La tehzen
94 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
🍁ረመዳን ሸህሩን ሙባረክ🍁
====================
★ ረመዳንን ከሌሎች ወሮች የሚለዮ 10 ነገሮች★


አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ሁላችንም እንደምናውቀው ውዱ የበረካ ወር የሆነው ረመዳን ለተጠቃሚዎች በበረካው ሊያምበሸብሻቸው አንድ ሁለት እያለነው ረመዳን በአመት ውስጥ ካሉ 12 ወራቶች አንዱ ነው እንዲሁም ቁርአን ውስጥ ከተጠቀሱት 4 የላቁ ወራትም አንዱ ነው። ረመዳን ከሌሎች ወሮች ለየት የሚያደርጉት ብዙ ነገሮች አሉ ከነዛም ዉስጥ
① ፆም መደንገጉ ፦ የረመዳንን ወር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች መሀከል አንዱና ዋነኛው ወሩን እንድንፆም መታዘዛችን ነው
ፆም አላህ ዘንድ በጣም ከፍተኛ ቦታ ካላቸው ኢባዳዎች መሀከል አንዱ ነው ፆም የሱና እና ዋጂብ የሚባሉ ክፍሎችም አሉት የሱና ፆም የሚባለው መፆም የተከለከለ ባቸው ጊዜያት ሲቀሩ በማንኛውም ቀን መፆም የሚቻል ሲሆን ዋጂብ ወይም ፈርድ(ግዴታ) የሚባለው ፆም ደግሞ አላህ በባሮቹ ላይ ግዴታ ያደረገው የፆም አይነት ነው አላህ ፆምን በኛላይ ግዴታ ማድረጉን ሲናገር እንዲ ይላል
(يا ايها الذن امن كتب عليكم اصيم كما كتب اللذين من قبلكم لعلكم تتقون)
(እናንተ ያመናችሁ ሆይ ፆም በናንተ ላይ ግዴታ ተደርጓል ልክ ከናንተ በፊት በነበሩት ግዴታ እንደተደረገው) ከዚ የቁርዓን አያ የምንማረው የመጀመሪያው ከኛበፊት በነበሩት ህዝቦች ላይ መደንገጉን እና በኛም ላይ መደንገጉን ነው።
② የቁርአን መውረድ፦ ቁርአን ለሰውልጆች መመሪያና ማስተማሪያ ነው እንዲሁም ከዚበፊት የሆኑ ፣አሁን እየሆኑያሉና ወደፊት የሚሆኑ ለኛ አስተማሪና አስጠንቃቂ የሆኑ ነገሮችን የያዘ ነው። የዚህ ዉድ ቁርአን በረመዳን መውረድ ረመዳንን ከሌሎች ወሮች ለየት ከሚያደርጉ ነገሮች መሀከል አንዱ ነው። እና እኛ በዚ በረመዳን ቁርአንን ልንቀራ ይገባናል
ቀደምት ደጋግ ቀደምቶች በረመዳን እስከ 60 ጊዜ ያኸትሙ ነበር።አኛስ?
③ የሰይጣን መታሰር፦ በረመዳን ወርየጀነት በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ አመፀኛ ሰይጣናትም ይታሰራሉ። ነብያችን ሰ,ዐ,ወ እንዲህ ይላوغلقت السماء، ابواب فتحت رمضان إذا دخل إذا رواية وفي الشياطين وسلسلت جهنم،ابواب الجنة ابواب فتحت رمضان جاء

" ረመዳን ሲገባ የሰማይ በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ ሰይጣናትም ይቀፈደዳሉ ።’’ በሌላ ዘገባም” የጀነት በሮች ይከፈታሉ” ብለዋል(ቡኻሪና ሙስሊም)

④ የስራዎች ምንዳ መደራረብ፦ በረመዳን ወር የሐሰናት ወይም የመልካም ስራዎች ምንዳ እጥፍ ድርብ ይሆናል። ነብዩ ሰ,ዐ,ወ ተጠይቀው ከሰደቃዎች ሁሉ በላጩ የቱ ነው ተብለው "በረመዳን የሚሰጥ ነው ብለዋል"
⑤ ከአንድሺ ሌሊቶች በላጭ የሆነችው ለይለትል ቀድር፦ አላህ ከአንድ ሺህ ሌሊቶች ያስበለጣት ሌሊት ናት እንዲሁም የአመቱን ጉዳዩች የሚፅፍባት የተበረከች ሌሊት ናት "ليلة القدر خير من الف شهر"
" ሌሊቶችም በላጭመወሰኛይቱ ሌሊት ከሺህ ናት"

