዘለፈ ማንም ምንም ቢያወራ፡
ብቻየን እንኳን ብቀር በምድረ-በዳ ጠራራ፡
ቃል እገባለሁ ወላሒ እኔ አንተን ብቻ ልጣራ፡
አንድነትህን እያዜምኩ በማንም ላላጋራ፡
ፈፅሞ እኔ ላልተወው የፈጠርክብኝን አላማ፡
ማንም ቢለፈልፍብኝ ማንም ድምፅ ቢያሰማ፡
ከናፍሮቼ ቢዘጉ እጀ ቢታሰር በካስማ፡
ቃል ገብቻለሁ በአንተ ፊት፤
ካንተ ውጭ ሌላ ላልሰማ፡
በመጨረሻው ነብይ፤
በሙሀመድ አበል ፋጢማ፡
በዚያ በጣፋጭ ቅመም፤
በላከው ለአለም ረህማ፡
በመካው የቀትር ፀሀይ፤
በመድና ላይ ጨረቃ፡
መልካምነቱ በአላም፤
ተጉዞ በማያበቃ፡
በተነገረ ቁጥር፤
ፍቅሩ የሚያሲዝ ሲቃ፡
በርሱ መንገድ ከመጓዝ፤
በፅሞ እኔ አልቦዝንም፡
አንተን አንድ አምላክ አምኘ፤
በፍፁም እኔማ አላዝንም፡
ስህተቴን እያስተካከልኩ፤
እስክሞት አመልክሀለሁ፡
አንተን በማምለኬ ላይ፤
ፅናትን እማፀናለሁ፡
አምላኬ በመሆንህ፤
ከልቤ ደስተኛ ነኝ፡
ግና በወንጀል ተለውሻለሁ
በዕዝነትህ ከዕሳት አድነኝ፡
የጀነት ነህ ብለህ አስደሳኝ፤
በስራዬ ሳይሆን በዕዝነትህ፡
ከዱንያ መከራም አውጣኝ፤
ጠብቀኝ በበረከትህ፡
እወድሀለሁ አምላኬ
የምገልፅበት ቃል የለኝም፡
በባርነቴ አምኛለሁ፤
ለማንም ግድ አይሰጠኝም፡
የሰወች ወቀሳ ትችን፤
ምንም አይሰማኝም፡
አንተን ባላወቅኩበት ዘመን፤
ብዙ ጥፋቶችን ብመኝም፡
በመሀይምነት ታውሬ፤
ግዙፍ ስህተት ብቀኝም፡
ወንጀለኛ ሆኘ እንኳን፤
ጥበቃህ አልተለየኝም፡
#አምላኬ______እወድሀለሁ።
〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️
✍️በኑረዲን
Audio
۞ إِنَّ اللَّهَ يَأْمُرُ بِالْعَدْلِ وَالْإِحْسَانِ وَإِيتَاءِ ذِي الْقُرْبَىٰ وَيَنْهَىٰ عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ وَالْبَغْيِ ۚ يَعِظُكُمْ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّرُونَ
አላህ በማስተካከል፣ በማሳመርም፣ ለዝምድና ባለቤት በመስጠትም ያዛል፡፡ ከአስከፊም (ከማመንዘር)፣ ከሚጠላም ነገር ሁሉ፣ ከመበደልም ይከለክላል፡፡ ትገነዘቡ ዘንድ ይገስጻችኋል፡፡
وَأَوْفُوا بِعَهْدِ اللَّهِ إِذَا عَاهَدتُّمْ وَلَا تَنقُضُوا الْأَيْمَانَ بَعْدَ تَوْكِيدِهَا وَقَدْ جَعَلْتُمُ اللَّهَ عَلَيْكُمْ كَفِيلًا ۚ إِنَّ اللَّهَ يَعْلَمُ مَا تَفْعَلُونَ
ቃል ኪዳንም በገባችሁ ጊዜ በአላህ ቃል ኪዳን ሙሉ፡፡ መሓሎቻችሁንም ከአጠነከራችኋት በኋላ አላህን በእናንተ ላይ በእርግጥ መስካሪ ያደረጋችሁ ስትኾኑ አታፍርሱ፡፡ አላህ የምትሠሩትን ሁሉ ያውቃልና፡፡🤍
አላህ በማስተካከል፣ በማሳመርም፣ ለዝምድና ባለቤት በመስጠትም ያዛል፡፡ ከአስከፊም (ከማመንዘር)፣ ከሚጠላም ነገር ሁሉ፣ ከመበደልም ይከለክላል፡፡ ትገነዘቡ ዘንድ ይገስጻችኋል፡፡
وَأَوْفُوا بِعَهْدِ اللَّهِ إِذَا عَاهَدتُّمْ وَلَا تَنقُضُوا الْأَيْمَانَ بَعْدَ تَوْكِيدِهَا وَقَدْ جَعَلْتُمُ اللَّهَ عَلَيْكُمْ كَفِيلًا ۚ إِنَّ اللَّهَ يَعْلَمُ مَا تَفْعَلُونَ
ቃል ኪዳንም በገባችሁ ጊዜ በአላህ ቃል ኪዳን ሙሉ፡፡ መሓሎቻችሁንም ከአጠነከራችኋት በኋላ አላህን በእናንተ ላይ በእርግጥ መስካሪ ያደረጋችሁ ስትኾኑ አታፍርሱ፡፡ አላህ የምትሠሩትን ሁሉ ያውቃልና፡፡🤍