La tehzen
94 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
Forwarded from Deleted Account
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሴት ልጅ ከፊቷ ፀጉር ከበቀለባት ማስወገድ እንዴት ይታያል??
በተለይ ቀድሞ ቀመስ ላይ ቀድሞ ቀመስ ማለት የከንፈራችን የላይኛዉ ማለት ነዉ
እንደዚሁ የእጇን ፀጉር የእግሯን ፀጉር ለባሏ ለመዋብ አስባ ብታስወግደዉ እንዴት ይታያል??
መልስ
የእጅ ላይ የእግር ላይ እንደዚሁ በሌላ ቦታ የሚወጡ ፀጉሮችን ማስወገድ የሚከለክል ነገር የለም
የፊት ፀጉር ማስወገድ በሚለዉ ተፍሲል አለዉ ፊቱዋን የሚረብሽ አዛ የሚያደርግ ከሆነ ብታስወግደዉ ችግር የለዉም። የቅንድብ ፀጉር ማስወገድ ረሱል ይሄን የፈፀመ ረግመዋል ከትላልቅ ወንጀሎች ነዉ። ሁሉንም አስወግዳ የሆነ ነገር ብታደርግበት እንኳ መቀባት ይመስል ከፊል መሀይም ሴቶች እንደሚፈፅሙት አመፀኞች ወይም የተወሰነዉን እንኳ ቅኖድብ ማስወገድ ይሄ ሁሉ የተከለከለ ነዉ ያገዘችም የተረገመች ናትያስወገደችዉ በመቁረጥ ይሁን በመንጨት ይሁን በመላጨት ወይም በማስወገጃ ነገሮች የቅንድብን ፀጉር ማስወገድ በማንኛዉ ሁኖታ ክልከላዉ ብርቱ (ጠንካራ)የሆነ ክልከላ ነዉ
👇👇👇
Forwarded from Deleted Account
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ተዉሂዲን ተማር አስተምር ‼️

↪️ሸይኽ ሷሊህ አል- ፈውዛን((ሃፊዘሁሏህ))

➧እንዲህ አሉ:-

ቡዙዎቹ ሰዎች ተውሂድ ምን ማለት ነው ተብለው ቢጠየቁ መመለስ የማይችሉትን ተውሂዲ ተማር!!

✍️ምክኒያቱም ሰዎች የተውሂድን ትርጉም እና በውስጡ ለማለት የተፈለገበትን ነገር አያውቁም!!

✍️ተውሂድ እሱ ከፍ ያለው ጌታችንን አላህን በዓምልኮ ብቸኛ ማዲረግና መነጠል ሲሆነ ሽይኽ መሃመዲ ዓብዱል-ወሃብ አላህ ይዘንላቸውና እንዳሉት ተውሂድ ማለት የሚገባውን አምልኮ ተገቢውን አምልኮ(ዒባዳን) በመስጠት አላህን ብቻውን መነጠል መሆኑን እወቅ!!

✍️ተውሂድ ማለት በጌትነቱ፤ነገራቶችን ሁሉ ፈጣሪ መሆኑ፤ሲሳይን ሰጭ መሆኑ፤የሚገል፤ሂያው የሚያዲረግ የሚለው ብቻውን በቂ እና ተውሂድ አይደለም ይህ ተውሂደል-አረቡቡያ(በጌትነቱ ማመን) ሲሆን በዚህ የተውሂድ ዘርፍ በፊት የነበሩ ጃሂሎች ያምኑና ያርጋግጡ ነበር በጌትነቱ አልካዱም !!

✍️ነገር ግን ከአላህ ጋር ሌላ ነገርን በመገዛታቸውና አምልኮን ለሌላ አካል በመስጠታቸው ምክኒያት ሙሽሪኮችና እሳት(ጀሃነብ)ውስጥ ዝንታለም ዘወታሪ የማይወጡ የሆኑት ከነሡ(ከሙሽሪኮቹ) ከመሞታቸው በፊት ወደ አላህ ቶብተው በመመለስ ተውሂድን ወይም አምልኮን ለአላህ ብቻ አጥብቀው የያዙት ሲቀሩ!!
Forwarded from Deleted Account
ጉድና ጉድ ክፍል①
=======^======
እግዚአብሄር :– እኔ ሰው አይደለሁም።( ሆሴዕ 11:9 )
ኢየሱስ :– እኔ ሰው ነኝ።(ዮሐንስ ወንጌል 8:40 )

( ትንቢተ ሆሴዕ 11:9 ) እኔ እግዚአብሔር አምላክ ነኝ
እንጂ #ሰው_አይደለሁምና

ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ሰው ነኝ ይላል

(የዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ነገር ግን አሁን ከእግዚአብሔር
የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን #ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ::

ነገር ግን ነገር ግን........
ኢየሱስ ሰው ነኝ አምላክ አይደለሁም እያለ እየተማፀናቹ እናንተ ግን አይ ኢየሱስ አምላክ ነህ፣ ጌታ ነህ፣ ፈጣሪ ነህ ወዘተ..... ብላችሁ የምታመልኩት ከሆነ ይህን መልዕክት በአንደበቱና በግልፅ አስቀምጦላቹሃል፣

የማቴዎስ ወንጌል 7 ፣ 21 በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ #ጌታ_ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ #የሚለኝ_ሁሉ_መንግሥተ_ሰማያት_የሚገባ_አይደለም

