La tehzen
94 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
በረመዳን በብዛት የሚፈፀሙ ስህተቶች

① ሶላት ሳይሰግዱ መፆም፣
② ሌሊቱን በጫት ካሳለፉ በኋላ ሱሑርን አስቀድሞ በመመገብ ፈጅር
ሳይሰግዱ መተኛት፣
③ ቀኑን በእንቅልፍ፣ ሌሊቱን በተከታታይ ፊልም/ ሙሰልሰላት ማሳለፍ፣
④ ረመዳንን ጠብቆ መንዙማና ነሺዳ እየለቀቁ ሰዎችን ከቁርኣን ማዘናጋት፣
⑤ ተራዊሕን በንቃት እየሰገዱ ፈጅር ሶላትን በእንቅልፍ ማሳለፍ፣
⑥ ተራዊሕ ላይ በየ አራቱ ረከዐ መሐል የቢድዐና የሺርክ እንጉርጉሮዎችን
ማስገባት፣
⑦ የተራዊሕ ኢማሞች ከሶላቱ ይልቅ ለቁኑት ዱዓእ የበለጠ ትኩረትና
ጊዜ መስጠት፣
⑧ መግሪብ ሶላት ሲጠናቀቅ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ለፊጥራ መጣደፍ
(ሰጋጆችን የሚያቋርጥ፣ የሰው ጫማ የሚያቀያይር፣…ብዙ ነው)
⑨ ሌሊት ላይ "ተሰሐሩ " እያሉ በእስፒከር መጮህ፣
(10) የሱሑር ጊዜ ሳያልቅ ለጥንቃቄ በሚል ቀድሞ አዛን ማድረግ፣
(11) ሱሑር ላይ "ነወይቱ ሰውመ ገዲን" እያሉ በቃል መነየት፣
(12) እያንቀላፉ ተራዊሕ መስገድ፣
(13) ልጆች "እንፁም" ሲሉ ማበረታታት ሲገባ መከልከል፣ "ውሃ
አያፈጥርም፣ ተደብቀህ ብላና ትፆማለህ" እያሉ መዋሸትና ውሸት
ማለማመድ፣
(14) ሴቶች በተጋነነ የምግብ ዝግጅት ሰፊ ጊዜያቸውን ማቃጠል፣
(15) ሴቶች ሽቶ ተቀብቶ ለተራዊሕ መውጣት፣
(16) በተራዊሕ ወቅት የሴቶችና የወንዶች አላስፈላጊ መዝረክረክ፣
(17) ሃሜት፣
(18) ፊጥራ ላይ ከመጠን በላይ መመገብ፣
(19) ቀኑን በካርታ፣ በዳማ፣ ወዘተ ማሳለፍ፣
(20) ሙዚቃ ማዳመጥ፣
(21) የሰው ስራ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ጧት በሰዓት አለመግባት (አማና
መጠበቅ፣ ቃልን ማክበር ግድ ይላል። ግዴታ ያልሆኑ ዒባዳዎች ተፅእኖ
የሚያሳድሩብን ከሆነ መተው ወይም መቀነስ ነው)፣
(22) በተለይ በስራ ቦታዎች ላይ በመንዙማና በነሺዳ ማሳለፍ (መሆን
ያለበት ከተመቼ ቁርአን መቅራት፣ ካልሆነ ዚክር ማድረግ ወይም ደዕዋ
ማዳመጥ፣ ካልሆነ ዝምታ ይሻላል።)
(23) ለይለተል ቀድርን ለማየት ሰማይ ሰማይ እያንጋጠጡ መጠበቅ
(የሚታይ ነገር የለም)፣
(24) አንዳንድ አካባቢዎች ዒሻን በጣም በማዘግየት ሰው ጀማዐ ላይ
እንዳይካፈል እንቅፋት መሆን፣
(25) አንዳንድ አካባቢዎች መስጂድ ውስጥ ጫት ይዞ ገብቶ መቃም፣
(26) አንዳንድ አካባቢዎች "ተርቲብ" ብለው ንፍሮ፣ ቆሎና መሰል
ምግቦችን ወደ መስጂድ እንዲያቀርቡ ሰዎችን ማዘዝ፣ ወዘተ