⑥ መላኢኮች በብዛት ወደ መሬት መውረድ፦ አላህ አንዲ ይላል ፦تنزل الملاإكة والروح فيها بإذن ربهم من كل أمر"
"በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ "
⑦ ሱሁር (የሌሊት ምግብ) ፦ ሱሁር ካለፍት ህዝቦች ፆም የኛን የሚለይና ብዙ በረካዎችን የያዘነው ነብዩ ሰ,ዐ,ወ እንዲህ ይላሉ "تسحروا فإن في السحور بركة"
"ሱሁርን ብሉ ሱሁር መብላት
በረካ አለውና "
⑧ የተራዊህ ሰላት፦በረመዳን ብቻ በጀማአ የሚሰገደው የሱና ሰላት የሆነው ተራዊህ አንዱ ረመዳንን ለየት ከሚያደርጉ ነገሮች መሀከል አንዱ ነው። ከረመዳን ውጭ ይህ ሰላት አይሰገድም ።
⑨ የኡምራ ትሩፋት፦በረመዳን ወር ኡመራ ማድረግ ከነብዩ ሰ,ዐ,ወ ጋር ሀጅ እንደ ማድረግ ነው።"عمرة في رمضان تعدل حجة او قال حجة معي"
"በረመዳን የሚደረግ ኡምራ ከሀጅ ጋር እኩል ነው ወይም ከኔጋር ከሚሰራ ሀጅ እኩል ነው"ብለዋል
¹⁰ ወንጀል ማበሻ፦ረመዳን ወንጀል እንዲታበሱ ከሚያደርጉ ነገሮች መሀል አንዱና መሰረታዊው ነው።
" الصلوات الخمس ولجمعة الى الجمعة ورمضان الى رمضان مكفرات لما بينهن إذا اجتنبت الكبائر"
"ታላላቅ ወንጀሎች ከተራቁ አምስት ወቅት ሰላቶች ከጁምአ እስከ ጁምአ ከረመዳን እስከ ረመዳን በመሀከላቸው ያለውን ወንጀል ያስምራሉ"

አላህ ካለ ከረመዳን ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዩች ላይ ክፍል ሁለት ይቀጥላል
ረመዳንኮ ሊገባ ነዉ፡፡ (ደስ ይላላ)
በሉ አዉፍ በሉኝ
ቂም ይዞ ጾም አይታሰብም፡፡ ጥላቻን አስወግደን በፍቅርና በመtሳሰብ የአጅር መአት የምንሰበስብበት ምርጥ ወር፤ ቀሽት ረመዳን ይሁንልን! ⭐️🌙 ከታች ከተዘረዘሩት ቁጥሮች ውስጥ አንድ ቁጥር በመምረጥ ለረመዷን ፆም ማስያዣ ስጦታ ትሰጠኛለክ ማለት ነው እንቢ ማለት አይቻልም
1💝2💝3💝4💝5💝6💝7💝8💝9💝10💝11💝12💝13💝14💝15💝16💝17💝18💝19💝20💝
The gifts that u are going to give me are
1💝 ቴምር🐵
2💝 Ring💍
3💝 16 gb original flash
4💝 candy🍬🍬
5💝 250 mb
6💝 500 mb
7💝 book📚📚
8💝 quran
9💝 ye 50 birr card
10💝 25 birr card
11💝 neshida🎧
12💝 8gb orginal flash
13💝 መስገጃ
14💝 just say u frind#i love u zizatyyy
15💝 meneፅer
16💝 tishirt
17💝 anchin/anten 😍😘
18💝 ተስቢህ
19💝 lettre💌💌
20💝 chocolate🍫🍫