22 በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።

23 የዚያን ጊዜም። #ከቶ_አላወቅኋችሁም#እናንተ_ዓመፀኞች#ከእኔ_ራቁ_ብዬ_እመሰክርባቸዋለሁ

ስለዚህ ኢየሱስን ምትወዱት ከሆነ ቃሉንና ምክሩን ስሙ! ከፊቴ ጥፉ አላውቃችሁም እላቹሃለው እያላቹ ነው።

በወንጌል ካላፈሩ እስኪ ሼር አድርጉት
ይህ 100% ከመፅሀፍ ቅዱስ ከ (ወንጌል) ስለወጣ ሁሉም #ክርስቲያን #ሼር ያድርገው።

📱 “እየሱስ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የፈጣሪ መልእክተኛ”
 ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄
💥1•
“የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የኣብ ነው እንጂ የኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 14:24)

የማን ነው ኣለ?
••••• የላከኝ የኣብ√

በዚህ ጥቅስ መሰረት ወልድ( እየሱስ) የኣብ መልእክተኛ ነው።

💥 2•
“እኔ ከራሴ ኣንዳች ላደርግ ኣይቻለኝም እንደሰማሁ እፈርዳሎ ፍርዴም ቅን ነው የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን ኣልሻምና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:30)

የማን ፈቃድ ኣለ?
••••• የላከኝን√
ማነው የላከው?

እየሱስ ኣምላክ ከሆነ, ኣምላክን የሚልክ ደግሞ ማነው?
ኣምላክ ይልካል ወይስ ይላካል?

💥 3•
“ቃሌን የሚሰማ የላከኝም የሚያምን የዘላለም ሂወት ኣለው”( የዬሐንስ ወንጌል 5:24)

ማንን የሚያምን ኣለ?
••••••• የላከኝን√
ማነው የላከው?

💥 4•
“ኢየሱስም ጮኸ እንዲህም ኣለ በኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 12:44)

በኢየሱስ ማመን በማን ማመን ነው?
•••••• በላከው√
ማነው የላከው?

💥 5•
“እኔ ከራሴ ኣልተናገርሁምና ነገር ግን የላከኝ ኣብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 12:49)

እዚህ ላይ ደግሞ ” የላከኝ ኣብ” በማለት የኣብ መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ተናግርዋል።

💥6•
“የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 8:26)

ኢየሱስን የላከ እውነተኛው ማነው?

💥 7•
“የላከኝም ኣብ ሰለኔ ይመሰክራል”( የዬሐንስ ወንጌል 8:18)

ማን ኣለ?
••••• የላከኝ ኣብ√

💥8•
“ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም ኣላቸው ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ 7:16)

ትምህርቱ ከማን ነው?•••••ከላከው√
ማነው የላከው?

💥 9•
“እኔም በራሴ ኣልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 7:28)

ኢየሱስን የላከ የማይታወቅ እውነተኛው ማነው?

💥 10•
“እኔንም የጣለ የላከኝም ይጥላል”( ሉቃስ ወንጌል 10:16)

የላከኝን? ማነው የላከው?

💥11•
“ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር ኣልተላክሁም ኣለ”( ማቴዎስ 15:34)

ወደ እስራኤል መልእክተኛ ኣድርጎ የላከው ማነው?

💥12•
“ኣንተም እንደላክኸኝ ኣመኑ”( የዬሐንስ ወንጌል 17:8)

ማነው የላከው?

💥13•
“ይህ የማደርገው ስራ ኣብ እንደላከኝ ስለኔ ይመሰክራልና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:36)

ኣብ እንደላከኝ በማለት መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ይናገራል።

💥14•
“የላከኝ ኣብም እርሱ ስለኔ መስክሮዋል”( የዬሐንስ ወንጌል 5:37)

ምን ያደረገኝ ኣብ?
•••••••• የላከኝ√

💥15•
“እኔ ከእግዚኣብሄር ወጥቼ መጥቻለሁና እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ ኣልመጣሁም”( የዬሐንስ ወንጌል 8:42)

ከእግዚኣብሄር የተላከ መልእክተኛ መሆኑን ይነግረናል።

💥16•
“ባሪያ ከጌታው ኣይበልጥም መልእክተኛም ከላከው ኣይበልጥም”
( የዬሐንስ ወንጌል 13:16)
መልእክተኛው ማነው? ላኪውስ ማነው?

💥17•
“ኣብ እንደላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኃለሁኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 20:21)