By Ibnu munewor

↷ ⇣🌹⇣↷
https://t.me/httpsLatahzen
መንገደኛ እና ፆም፡-

♦️መንገደኛ ፆምን መፍታት ስለተፈቀደለት ካልፆመ ከጉዞው መልስ ያልፆማቸውን ቀናት ቀዳእ ማውጣት ይኖርበታል፡፡ ይህን በተመለከተ አላህ እንዲህ ብሏል፦
فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ ٱلشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ ۖ وَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍۢ فَعِدَّةٌۭ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ
 البقرة ١٨٥

“ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት”፡፡አል-በቀራህ 185

ነብዩም (ﷺ) በጉዞ ላይ ስለመፆም ሲጠየቁ “ከፈለግክ ፁም ካስፈለገክም ፍታ” ብለዋል፡፡ እሳቸውም ወደ መካ ጉዞ ላይ ሳሉ ፆም ላይ ቆይተው ኹደይድ የሚባል ስፍራ ሲደርሱ ፆማቸውን ፈተው ሰሃቦችም እንዲፈቱ አዘዋል፡፡ ፆምን መፍታት የሚፈቀድበት የጉዞ መጠን ሰላትን ማሳጠር በሚፈቀድበት የጉዞ መጠን ሲሆን እሱም ሰማንያ ኪሎ ሜትር ርቀት ነው፡፡ እንዲሁም ፆምን መፍታት የሚፈቀድበት የጉዞ አይነት የኃጢአት ጉዞ ወይም ፆምን ለማፍረስ ብቻ የታቀደበት ጉዞ መሆን የለበትም፡፡

መንገደኛ ቢፆም ፆሙ ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡ አነስ እንዲህ ብለዋል፦
“ከነቢዩ(ﷺ) ጋር ጐዞ ላይ ስንሆን ከመካከላችን የሚፆምና የሚፈታ ቢኖርም የፆመው የፈታውን የፈታውም የፆመውን አያነውርም ነበር”
📚አል ቡኻሪ (1947)

መንገደኛ ሲፆም የሚጐዳ ወይም ፆም የሚከብደው ከሆነ ግን ባይፆም ይመረጣል:: ምክንያቱም ነቢያችን (ﷺ) አንድ ሰው በጉዞ ላይ ሳለ በመፆሙ ስለተጎዳ አቅራቢያው ያሉ ሰዎች ከፀሐይ ሲጠልሉት ተመልክተው
“ጉዞ ላይ መፆም ከመልካም ስራ አይደለም” ብለዋል፡፡
📚አል ቡኻሪ (1946)

↷ ⇣🌹⇣↷
https://t.me/httpsLatahzen
አፍጡር ላይ የሚባል

ذَهَبَ الظَّمَأُ وَابْتَلَّتِ الْعُرُوْقُ وَثَبَتَ اْلأَجْرُ إِنْ شَاءَ اللهُ.

‘ዘሐበዝዘመኡ ውበተልለቲል ዑሩቁ፣ ወሠበተል አጅሩ ኢንሻአህ

اَللَّهُمَّ إِنِّيْ أَسْأَلُكَ بِرَحْمَتِكَ الَّتِيْ وَسِعَتْ كُلَّ شَيْءٍ أَنْ تَغْفِرَ لِيْ
, አላህ ሆይ! ምህረትን ትለግሰኝ ዘንድ ሁሉንም ነገር ባዳረሰችው እዝነትህ እማፀንሐለሁ፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/httpsLatahzen
ኢብኑል ቀይም - ረሂመሁላሁ ተአላ እንዲህ ይላል :-

"ፆመኛ ማለት አካላቱ ከወንጀል
ምላሱ ከውሸትና ከመጥፎ ንግግር ከውሽት ምስክርነት
ሆዱ ከምግብና ከመጠጥ
ብልቱ ከዝሙት የፆመ ነው
ከተናገረ ፆሙን የሚጠፋ ንግግር አይናገርም ከሰራም ፆሙን የሚያበላሽ ነገር አይሰራም "

📚አል ዋቢሉ ሰይብ ገፅ ( 43 )
https://t.me/httpsLatahzen
Channel photo removed
ما حكم متابعة الإمام في التراويح بالمصحف ؟ لفضيلة الشيخ الدكتور…
◉ቁርአን ይዞ ኢማምን መከታተል
------------------------------------------
➜ኢማሙን በተራዊህ ሰላት ሲያሰግድ በቁርአን መከታተል ፍርዱ ምንድን ነው ?