Dersew kemisomut allh
Yargen 🤲🤲🤲🤲🤲
✦ የጁምአ ቀን ሱናዎች
- ገላን መታጠብ
- ጥሩ ልብስ መልበስ
- ሽቶ መቀባት(ለ ወንዶች ብቻ)
- በግዜ ወደ መስጂድ መሄድ
- በነብዩ -ﷺ-ላይ ሰለዋት ማብዛት
- ሱረቱል ካህፍን መቅራት
- ዱዓ የሚያገኝበትን ሰዐት መጠባበቅ

➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
🇸🇦በተጨማሪ አርፍደው ከመጡ የሰው ትከሻ ላይ እየተረማመዱ ሶፍ ውስጥ ከመግባት መቆጠብ,
🇸🇦ኹጥባን በጥሞና ማዳመጥ,
🇸🇦ሌላ ሰው ቢያወራም ዝምበል አለማለት እና
🇸🇦 ሶላት ካለቀ በኋላ ያመለጣቸውን ሰዎች ሶላት ሳይቆርጡ ረጋ ብሎ መውጣት ያስፈልጋል።

🌙ፏ ያለ ጁምዓ ይሁንልን🌙
በፍፁም ሳያነቡት እንዳያልፉ 😳

ከለሊቱ ስምንት ሰአት አካባቢ የቤቴ በር በሀይል ተንኳኳ።😳 ከእንቅልፌ
ባንኜ ተነሳሁ። በቀስታ ወደ በሩ ተጠጋሁና በሩን ከፈትኩ።
በር ላይ አንድ ወጣት ቆሟል ጓደኛዬ ነው አጎቱ ነበር የሞቱት።😭 ቶሎ መቀበር እንዳለበት
ሀኪም ስለነገራቸው ተያይዘን ወደ ቤታቸው አመራን።🚶‍♂🚶‍♂

ጀናዛውን ማጠብ ጀመርኩ በመሀል ግን አንድ የሚያስደነግጥ ሁኔታ
ተፈጠረ።😱
የሰውነት ከለሩ መቀያየር ጀመረ። ፊቱ ጠቆረ አካሉ ከሰለ።
እንደምንም አጥበን ጨረስን። ወደመቃብር ስፍራም ይዘነው ሄድን።
የተቆፈረው ቀብር ውስጥ ገባሁ። መሬቱን ጠራረኩና አፀዳሁት የለህዱንም
ስፋት ሞከርኩት። ወደ ውስጥ ጀናዛውን አስገባነው። ምድር ሰውነቱን
እንደነካው ከመሬት ስር ትልቅ ትል ወጣና ሰውነቱ ላይ ተለጠፈ።🐉
አስወገድኩት ሆኖም ግን ሌላ ከመጀመርያው የተለቀ እባብ የመሰለ
በደረቱ የሚሳብ አስፈሪ እንሰሳ ሰውነቱ ላይ ተጠመጠመ። ነገሩ
ስላስደነገጠንና ከአቅማችን በላይ ስለሆነ ትተነው ከቀብር ወጣን።
በስነስርዓት ሳይቀበር በላዩ ላይ አፈር ደፋንበት።

በህይወት ዘመኑ ምን አይነት ሰው እንደነበር ጠየቅን። ሰላትን ወቅቱን
ጠብቆ እንደማይሰግድ ከአንድ ዘመዱ ተነገረኝ ።
ሙሰልሰል ስትመለከቱና ፌስቡክ ላይ ተጥዳችሁ ሰላት የሚያመልጣችሁ፣
ኳስ እየተጫወታችሁ ሰላት የሚያልፋችሁ ሰዎች ሆይ !!! ስሙ
ይህን አይነት አሟሟት ነው የምትሹትን? !
በአላህ እምላለሁ ባጠፋሀቸው ጊዜያት የምትቆጩበት ቀን ይመጣል።😔
ዱንያን ለቀህ ከመውጣትህ በፊት ለኸይር ነገር ተቻኮል።

#ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድ አዳርሱ
ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡ ዐዋቂና ብልህ ሰው ማለት ሥጋዊ ፍላጎቱንና ስሜታዊ ዝንባሌውን ተቆጣጥሮ ከሞት በኋላ ላለው ሕይወቱ የሰራ ነው። ሞኝ ተላላና ደካማ ሰው ማለት ደግሞ ራሱን (ወደ ተከለከሉና አጥፊ ወደሆኑ እኩይ ተግባራት በምትመራው ነፍሱ) ስሜታዊ ዝንባሌ ቁጥጥር ሥር አውሎ የዝንባሌው ተከታይ በመሆን (ምህረትና ጸጋውን ያላንዳች ጥረት) በባዶ ተምኔት ከአላህ የሚጠብቅ ሰው ነው። /ትርሚዚ/
የነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ሀዲሶች

sher
ሶላት ከሰገዱ ቡኋላ መስገጃዎ ላይ መቆየት ምን ያህል አጅር እንደሚያስገኝ ያውቃሉ?
✿┈┈┈┈•✶✾✶•┈┈┈┈┈✿
👉👉 የአላህ መልክተኛ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ "ከእናንተ መካከል አንዳቹ ሶላት የሰገደበት መስገጃው ላይ እስካለ እና ውዱእ እስካላጠፋ ድረስ መላኢካዎች በርሱ ላይ ሰለዋት ያወርዱለታል። "አላህ ሆይ! ወንጀሉን ማረው፣ አላህ ሆይ! እዘንለት።" ይላሉ።"
(ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)

👉 ኢብኑ በጣል(ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "እጅግ ብዙ ወንጀል ያለበት ያለ ብዙ ልፋት ወንጀሉን አላህ እንዲያራግፍለት የሚፈልግ ሰው ካለ፦ መላኢካዎች እርሱ ላይ የሚያደርጉት ዱዓ እና ኢስቲግፋር ይበዛለት ዘንድ ሶላት ከሰገደ ቡኋላ መስገጃው ላይ በመፅናት እድሉን ይጠቀሙ።
* ዕለተ ጁሙዓ - ሸዕባን 1443 ዓ.ሂ ላይ ደርሰናል፡፡
* ለታላቁና ተወዳጁ ረመዷን 30 ወይም 29 ቀን ቀረው፡፡

* ሸዕባን - ከረመዷን ቀጥሎ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ.) በብዛት የፆሙት ወር ነበር፡፡

* ወሩ የዓመት ሥራዎቻችን አላህ ዘንድ የሚቀርቡበት ወር ነው፡፡

* ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ.)"ለምን እንደሚፆሙት ተጠይቀው በረመዷን እና በረጀብ መካከል ስለሚገኝ ብዙዎች ይዘናጉበታል፣ ፆመኛ ሆኜ ሥራዬ አላህ ዘንድ ቢቀርብ እወዳለሁ ብለዋል፡፡

* ሸዕባን መፆም ለረመዷን ፆም መዘጋጃና አካልንና መንፈስንም ማለማመድ ነው፡፡

* ሸዕባን ላይ ረመዷን በእጅጉ ይናፍቃል፣ ወሬው ሁሉ ስለ ረመዷን ይሆናል፡፡

* አላህ ሆይ ሸዕባንን ባርክልን ለረመዷን በሰላም አድርሰን፡፡
➧የእውቀት ፍሬው ተግባር ነው
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➛ክፍል ዘጠኝ


አምስተኛው፡ - ሰለፎቹ ባወቁት ለመስራት ተሸቀዳዳሚ ነበሩ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➲ይህን ደረጃ ከሚያብራሩ ነጥቦች መካከል፡ የሰለፎች አስደናቂ ባህሪያቸው ነው፡፡ሰለፎቹ ተግባርን በቋሚነት ለመፈጸም ይሽቀዳደሙ ነበር፡፡ ከረሡል صلى الله عليه وسلم የሰሙትን ፈጥነው ለመተግባር ይቸኩሉ ነበር፡፡

➭በዚህ ትርጉም ላይ ሰለፎቹ ምን ያክል ባወቁት ለመተግበር ፍላጎቱ እንደነበራቸው ብርቱ ትኩረት እንደሚሰጡ የሚገልጹ በርካታ መረጃዎች መጠዋል፡፡ከዚህ መካከል ቡኻሪና ሙስሊም ላይ ተዘግቦ የሚገኘው ሐዲስ ነው፡፡ የረሡል صلى الله عليه وسلم ልጅ ፋጢማ ረድየላህ አንሃ አገልጋይ ፈልጋ ለአላህ መልእከተኛ ጥያቄ አቀረበች፡፡