ኣብ እንደላከኝ በማለት የኣብ መልእክተኛ እንደሆነ በግልፅ ነግሮናል።

==============∞
ስለዚህ እራሱ አምላክ መሆኑን የነገረንን ጌታ አላህን እናምልክ

إنَّنِي أنا اللهُ لآ إلَٰه إلّآ أنَاْ فَاعْبُدنِي وَأَقِمِ الصَّلَوٰة لِذِكْرِي
እኔ አላህ ነኝ ። ከእኔ ውጪ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም።ተገዛኝ።ሰላትንም(በእርሷ) እኔን ለማስታወስ ስገድ።ሱረቱ ጣሃ አንቀፅ 14
ሼር ሼር ሼር👇👇
https://t.me/Pointing_to_the_True_Religion
https://t.me/Pointing_to_the_True_Religion
እኛ ብንሆን ኖሮስ!
~
ለኢማሙ አሕመድ የሆነ ሰው ስም ተነሳላቸው።
* "እኔ ስለሱ መልካምን እንጂ አላውቅም" አሉ።
* "አንተ በሱ ላይ የምትናገረው እሱ ባንተ ላይ ከሚናገረው ይለያል" አላቸው አንዱ። (በክፉ ያነሳሀል ማለቱ ነው።)
* ፈገግ ብለው "እኔ ስለሱ መልካምን እንጂ አላውቅም። ስለሚናገረው እሱ ያውቃል። የማላውቀውን እንድናገር ነው የምትፈልገው?" አሉ።
ቀጥለውም እንዲህ አሉ፦
"ሳሊምን አላህ ይዘንላቸው። (ሳሊም የኢብኑ ዑመር ረዲየላሁ ዐንሁ ልጅ ናቸው።) አንዴ ግመላቸው የሌላን ሰው ግመል ገፋች። ሰውየው በዚህን ጊዜ ለሳሊም 'ክፉ ሽማግሌ ትመስለኛለህ!' አላቸው። 'አልራቅክም!' አሉት። (ልክ ነህ! እያሉት ነው። ኢማሙ አሕመድም ለራሳቸው ተመሳሳይ ነገር መጠቀማቸው ነው።)
ምንጭ፦ አልወረዕ ሊልመርወዚ፡ 197]

* እስኪ እራሳችንን በሳሊም ቦታ አድርገን እናስብ። ምን ይሆን ነበር ምላሻችን? አላሁል ሙስተዓን!
* እስኪ እራሳችንን በኢማሙ አሕመድ ቦታ አድርገን እናስብ። ምን ይሆን ነበር ምላሻችን? አላህ ይድረስልን
……… ስድስቱ የተውበት መስፈርቶች ………
===========================
በህይወታችን ብዙ ጊዜ ወንጀሎችን እንፈፅማለን። አላህ ያደለው በወንጀሉ አላህ ፊት እንዳይጠየቅ ተውበት ማድረግን ያስባል። ግን ስንቱ ነው ተውበቱ መስፈርቶችን የሚያሟላ እንዲሆን የሚጨነቀው? እራሳችንን በሚገባ ጠይቀን እናውቃለን?! ለመሆኑ መስፈርቶቹን ምን ያህሎቻችን በሚገባ እንለያቸዋለን? ለማያውቁ ጥቆማ፣ ለሚያውቁ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ እጠቅሳለሁ። የተውበት መስፈርቶች ስድስት ናቸው። እነሱም:–

① ኢኽላስ: – አላህን ብቻ በማሰብ መፈፀም ማለት ነው። አንድ ሰው ወንጀልን የሚተወው ዱንያዊ ጥቅሞችን አስቦ ከሆነ የመጀመሪያውን የተውበት መስፈርት ዘንግቷል።
② ወንጀሉን ማቆም:– አንድ ሰው የሚፈፅመውን ወንጀል ባላቋረጠበት ሁኔታ "ቶብቻለሁ" ቢል ቀልድ ነው የሚሆነው። ስለዚህ ተውበት ያሰበ ሰው ጥፋቱን በቀጠሮ ሳይሆን ቀጥታ ሊያቆም ይገባል።
③ ወደ ጥፋቱ ዳግም ላይመለሱ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ መድረስ። አንድ ሰው ከወር ቡ በኋላ እንደሚመለስ እያሰበ ረመዳን ሊገባ ሲል አንድን ወንጀል ቢተው መስፈርት ስላላሟላ ተውበት አድርጓል ማለት አይቻልም።
④ በወንጀሉ መፀፀት፦ ሰውየው ሲፈፅመው በቆየው ወንጀል ላይ ደንታ ቢስ ከሆነ ተውበቱ የሐቂቃ አይደለም። ፀፀቱ "ሰው ምን ይለኛል" ወይም "ክብሬ ጎደፈ" በሚል ሳይሆን የጌታውን ህግ በመጣሱ ሊሆን ይገባል። ለምሳሌ ብዙ ሰዎች ዝሙት ፈፅመው ጌታቸው ዘንድ ካለው ሂሳብ ይልቅ ዱንያ ላይ ያለው የሰው ወሬ ሲያስጨንቃቸው ይፀፀታሉ። እንዲህ አይነት ፀፀት የተውበትን መስፈርት አያሟላም። ይልቅ ከዛሬው የበዛ ህዝብ ፊት ነገ በአኺራ መዋረድ ከመምጣቱ በፊት ትክክለኛውን ፀፀት እዚሁ ልናስገኝ ይገባል።
⑤ ተውበቱ ወቅቱን የጠበቀ መሆን። ይህም ሞት አፋፍ ላይ ከመድረሱ በፊት እና ፀሀይ በመጥለቂያዋ ከመውጣቷ በፊት መሆኑ ነው።
⑥ ወንጀሉ የሰው ሐቅ መግፋት ከሆነ ሐቁን ሊመልስ ወይም ይቅርታውን ሊያገኝ ይገባል። ያን ማድረግ ካልቻለ ዱዓእ ሊያደርግለት እንዲሁም ኢስቲግፋርና ኸይር ስራ ሊያበዛ ይገባል።
📌ማንቂያ!!!

#ሙቅ ውሃ "በየቦታው ስለ ማፍሰስ"


👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆


#ሸይኽ ኢብን ባዝ (ረሂመሁላህ) ተጠየቁ ፡
ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ #ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ በመፍራት ነው !