◎ما حكم متابعة الامام في التراويح في المصحف?

◁◦ لا يجوز. ابداً عليك ان تنصت. لا تتابعه ابداً.
إنما عليك أن تنصت للقراءة ولا تقرأ معه.

لا تتابع معه في المصحف ولا تقرأ معه اثناء قراءته. كل ذلك مخالفٌ بل يعني يخشى ان لا تصح صلاتك.

لانه يجب عليك الانصات وجوباً. يجب عليك ومتابعة الامام بالانصات◦
▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▬


🎙فضيلة الشيخ د.صالح السحيمي
📨 ፆመኛው ማን ነው ?


📌 ﻗـﺎﻝ ﺍﺑﻦ ﺍﻟﻘﻴِّﻢ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ :

« ﻭﺍﻟﺼَّﺎﺋﻢ ﻫﻮ ﺍﻟَّﺬﻱ ﺻﺎﻣﺖ ﺟﻮﺍﺭﺣﻪ ﻋﻦ ﺍﻵﺛﺎﻡ, ﻭﻟﺴﺎﻧﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻜﺬﺏ ﻭﺍﻟﻔﺤﺶ ﻭﻗﻮﻝ ﺍﻟﺰُّﻭﺭ, ﻭﺑﻄﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻄَّﻌﺎﻡ ﻭﺍﻟﺸَّﺮﺍﺏ, ﻭﻓﺮﺟﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﺮَّﻓَﺚ ؛

«ፆመኛ ማለት አካሎቹን ከሀጢአት የጸዱ፤ ምላሱን ከአሉባልታ፣ ከውሸት እና ከአጸያፊ ንግግር የጠበቀ፤ ሆዱን ከምግብ ፣ ከመጠጥ እና ብልቱን (በቀን ክፍለ ጊዜ) ከግብረ ስጋ ግንኙነት የጠበቀ ነው።

ﻓﺈﻥْ ﺗﻜﻠَّﻢ ﻟﻢ ﻳﺘﻜﻠَّﻢ ﺑﻤﺎ ﻳﺠﺮﺡ ﺻﻮﻣﻪ, ﻭﺇﻥ ﻓﻌﻞ ﻟﻢ ﻳﻔﻌﻞ ﻣﺎ ﻳﻔﺴﺪﺻﻮﻣﻪ,

ፆመኛ ከተናገረ:– ፆሙን በማይጎዳ ስራ ከሰራ ጾሙን በማያበላሽበት መልኩ ይሰራል።

ﻓﻴﺨﺮﺝ ﻛﻼﻣﻪ ﻛﻠُّﻪ ﻧﺎﻓﻌًﺎ ﺻﺎﻟﺤًﺎ, ﻭﻛﺬﻟﻚ ﺃﻋﻤﺎﻟﻪ, ﻓﻬﻲ ﺑﻤﻨﺰﻟﺔ ﺍﻟﺮَّﺍﺋﺤﺔ ﺍﻟَّﺘﻲ ﻳﺸﻤُّﻬﺎ ﻣﻦ ﺟﺎﻟﺲ ﺣﺎﻣﻞ ﺍﻟﻤﺴﻚ،

ፆመኛ ጠቃሚና ቁምነገር ያለው ንግግር እና ስራ ሲሰራ ምሳሌው ልክ ከሽቶ ተሸካሚ ሰው ጋር ተቀምጦ መልካም ሽታ እንደሚያገኝ ሰው ነው።

ﻛﺬﻟﻚ ﻣﻦ ﺟﺎﻟﺲ ﺍﻟﺼَّﺎﺋﻢ ﺍﻧﺘﻔﻊ ﺑﻤﺠﺎﻟﺴﺘﻪ, ﻭﺃَﻣِﻦ ﻓﻴﻬﺎ ﻣﻦ ﺍﻟﺰُّﻭﺭ ﻭﺍﻟﻜﺬﺏ ﻭﺍﻟﻔﺠﻮﺭ ﻭﺍﻟﻈُّﻠﻢ,