▪️የአላህ መልክተኛም صلى الله عليه وسلم የሚከተለውን ምላሽ ሰጧት፡- “ለአንች ከአገልጋይ የተሻለውን ልጠቁምሽ?” አሏት፡፡ (ለመተኛት) ወደፍራሽ በተጠጋሽ ጊዜ ሰላሳ ሶስት ጊዜ ሱብሃን አሏህ ፣ አልሀምዱ ሊላህ ሰላሳ ሶስት ጊዜ ፤ አሏሁ አክበር ሰላሳ ሶስት ጊዜ በይ” አሏት፡፡ ባለቤቷ ዓልይ ረድየላህ አንሁ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

"فما تركتها منذ سمعتها من رسول الله صلى الله عليه وسلم"

“ከረሡል ከሰማሁበት ጊዜ ጀምሮ ትቸው አላውቅም” ከመካከላቸው አንዱ “አስቸጋሪ ሌሊት ላይ እንኳ ቢሆን? - ማለትም ሰው በሚዘነጋበት ሰኣት ላይ እንኳ ቢሆን? - ይህን ዚክር ረስቶት አያውቅም?” ፤ “በሲፊን ሌሊት እንኳ ቢሆን?!” - ይህ ሌሊት የታወቀ ጦርነት ነው - የሚል ጥያቄ ተጠየቀ፡፡ “በሲፊን ሌሊት እንኳ ቢሆን” በማለት ምላሽ ሰጧል፡፡ ቡኻሪ፡ 5362 ሙስሊም፡2727

➧ዓንበሳህ ብን አቢ ሱፍያን -ረሂመሁሏህ- በሞተበት በሽታ ላይ ሆኖ ኡሙ ሀቢባ ረድየላህ አንሃ ከረሡል صلى الله عليه وسلم ሰማሁ ብላ የሚከተለውን ሐዲስ ነገረችኝ ብሎ ለእኔ አስተላልፎልኛል ይላል ዓምር ብን አውስ፡፡

"من صلى اثنتيني عشرة ركعة في يوم وليلة بني له بهن بيت في الجنة"

▪️“አስራ ሁለት ረከዓዎችን በሌሊትና በቀን የሰገደ ሰው በእነርሱ አማካኝነት በጀነት ቤት ይገነባለታል፡፡” ኡሙ ሀቢባ ረድየላህ አንሃ የሚከተለውን ተናግራለች ፡-
"فما تركتهن منذ سمعتهن من رسول الله"

➧“ከረሡል صلى الله عليه وسلم ከሰማሁ ጀምሬ (እነዚህን አስራ ሁለት ረከዓዎች) ትቻቸው አላውቅም” አንበሳህ ደግሞ በተመሳሳይ “ከኡሙ ሀቢባ ከሰማሁ ጀምሮ ትቻቸው አላውቅም”ይላል፡፡ ዓምር ብን አውስ ደግሞ “ከአንበሳህ ከሰማሁበት ጊዜ ጀምሮ ትቻቸው አላውቅም” ይላል፡፡ ኑዕማን ብን ሳሊም ደግሞ “ከዓምር ብን አውስ ከሰማሁበት ጊዜ ጀምሮ ትቻቸው አላውቅም” ይላል፡፡ ሙስሊም፡728

➠ይህ ፍጥነትን እና በቋሚነት መፈጸምን ያጣመረ ታላቅ ወኔ ነው፡፡ ለስራ መፍጠን ፣ቋሚ ደምበኛ ለመሆን መሽቀዳደም፡፡

▪️ቡኻሪ በዘገቡት ሐዲስ አቡሁረይራ ረዲየላህ አንሁ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

"أوصاني خليلي بثلاث لا أدعهن حتى أموت: صوم ثلاث أيام من كل شهر ، وصالة الضحى ، ونوم على وتر"

➲“ወዳጀ እስከምሞት ድረስ የማልተዋቸው በሆኑ ሶስት ነገሮች አደራ አለኝ፡፡ ከየወሩ ሶስትቀናቶችን (እንድጾም) ፣ የዱሃ ሶላት (እንድሰግድ) ፤ ዊትር ሰግጀ እንድተኛ” ቡኻሪ፡1178