መልስ፡-

"አዎን! 👉 #ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ እንዲነቃ ለማድረግ ነው

" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም #በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ ነበር ።

#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን ያዝከው "አለው
#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ

#የሚቀራው ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን ስላላወቀ ነው" አለው

#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው(እንዲያነቃው)"

#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ (ረሂምሁሏህ) እንዲህ አሉ ፡-

"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ አይደፋም ምክንያቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች!!

ምናልባትም #በጂኖች አለም ወይም #በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።

📌ስለዚህ አንድ ሰው #የሞቀን ውሃ መድፋት ከፈለገ #በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር እስኪሆን ያብርደው ከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ፣ ከፈለገ መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ!
፟፟======================================================
#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች በዚህ ሰበብ ችግር ውስጥ ይገባሉ !
Forwarded from ኑሩተውሂድ የግጥም ቻናል
ሲነኩሽ ያመኛል

የፍቅር ፅንሰ ሀሳብ ካንቺ የመነጨ
የመውደድ እጮኛ ካፈርሽ የታጨ
ዛሬስ እንካ በንካ መሪ ተዘውሮ
ከባዕዱ ፍቅር አይናችን ታውሮ
በራስ ወዳድ ጫንቃ ነገር ተቀምሮ
አለውልሽ ያለው ሀሳቡን ቀይሮ
ሲነኩሽ ያመኛል
ሲቃሽ ይሰማኛል
እንባሽ ያነባኛል
ሲያምሽ ያመኛል
እንኳንስ ነክተውሽ
ሲያዪሽም ያመኛል
በዘር ቆጠራ ና በአጥንቱ ፍልጫ
ወንድም ከወንድሙ ሲታይ በፍጥጫ
ከባማሽ በሽቅብ ሊጥሉሽ ከፅልመት
ካኬልዳማ ምድር ሲያውሉሽ ከፀፀት
የሳቅሽን አጀብ የፈገግታሽ ጣራ
ሲነኩሽ ያመኛል በሀሰት ፈጠራ
ከጉያሽ የወጡ ከፍቅርሽ የጠጡ
ለሆዳቸው መብል ከእውነት የወጡ
ያለምክንያት ሰበብ ታናሹ ሲቀላ
አንቺን ተመክቶ አሳሩን ሲበላ
ሲነኩት ያመኛል ያብራክሽን ፍሬ
ብሎ የቆረጠን ሀገሬ ናት ክብሬ
የኔ ምርጥ ምን ነካሽ
ህትብቴ የተቀበረብሽ
ድሮሽ ወዴት አለ የፍቅርሽ ካባ
ሀገሬ ጨቅይተሽ ምነው ደም ተቀባ
ለጥፋት መራራ ስለሞት ሲተጉ
ሲነኩሽ ያመኛል ጎንሽን ሲወጉ
ፅዋሽ ለኔ ይሁን መራራሽን ይስጠኝ
ያላንቺ ከመኖር መሬቷም ትዋጠኝ
ሀገር ና እናት ይመሰላል ካሉ
እናትስ ያላገር የት ይሆን ውሉ

ኑርአህመድ
Forwarded from ኑሩተውሂድ የግጥም ቻናል
በሠው ሚዛን ሞልቶ ባንተ እንዲህ መጉደል
ውበቴ ያልታየህ ለት መወርወር አማረኝ ከረጅሙ ገደል
ቆንጆ ነሽ ይለኛል ሚመጣ
ሚሄደው
እና የኔ ፍቅር ይህ አብሪ ውበቴ ባንተ ቀመር ልኩ ምንድነው የጎደለው
እንቁ በሚመስሉ እኒ ውብ አይኖችህ
የኔን ውበት እንዳታይ ምንድነው የጋረደህ
እስቲ መልስልኝ አንተ የኔ ህመም
ከኔ ውበት መሀል የሚስብህ የለም
አይን አይኔን እያየህ ንገረኝ የኔ አለም
ደርሶ ካልመጠነህ ይህ አብሪ ውበቴ
ከአፍህ አውጣና በለኝ አይደለሽም ልኬ
ልቤም ከቶ የብቃው ላንተ ማጎብደዱ
ሳይሻል አይቀርም
አንተን ውስጥ ቀብሮ ከሌላ መልመዱ
ኑርአህመድ

"SHARE"
◼️ትዝብት‼️


ብዙ ጊዜ ሶላት በምንሰግድበትና ጌታችን ፊት በምንቀርብበት ጊዜ የተቦጫጨቀ፣ ያረጀና የተቀደደ ወይም የመኝታ ወይም የስራ ልብስ ለብሰን እንቀርባለን። ወደ ውጭ ስንወጣ ወይም ሰዎች ፊት ስንቀርብ ግን ያማረ ልብስ ለብሰን፣ ፕሮቶኮላችን ጠብቀን፣ ተውበንና ተስተካክለን ነው።

↪️ መሆን የነበረበት ግን ከምንም በላይ ወደ ጌታችን ስንቀርብ እጅግ ባማረና በተዋበ ሁኔታ ነበር። ምክንያቱም (إن الله جميل يحب الجمال)