ከፆመኛ ጋር የተቀመጠም ሰው መልካም ነገርን እንጂ ሌላ አያገኝም። ከተለያዩ መጥፎ ነገሮች እንደ ቅጥፈት፣ ውሸት፣ ጥመትን እና በደልን ሁሉ ሰላም ይሆናል።

ﻫﺬﺍ ﻫﻮ ﺍﻟﺼَّﻮﻡ ﺍﻟﻤﺸﺮﻭﻉ ﻻ ﻣﺠﺮَّﺩ ﺍﻹﻣﺴﺎﻙ ﻋﻦ ﺍﻟﻄَّﻌﺎﻡ ﻭﺍﻟﺸَّﺮﺍﺏ ... ؛

ይህ ነው ትክክለኛና ህጋዊ ፆም ማለት ከምግብና መጠጥ ብቻ መታቀብ ፆም አይባልም።

ﻓﺎﻟﺼَّﻮﻡ ﻫﻮ ﺻﻮﻡ ﺍﻟﺠﻮﺍﺭﺡ ﻋﻦ ﺍﻵﺛﺎﻡ, ﻭﺻﻮﻡ ﺍﻟﺒﻄﻦ ﻋﻦ ﺍﻟﺸَّﺮﺍﺏﻭﺍﻟﻄَّﻌﺎﻡ ؛

ፆም ማለት አካላትን ከሀጢአት እና ሆድን ከምግብና መጠጥ በመታቀብ መፆም ነወ።

ﻓﻜﻤﺎ ﺃﻥَّ ﺍﻟﻄَّﻌﺎﻡ ﻭﺍﻟﺸَّﺮﺍﺏ ﻳﻘﻄﻌﻪ ﻭﻳﻔﺴﺪﻩ, ﻓﻬﻜﺬﺍ ﺍﻵﺛﺎﻡ ﺗﻘﻄﻊ ﺛﻮﺍﺑَﻪ, ﻭﺗﻔﺴﺪُ ﺛﻤﺮﺗَﻪ, ﻓﺘُﺼَﻴِّﺮﻩ ﺑﻤﻨﺰﻟﺔ ﻣﻦ ﻟﻢ ﻳﺼُﻢ ».

ምግብና መጠጥ ፆምን እንደሚያጠፋ ሁሉ ሀጢአትም የፆምን ምንዳ ያጠፋል፣ ውጤቱን ያበላሻል። በዚህም ምክንያት ልክ ፆም እንዳልጾመ ተደርጎ ይታሰባል።

📜 [ ﺍﻟﻮﺍﺑﻞ ﺍﻟﺼَّﻴِّﺐ ص(31 ، 32 ) ]



┄┄┉┉✽‌»‌🌹🌹»‌✽‌┉┉┄┄
ሼር 👇JoiN👇 & Share
https://t.me/httpsLatahzen
ما تيسر من سورة المائدة _ تــلاوة بديعة _ القارئ عبدالله بصفر
مجموعات تلاوات خاشعة
ቁርአን የአላህ ስጦታ‼️

ቁርአንን በማስተንተን ከማንበብ የበለጠ ለቀልብ የሚጠቅም ነገር የለም!

♦️ቆንጆ የምሽት ግብዣ
01 የረመዷን ምክር በሸይኽ ሐሰን ገላው (1443)
የረመዷን ምክር 01

በሸይኽ ሐሰን ገላው ሃፊዞሁሏህ
02 የረመዷን ምክር, በወንድም ሰዓድ ዓብዱል’ለጢፍ ሃፊዞሁሏህ (1443)
የረመዷን ምክር 02

በወንድም ሰዓድ ዓብዱል`ለጢፍ ሃፊዞሁሏህ
ፆመኛ ሊጠነቀቃቸው የሚገቡ ከፊል ነገሮች

① ሀሜት፣ውሸት ፣ነገረኝነት እና ማንኛውንም አሉባልታ ወሬዎች
ፆመኛ የሆነ ሰው እነዚህን ሊጠነቀቅ ይገባዋል እነዚህን ነገሮች ካልተጠነቀቀ እየተራበ እና እየተጠማ ያለው በከንቱ ነው ማለት ነው ።
የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ በለዋል
"የውሸት ንግግርን እና በእሱ መስራትን ያልተወ ሰው ምግብ እና ፆም በመተዎ ለአላህ ጉዳይ የለውም" [ቡኻሪ 6057]