ኢንሻአላህ ይቀጥላል



➭ጥሩ ፀሀፊ ባትሆን ጥሩ አንባቢ ሁን ትጠቀማለህ
➲ከተውሂድ አርማዎች
➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➧ክፍል ሁለት
➻➻➻➻➻➻

የተውሒድ መለያዎችና ትሩፋቶች


➧ተውሒድ፡ ከፍተኛ ደረጃና ቦታ የሚሰጠው መሆኑን የሚጠቁሙ በርካታ መለያ ባህሪያትና ትሩፋቶች እንዳሉት እወቅ፡፡ ከእነርሱ መካከል አስሩን እንደሚከተለው እጠቁምሃለሁ፡፡

➲አንደኛ፡- የሚከተለው ቁርኣናዊ አንቀጽ እንደሚጠቁመው እኛ የተፈጠርንበት እና
የተገኘንበት ዋና ዓላማ ለተውሒድና ተውሒድን ለማረጋገጥ ብቻ ነው፡፡


▪️وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ

“ጅንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ (ዓላማ) አልፈጠርኳቸውም፡፡” አዝ ዛሪያት፡56

➧“ኢልላ ሊየዕቡዱን” ፡ የሚለው የቁርኣን ቃል ትርጉም “እኔን (በአምልኮት) ብቸኛ ሊያደርጉኝ” ማለት ነው፡፡ በዚህ ዓለም የተፈጠርንበት ዋና ዓላማ ለቀልድና ለጨዋታ ሳይሆን ለተውሒድ ሲባል ነው፡፡

➭አላህ - ሱብሃነሁ ወተዓላ - ልቅ አድርጎ
ሊተወን ሳይሆን እርሱን በብቸኛነት ልንገዛው ፈጠረን ፤ እርሱን በአምልኮ ብቸኛ ልናደርግ አስገኘን፡፡ የተውሒድ ሁኔታ ላቅ ያለ ለመሆኑ ከማስረጃ በኩል በዚህ ይብቃ፡፡

➲ሁለተኛ፡- ተውሒድ የነብያቶችና የሩሡሎች ጥሪ መሽከርከሪያ ምህዋር ነው፡፡ አላህ የላከው ማንኛውም ነብይ የጥሪው ትኩረትና መቆሚያ መሰረቱ ተውሒድ ነው፡፡ ለዚህም በርካታ ማስረጃዎች አሉ፡፡

▪️አላህ በተከበሩት ቁርኣናዊ አንቀጾች የሚከተለውን ተናግሯል፡

وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَّسُولًا أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ وَاجْتَنِبُوا الطَّاغُوتَ ۖ

➧“በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ “አላህን ተገዙ ፤ ጣዖትንም ራቁ” በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፡፡” አን ነሕል (36)

▪️وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

➧“ከአንተ በፊትም እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ በማለት ወደርሱ የምናወርድለት ቢሆን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡” አል አንቢያእ፡(25)

▪️وَاسْأَلْ مَنْ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رُّسُلِنَا أَجَعَلْنَا مِن دُونِ الرَّحْمَٰنِ آلِهَةً يُعْبَدُونَ

➧“ከመልክተኞቻችንም ካንተ በፊት የላክናቸውን (ተከታዮቻቸውን) ከአልረህማን ሌላ የሚገዟቸው የሆኑን አማልክት አድርገን እንደሆነ ጠይቃቸው፡፡” አዝ ዙኽሩፍ (45)

۞ وَاذْكُرْ أَخَا عَادٍ إِذْ أَنذَرَ قَوْمَهُ بِالْأَحْقَافِ وَقَدْ خَلَتِ النُّذُرُ مِن بَيْنِ يَدَيْهِ وَمِنْ خَلْفِهِ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ

“የዓድንም ወንድም (ሁድን) ሕዝቦቹን በአሕቃፍ ባስጠነቀቀ ጊዜ አውሳላቸው፡፡ በስተፊቱና በስተኋላውም ብዙ አስፈራሪዎች በእርግጥ አልፈዋል፡፡ “ከአላህ በስተቀር አትግገዙ ፣ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁና” በማለት (ባስጠነቀቀ ጊዜ)፡፡ አል አህቃፍ፡21