↪️ ይህ ማለት ግን ከላይ በተወሱ አይነት ልብሶች መስገድ አይቻልም ማለት አይደለም። ጦሀራ እስከሆነና አውራችን እስከሸፈነ ድረስ በየትኛውም ልብስ ልንሰግድ እንችላለን። ነገር ግን ከምንም በላይ በተዋበና ባማረ ሁኔታ ልንቀርብ የሚገባን ሶላት ላይ ነው።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በፍጡር መማል
~~~~
በፍጡር መማል ከሺርክ ነው የሚመደበው። እንደ አካባቢውና ባህሉ በተለያዩ ፍጡሮች የሚምሉ ሰዎች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦
1. “አባቴን”፣ “እናቴ ትሙት” እያለ የሚምሉ አሉ። ነብዩ ﷺ ግን {አዋጅ! አላህ፡ በአባቶቻችሁ እንዳትምሉ ይከለክላችኋል። የሚምል በአላህ ይማል። ያለበለዚያ ዝም ይበል} ይላሉ። [ቡኻሪ፡ 6108፣ ሙስሊም፡ 4346]
2. “ሸሆቹን”፣ “ሸህ እከሌን”፣ “ሐጂ እንትናን” እያለ የሚምል አለ። ነብዩ ﷺ ግን በሸይኽ ቀርቶ {አንዳችሁ በመሲሑ (በዒሳ) ቢምል አደጋ ላይ ወድቋል። መሲሕ ግን ከአባቶቻችሁ የበለጠ ነው} ይላሉ። [አልሙሰነፍ፡ 12278]
3. “እንዲህ ካደረግኩኝ እኔ ክርስቲያን ነኝ!” እያለ የሚምል አለ። ነብያችን ﷺ ግን {ከኢስላም ውጭ ባለ ሃይማኖት መሀላ የማለ (ለምሳሌ 'ይህን ካደረግኩ እኔ ክርስቲያን ነኝ!' ያለ) እንዳለው ሆኗል (ከኢስላም ወጥቷል)!} ይላሉ። [ቡኻሪ፡ 1363፣ ሙስሊም፡ 315]
4. በከዕባ የሚምሉም አሉ። ነብያችን ﷺ ግን ከዚህ ተግባር ከልክለዋል። [ሶሒሑ ነሳኢይ፡ 3782]
5. “ነቢን” የሚሉ፣ በዶሪሕ (በመቃብር) የሚምሉም ብዙ ናቸው። ውዱ ነብይ ﷺ ግን {በአባቶቻችሁ፤ በእናቶቻችሁና ያለአግባብ ሰዎች ለአላህ ብጤዎች ወይም አቻዎች አድርገው በሚይዟቸው አትማሉ። በአላህ እንጂ አትማሉ። እውነተኞች ሆናችሁ እንጂ አትማሉ} ይላሉ። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7249]
6. “የልጅነቴ አበባ ይርገፍ”፣ “ከፊትህ ይነጥለኝ”፣ “የናቴን አጥንት”፣ “የናቴን ቀን ይስጠኝ” እያሉ የሚምሉ ሞልተዋል። ድንጋይ በእጁ በመምታት፣ ጠመንጃ በመራመድ፣ ቆቲ (የአበጋር ብትር) በመራመድ የሚምልም አለ። ታማኙ ነብይ ﷺ ግን {ከአላህ ሌላ ባለ ነገር የሚማል መሀላ ሁሉ ሺርክ ነው} ይላሉ። [አሶሒሐህ፡ 2042] በሌላ ሐዲሣቸውም {ከአላህ ሌላ ባለ የማለ በርግጥም ክዷል ወይም አጋርቷል} ይላሉ። [ኢርዋእ፡ 2561]

እዚህም እዚያም እንደዋዛ የምንሰማቸው ወጣ ያሉ መሃላዎች አደጋቸው ምን ያክል የከፋ እንደሆነ ተመልከቱ። ነገሩ ምን ያክል ከባድ እንደሆነ ከሶሐቦች ንግግር መረዳት እንችላለን። ዐብዱላህ ብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ “እውነት ተናግሬ ከአላህ ሌላ ባለ ከምምል ውሸት ተናግሬ በአላህ ብምል እመርጣለሁ” ይላሉ። [ኢርዋእ፡ 2562] ኢብኑ ዐባስም እንዲሁ “አንድ ጊዜ ከአላህ ሌላ ባለ ምዬ እውነት ከምናገር መቶ ጊዜ በአላህ እየማልኩ ብወነጅል እመርጣለሁ” ይላሉ። [ሸርሑ ሙስሊም፣ነወዊይ፡ 11/105] ሱብሓነላህ! ሺርክ ምን ያክል አደገኛ ጥፋት ቢሆን ነው እንዲህ አይነት አስፈሪ ነገር የሚናገሩት?!
♦️ሱፍያነ ሰውሪይ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላአሉ:-

"ላኢላሀ ኢለላህ ከሚለው ቃል የበለጠ የሰይጣንን ወገበ የሚቆርጥ የለም"

[ሲየር አእላሚ ኑበላእ (7/260)]
♦️ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይምያህ (ረሂመሁላሁ)

"ለሸሪአ ተፃራሪ የሆነን ሸይኽ የወደደ ከሱጋር ይሆናል ሸይኹ እሳት ቢገባም ከሱጋር (አብሮ ይገባል)"

[መጅሙኡል ፈታዋ (315)]
↪️የረመዳን ወር በመቃረቡ ምክንያት ምን ትመክራላችሁ⁉️

🎙ሸይኽ ዶ/ር ሷሊሕ ኢብኑ ፈዉዛን አል ፈዉዛን ሐፊዘሁሏሁ


♦️አንድ ሙሰሊም አላህ ለረመዳን ወር እንዳያደርሰዉ እና አድርሶትም ፆሙ ላይ ሰግደቱ ላይ እና ሌሎች አምልኮዎች ላይ አላህ እንዲያግዘዉ አላህን መለመን አለበት።

🔺ምክንያቱም ይህ ወር በአንድ ሙሰሊም ህይወት ዕድል ነዉ።ረሱል /እንዲህ አሉ:-ረመዳንን አምኖ እና ምንዳዉን ከአሏህ ከጅሎ የፆመ ያለፈዉ ወንጀሉ ይማርለታል።