② ውዱ በሚያደርግ ግዜ በአፍንጫው ውሃ ሲያስገባ(እስቲንሻቅ ሲያደርግ) በደንብ አለመሳብ
የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም "ፀመኛ የሆንክ ግዜ ሲቀር በአፍንጫህ በደንብ ውሀን ሳብ" ብለዋል [ሱነን አቢ ዳውድ 2366]
ከዚህ ሐዲሥ እንደምንረዳው ውሃን የውዱ ግዜ በአፍንጫ በደንብ ወደ ውስጥ በመሳብ ማስገባት ሱና ነው ግን የፆም ግዜ ክልክል ነው ምክያቱም በደንብ ውሃውን ከሳብን ወደ ጉሮሯችን መግባቱ ስለማይቀር ነው በፆም ግዜ የተከለከለው።

③ አብዛሀኛውን ወይን ብዙውን የቀን ክፍል መተኛት ለፆመኛ ጥሩ አይደለም ምክኒያቱም ውድ የሆነውን ግዜ ያለምንም ኢባዳ እንዲያልፍ ያደርግበታል (እንቅልፍም ኢባዳ አይደል ላላችሁኝ አዎ ግን መባል የያዘው ሁሉም በልክ ይሁን ነው)
ታላቁ ዐሊም ኢብኑ ዑሠይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ:-
"ለፆመኛ በሶላት፣አላህን በማውሳት(በዚክር)፣በዱአና ቁራኣን በመቅራት (ግዜውን ሊያሳልፍ) ይገባዋል። ሰው በፆመ ግዜ ነፍሱን በተለያየ ኢባዳ ካላመዳት ይህ ለሱ ይገራለትል። (ግን በተቃራኒው ነፍሱን)
በስንፍና እና ረፍት(እንቅልፍ) በማብዛት
ከሆነስ ያላመዳት እሄንኑ ስንፍናውን እንጅ ሌላን አይለምድም (ሁኔታው እንዲህ ከሆነች) የፆመ ግዜ በእርሱ ላይ መልካም ስራ እና ዒባዳዎች ይከብዱበታል" [መጅሙኡል ፈታዋ ወረሳኢል 19/171]

④ በራሱ ላይ ስሜቱን የማይተማመን ሰው ሚስቱን መሳም ይህም በፆም ሰአት ሊጠነቀቁት የሚገባ አደጋ ነው።
ኢብኑ አብዲል በር (ረሂመሁላህ)
"ሚስቱን ከመሳም የተነሳ ፆም የሚያበላሽ ነገር የሚመጣበት ለሆነ ሰው መሳምን(ይፈቀዳል) ያለ (ዐሊም) አንድንም አላውቅ" ይላሉ [አት-ተምሂድ 5/114]
ስለዚህ በራሱ ላይ ስሜቱን የማይተማመን ሰው ከንደዚህ አይነት ድርጊት እራሱን ሊቆጥብ ይገባዋል
አላህ ፆማቸውን ከተቀበላቸው ያድርገን

⑤ ፉጡርን ማዘግየት ብዙ ሰዎች ፀሀይ ተገባ በሗላ ፉጡርን የሚያዘገዩ አሉ አንዳዶች አዛንኳ እየተደረገ ከሶላት በሗላ ካልሆነ እንጅ የማያፈጥሩ አሉ ይህ ስህተት ነው። ፀሃይ መግባቱ ከተረጋገጠ ፉጥርን ማቻኮል ሱና ነው። ነቢዩ(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ "ሰዎች ፉጡርን እስካቻኮሉ ድረስ ከመልካም ነገር አይወገዱም" 【ቡኻሪና ሙስሊም】