➲“ኑዙር” ማለት መልክተኞች ማለት ነው፡፡ ከዚህ በፊት የነበሩትም ይሁን ወደኋላ የመጡት መልክተኞች “ከአላህ በቀር አትግገዙ” በሚለው አላማ ላይ አንድ ሆነዋል፡፡

➧ተውሒድ ፡ የነብያቶች እና የሩሡሎች ጥሪ መሰረት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ህዝቦቻቸው ከመልእክተኞች ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያደምጡት ቃል የተውሒድን ቃል ነው፡፡ ወደአላህ ጥሪ ሲያደርጉ አንድ ብለው የሚጀምሩት በተውሒድ ነው፡፡



ኢንሻአላህ ይቀጥላል

🖊🖊🖊Nurahemd

【አንብብ በማንበብ ብዙ እውቀት ይገኛል】📚📚📚📚📚

🍁ረመዳን ሽህሩን ሙባረክ🍁
==================

★ የረመዳን ወር የትኩረት አቅጣጫዎች★

① ልቦናዎች የሚደብቁትን ሁሉ የሚያየውና የሚያውቀው አላህ ሱ,ወ የኢማናችንን ጥንካሬ በዚህ ፆም ሊፈትነን እንደፈለገ በመገንዘብ ከፋተኛ ትኩረት
መስጠት።
② ረመዳንን ስንፆም በኒያ (አስበንና ወስነን) መሆን አለበት ምክንያቱም ማንኛውም ኢባዳ ያለኒያ ስለማይሆን።
③ ቀኑን በሙሉ በመኝታ ከማሳለፍ መቆጠብ ምክንያቱም ረመዳን የኢባዳ ወር ነው ስለሆነም የቻልነውን ያክል በኢባዳ መበርታት አለብን።
④ቁርአንን ጀሌላው ጊዜ በተሻለ መቅራት አለብን ረመዳን የቁርአን ወር ነው ቁርአን የወረደውም በረመዳን ወር ነው።
⑤ከፈጣሪያችን ከአላህ ጋር ተውባ በማድ ረግ (በመፀፀት) ወደሱ ልንመለስና ልናስደስተው ይገባል።

⑥የረመዳን ሌሊቶችን በመይጠቅሙ ነገሮች ከማሳለፍ መቆጠብ ።
⑦ በረመዳን ወር ዱአ ማድረግና ወደ አላህ መተናነስን ማብዛት።
⑧ አምስት ወቅት ሰላቶችን በጀመአ መሰጊድ መስገድ።
⑨ ምግብን ደግሞ የቀኑን ለማካ ካስ የሚበቃ ያክል አብዝቶ አለመብላት።
【¹⁰】 ሙሉ አካላችንን ከአላህ ትእዛዝ መስጠት ወይም መገዛት አለብን።