♦️ረመዳንን አምኖ እና ምንዳዉን ከአላህ ከጅሎ የሰገደ ያለፈዉ ወንጀሉ ይማርለታል።

🔻ሰለዚህ ይህ ወር ላይመለሰ የሚችል ዕድል ነዉ።

♦️ሙሰሊም የሆነ ሰዉ ረመዳን ሲመጣ ይደሰታል፣ተሰፋም ያደርጋል በደሰታ ነዉ የሚቀበለዉ፣እድሉን
በደንብ በአላህ ትዕዛዝ ላይ ነዉ
ሚያሳልፈዉ።

🔺ሌቱን በመቆም፣ቀኑን በመፃም ቁርዓን በመቅራት እና አላህን በማሰታወሰ ነዉ የሚያሳልፈዉ።
ትልቅ ዕድል ነዉ።

♦️ነገር ግን አንዳንዶቹ ግን ሙሰሊሞችን ለማዘናጋት ረመዳን ሲደርሰ አዘናጊ ፕሮግራሞችን
ፊልሞችን፣ዝባዝንኬዎችን፣ዉድድሮችን የሚያዘጋጁ አሉ።

🔻እነዚህ የሸይጣን ወታደሮች ናቸዉ። ሸይጣን ነዉ ለዚህ ተግባር ያዘጋጃቸዉ።

♦️አንድ ሙሰሊም የሆነ ሰዉ ደግሞ ከነዚህ ሰዎች እና ከተግባሮቻቸዉ መጠንቀቅ አለበት።

🔺ረመዳን የፈንጥዝያ፣የጨዋታ የፊልም፣የዉድድር ወር አይደለም።🖊

↷ ⇣🌹⇣↷
📌ማንቂያ!!!

#ሙቅ ውሃ "በየቦታው ስለ ማፍሰስ"


👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆


#ሸይኽ ኢብን ባዝ (ረሂመሁላህ) ተጠየቁ ፡
ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ #ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ በመፍራት ነው !

መልስ፡-

"አዎን! 👉 #ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ እንዲነቃ ለማድረግ ነው

" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም #በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ ነበር ።

#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን ያዝከው "አለው
#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ

#የሚቀራው ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን ስላላወቀ ነው" አለው

#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው(እንዲያነቃው)"

#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ (ረሂምሁሏህ) እንዲህ አሉ ፡-

"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ አይደፋም ምክንያቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች!!

ምናልባትም #በጂኖች አለም ወይም #በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።

📌ስለዚህ አንድ ሰው #የሞቀን ውሃ መድፋት ከፈለገ #በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር እስኪሆን ያብርደው ከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ፣ ከፈለገ መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ!
፟፟======================================================
#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች በዚህ ሰበብ ችግር ውስጥ ይገባሉ !
ውሸትን የደዕዋ መሳሪያ ከማድረግ መጠንቀቅ
~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~
ወንድሜ ሆይ! ውሸትን ተጠንቀቅ! ሙብተዲዕ ነው ብለህ በምታምነው ሰው ላይ እንኳ ፈፅሞ አትዋሽ። ደዕዋ ላይ የተሰማራህ ስትሆን ደግሞ ይበልጥ ጥንቃቄ ይኑርህ። የዳዒያህ ውሸታም አደጋው ከሌሎች ውሸታሞች የከፋ ነው።
1- ውሸት ልፋቱን ከንቱ ያደርጋል። ለደዕዋ እየለፋ ዞሮ በየመሀሉ ሆነ ብሎ ውሸትን የሚሰነቅር ከሆነ እየፈጩ ጥሬ ነው የሚሆው።
2- ውሸት መቋጫ የሌለው ድርብርብ ወንጀል ላይ ይጥላል። በተለይ ውሸቱ በደዕዋው ላይ የሚንፀባረቅ ከሆነ (ለምሳሌ፦ ሰዎችን ዋሽቶ የሚወነጅል ቢሆን) ያ ውሸቱ ባሳደረው ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ ይሆናል። በሱ ውሸት የተነሳ ደዕዋ ቢደናቀፍ፣ የሰዎች ስም ቢጎድፍ፣ ሰዎች ለኢስላም ወይም ለደዕዋው ያላቸው እይታ ቢበላሽ፣ ሰዎች ከኸይር ቢርቁ፣ በቀጥታ በራሱ ውሸችም ይሁን በሱ የውሸት ውንጀላ በተሸወዱ ሰዎችም ይሁን በየትኛውም መልኩ ሌሎች ላይ ጉዳት ቢደርስ የውሸቱ ጠንሳሽ ላይ ድርብርብ ወንጀል አለበት።
3- የውሸት ፀያፍነት ሰዎች ዘንድ ቀልሎ እንዲታይ ያደርጋል። ሸይኽ ወይም ኡስታዝ እከሌ እንዲህ የሚዋሸው ጉዳዩ ያን ያህል ከባድ ባይሆን ነው የሚል ሸፋፋ ሂሳብ የሚሰራ ሊያጋጥም ይችላል።
4- ውሸታም ሌሎች የዳዕዋ ሰዎችን ያስንቃል። የጥፋት አንጃዎች ዘንድ መሳለቂያ ያደርጋል። የዑለማእ፣ የዱዓት መናቅ ደግሞ ትምህርታቸው ተቀባይነት እንዲያጣ ያደርጋል።
5- ውሸታም ለሌሎች ክፉ ምሳሌ ይሆናል። አስተማሪው ሲዋሽ የተመለከተ ሰው ነፍሲያ በጎተጎተው ቁጥር ያለምንም ጥንቃቄ ሊዋሽ ይችላል። ውሸታም አስተማሪ ውሸታም ተማሪዎችን ያፈራል። ይሄ ደግሞ አጠቃላይ ደዕዋው ላይ ከባድ ጉዳት ነው የሚያደርሰው። ምክንያቱም የተቀየመውን ሁሉ በረድና ተሕዚር ስም ዋሽቶ ለማጠልሸች የማይመለስ መንጋ ይተካልና።
ወንድሜ ሆይ! አስተውል! ተውሒድ በሺርክ፣ ሱና በቢድዐ፣ እውነት በሀሰት አይታገዝም። ዲንን ለማስተማር ብለህ አታዋሽ። ዲንህ የውሸትን እርዳታ የሚፈልግ አይደለምና። አጥፊን ለማስጠንቀቅ ብለህ አትዋሽ። ሳትዋሽ ከአጥፊ ማስጠንቀቅ ካልቻልክ ከምታለማው የምታጠፋው ይበዛልና ይቅርብህ። አትሸወድ! የበደለኛን በደል በሌላ በደል አስቆማለሁ ማለት አጥፎቶ መጥፋት ነው። ተያይዞ ገደል! የትም ቦታ ቢሆን ፍትህ መጠበቅ አለበት። አላህ እንዳስፈላጊነቱ ከሀ*ዲዎችን ከፍ ስል በመሳሪያ ዝቅ ሲል በደዕዋ እንድንዋጋቸው አዞናል። ከመሆኑም ጋር ፍትህ እንዳናዛባ አሳስቦናል። ይሄውና አደራው፦
(یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ كُونُوا۟ قَوَّ ٰ⁠مِینَ لِلَّهِ شُهَدَاۤءَ بِٱلۡقِسۡطِۖ وَلَا یَجۡرِمَنَّكُمۡ شَنَـَٔانُ قَوۡمٍ عَلَىٰۤ أَلَّا تَعۡدِلُوا۟ۚ ٱعۡدِلُوا۟ هُوَ أَقۡرَبُ لِلتَّقۡوَىٰۖ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَۚ إِنَّ ٱللَّهَ خَبِیرُۢ بِمَا تَعۡمَلُونَ)
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ለአላህ ቀጥተኞች በትክክል መስካሪዎች ሁኑ፡፡ ህዝቦችንም መጥላት ባለማስተካከል ላይ አይገፋፋችሁ፡፡ አስተካክሉ፡፡ እርሱ (ማስተካከል) ለአላህ ፍራቻ በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡" [አልማኢዳህ፡ 8]
እወቅ! ውሸት ተራ መስሊሞችም ላይ ቢሆን ፀያፍ ከመሆኑ ጋር ነገር ግን የሙስሊም መሪዎችና ዑለማዎች ላይ ሲሆን ክብደቱ ይጨምራል። ምክንያቱም በተራ ሙስሊሞች ላይ ከመዋሸት የከፋ ውጤት ያስከትላልና። ውሸቱ በአላህና በነብዩ ﷺ ላይ ሲሆን ደግሞ የበለጠ አደገኛ ይሆናል። የአንድን ሙስሊም ክብር የሚያጠለሽ ውሸት ተሻጋሪ ጉዳት ከሌለው ውሸት የከፋ ነው። በህዝብ ላይ፣ በደዕዋ ላይ ጉዳት የሚያስከትል ውሸት ደግሞ በግለሰብ ላይ ጉዳት ከሚያደርሰው ውሸት የከፋ ነው። ስለዚህ በጣም መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
እና እልሃለሁ! ለሱና እከላከላለሁ ብለህ አትዋሽ! ቢድዐን እዋጋለሁ ብለህ አትዋሽ። ያለበለዚያ ይበልጥ ቆሻሻ ጥፋት ውስጥ እየተነከርክ ነው። ሸይኽ ረቢዕ - ሐፊዘሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
الكذب أخبث من البدع يا إخوان والكذَّاب أخبث عند أهل السنة من المبتدع المبتدع يروى عنه, رَوَوْا عن القدرية رَوَوْا عن المرجئة ورَوَوْا عن غيرهم من أصناف أهل البدع ما لم تكن بدعة كفرية ما لم يكن كذابا. لو كان ينتمي إلى أهل السنة كذَّاب فهو عندهم أحط من أهل البدع .
ومن هنا عقد ابن عدي-رحمه الله- في كتابه "الكامل" حوالي تسعة وعشرين باباً للكذَّابين([1]) وبابًا واحداً لأهل البدع .
وقَبِل أهل السنة رواية أهل البدع الصادقين غير الدعاة .
"ውሸት ከቢድዐ ይበልጥ ቆሻሻ ነው፣ ወንድሞች። ውሸታም የሱና ሰዎች ዘንድ ከሙብተዲዕ የከፋ ቆሻሻ ነው። ሙብተዲዕ ከሱ ይዘገባል። (የሐዲሥ ምሁራን) ከቀደሪያ ዘግበዋል። ከሙርጂአ ዘግበዋል። ከሌሎች የቢድዐ አራማጅ አይነቶችም እንዲሁ። ይህም ቢድዐው ክህደት የሚደርስ እስካልሆነና ዋሾ እስካልሆነ ድረስ ነው። ይሁን እንጂ አንድ ውሸታም እራሱን ወደ አህለ ሱና የሚያስጠጋ ቢሆን እንኳ እሱ እነሱ ዘንድ ከቢድዐ ሰዎች በታች ናቸው። ለዚህም ነው ኢብኑ ዐዲይ - ረሒመሁላህ - አልካሚል በተሰኘው ኪታባቸው ውስጥ ሙሸታሞችን በተመለከተ ሃያ ዘጠኝ ርእሶችን ሲሰጡ፣ የቢድዐ ሰዎችን በተመለከተ ግን አንድ ርዕስ ብቻ መስጠታቸው።"

ልብ በሉ! ውሸትና ውሸታሞች ፀያፍ የሚሆኑበትን ገፅ አጉልተው ለማሳየት እንጂ ይህን ማለታቸው እንዳጠቃላይ ቢድዐውን እንደ ኢስላም መቃረቢያ አድርጎ የሚቆጥረው ሙብተዲዕ የከፋ ወንጀለኛ መሆኑ የሚያከራክር አይደለም።
ፅሁፌን የምቋጨው በተከታዩ የነብዩ ﷺ ሐዲሥ ነው፦
"وإيّاكم والكذِبَ، فإنّ الكَذِبَ يَهْدِي إلَى الفُجُورِ، وإِنّ الفُجُورَ يَهْدِي إِلَى النّارِ وَمَا يزَالُ العبْدُ يَكْذِبُ وَيَتَحَرّى الكَذِبَ حَتّى يُكْتَبَ عِنْدَ الله كَذّابا".
"ውሸትን አደራችሁን (ተጠንቀቁ)። ውሸት ወደ አመፅ ይመራልና። አመፅ ደግሞ ወደ እሳት ይመራል። አንድ ሰው ከመዋሸትና ውሸት ላይ ከማተኮር አይወገድም አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ እስከሚመዘገብ ድረስ!" [ቡኻሪና ሙስሊም]
==
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor

ወደ ዋናው ፔጅ ገብቶ ለማንበብ
ከ4 ወር በፊት አካባቢ የተፖሰተ

https://t.me/IbnuMunewor/2457
Audio
ስለ ረመዷን ወሳኝ ትምህርት
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭

የትምህርቱ ርዕስ፦➴➴➴
አህዋሉሰለፍ ፊረመዷን (የሰለፎች ሁኔታ በተከበረው የረመዳን ወር ውስጥ)

📚ክፍል አንድ

የትምህርቱ አቅራቢ፦➴➴➴
🎙ኡስታዝ ሙሐመድ አህመድ ሙነወር [ኢብኑ ሙነወር] አላህ ይጠብቀው
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭

በረመዷን ዙሪያ የሰለፎቻችንን ሁኔታ መዳሰስ ለምን አስፈለገ‼️
ያስፈለገበት ምክንያትማ

❶ኛ .ለእያንዳንዱ ስራችን ሞደላችን (ምሳሌያችን) ነብዩ ሙሐመድ ﷺ ናቸው። የሳቸውን ተግባራት ደግሞ በስነ_ስርዓት ወደኛ ያስተላለፉልን ሰለፎቻችን በመሆናቸው የነሱን አህዋል (ሁኔታ) ማየቱ ተገቢ ነው።
አላህ እንዲህ ይላል፦
لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا
ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ፡፡
(ሱረቱ አል- አሕዛብ - 21)

❷ኛ .ሌላኛው ያስፈለገበት ምክንያት እኛ ልክ ሰለፎቻችን እንዳመኑበት አይነት ካመንን እንደነሱ አውቀን ከተገበርን ቅናቻውን መንገድ እንመራለንና
አላህ እንዲህ ብሏል፦
فَإِنْ آمَنُوا بِمِثْلِ مَا آمَنتُم بِهِ فَقَدِ اهْتَدَوا ۖ وَّإِن تَوَلَّوْا فَإِنَّمَا هُمْ فِي شِقَاقٍ ۖ
በርሱ ባመናችሁበት ብጤ ቢያምኑ በእርግጥ ተመሩ፡፡ ቢዞሩም እነርሱ በጭቅጭቅ ውስጥ ብቻ ናቸው፡፡
( አል-በቀራህ - 137)

አላህ በሰለፎቻችን አይነት ተግባር ሰርተን የምንጠቀምበት ችሎት ይለግሰን !!
አጠቃላይ ወሳኝ ምክር
ወንድም ሳዳት ከማል
የኛን ተውት የነብያቶቹን ግን አንተውም።
#ሳዳት_ሀፊዞሁሏህ__

➻የመጀመሪያ የሳዳት ከማል ሙሐደራ 01
➻በጉራጌ ዞን በአክሊል ወረዳ በዘነበነር ቀበሌ
➻ወደ ዋናው የሳዳት ከማል ፔጅ ለመቀላቀል

https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
4/7/2014