በተያያዥ ነጥቦች ላይ ክፍል 3 ይቀጥላል ኢንሻ አላህ።

ኑር አህመድ ሙሀመድ
Forwarded from Deleted Account
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሆነ ሰውየ መስጅድ ገባ ሊሰግድ. ከዛ አሰጋጁ. የት ነህ አይተንህ አናቅም አለው ላድሱ ሰውየ አሁን በቅርብ ነው ከዚህ ከገሌ ቤት ቀጥሎ ያለዉን ቤት ገዝቼ ነዉ አለዉ . የገባሁት. አለው. ኢማሙ. ( አሰጋጁ ). ለሰውየው አላህ. ይሁንህ. አለው. ሰውየው ምን ነው ሲለው ከጎንህ ያለው ጎረቤትክ. አላህን አይፈራም አይሰግድም. አደዛዥ እፅ የሚጠቀም ሰካራም ነዉ አለው.
ሰዉየዉ ለምን ቀድማቹሁ አልነገራቹሁኝም አለዉ ይሄ እጣህ ነዉ ያዝ አለዉ ከመስጅድ ወጣ ሲል ሌላኛዉ ሰዉ ጠየቀዉ የእገሌን ቤት ገዝቼ ነዉ ሲለዉ አሏህ ይዘንልህ ጎረቤትህ አስቸጋሪ ነዉ ብሎ ልክ ኢማሙ ያለዉን አለዉ አሱርን ሶላት ከመስጅድ ሰግዶ ሲወጣ ጎረቤቱን ከቤቱ በር ቁጭ ብሎ ይመለከተዋል ልክ እንዳየዉ በፈገግታ አሰላሙአለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱሁ ብሎ ሰላምታ ካቀረበ ቡኋላ ጎረቤቶችህ ይወዱኋል ያወዱሱሀል ብሎ ነገረዉ ከዚያ ላትመለሰኝ አደራ ብሎ ከቤቴ ራት ልጋብዝህ ብሎ ጋበዘዉ ከቤቱ ሲመጣ ማንም የለም እሱ ብቻ ነዉ ከእኔ ዉጭ ሌላ አልጋበዝክም ሲለዉ ይሄ ራት ግብዣ ላንተ ነዉ አንተን ለማክረም ከዚያ ራት ግብዣዉ ካለቀ ቡኋላ ዉድ ስጦታ ሰጠዉ
. . ከዚያ አደዛዥ እፅ የሚጠቀመዉ የማይሰግድ የነበረ ሰዉ ሶላተል ፈጅር በጀመዓ ሰገደ . ኢማሙ ተገረመ. ምን አድርግለት ምን ብለኽው ነው አለው. በመልካም ንግግር ብቻ ነው ያናገርኩት ሌላምን አላዴረኩለትም አለው

እናም. ሰዎችን በሂክማ መጣራት እዳለብን. ነው. የሚያስተምረው. ወላሁ አእለም።
👇👇👇👇
https://t.me/httpsLatahzen
Forwarded from Deleted Account
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጧት ዚክር
➱➱➱➱➱➱

وَاذْكُرِ اسْمَ رَبِّكَ بُكْرَةً وَأَصِيلًا

የጌታህን ስም በጧትና በማታ አውሳ!!

https://t.me/httpsnurutewhide
La tehzen
➲ከተውሂድ አርማዎች ➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➧ክፍል ሁለት ➻➻➻➻➻➻ የተውሒድ መለያዎችና ትሩፋቶች ➧ተውሒድ፡ ከፍተኛ ደረጃና ቦታ የሚሰጠው መሆኑን የሚጠቁሙ በርካታ መለያ ባህሪያትና ትሩፋቶች እንዳሉት እወቅ፡፡ ከእነርሱ መካከል አስሩን እንደሚከተለው እጠቁምሃለሁ፡፡ ➲አንደኛ፡- የሚከተለው ቁርኣናዊ አንቀጽ እንደሚጠቁመው እኛ የተፈጠርንበት እና የተገኘንበት ዋና…
➲ከተውሂድ አርማዎች
➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➭ክፍል ሶስት
➻➻➻➻➻➻

➲የተውሒድ መለያዎችና ትሩፋቶች


➧ተውሂድ ፦ የነብያቶች እና የሩሡሎች ጥሪ መሰረት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ህዝቦቻቸው ከመልእክተኞች ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያደምጡት ቃል የተውሒድን ቃል ነው፡፡ ወደአላህ ጥሪ ሲያደርጉ አንድ ብለው የሚጀምሩት በተውሒድ ነው፡፡ ምክንያቱም የኢስላም እምነት በእርሱ ላይ ነው የሚመሰረተው፡፡ የእምነቱ ምሳሌ ልክ እንደዛፍ ነው፡፡

➭ዛፍ መሰረትና ቅርንጫፎች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ በመሰረቱ ላይ ካልሆነ በቀር ዛፉ ቀጥ ብሎ ሊቆም አይችልም፡፡ ዲኑም በመሰረቱ ላይ ካልሆነ ቀጥ ብሎ ሊቆም አይችልም፡፡ የዲን መሰረቱ ደግሞ ተውሒድ ነው፡፡

➲አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፦

▪️ألَمْ تَرَ كَيْفَ ضَرَبَ اللَّهُ مَثَلًا كَلِمَةً طَيِّبَةً كَشَجَرَةٍ طَيِّبَةٍ أَصْلُهَا ثَابِتٌ وَفَرْعُهَا فِي السَّمَاءِ
➧“አላህ መልካምን ቃል ስሯ (በምድር ውስጥ) የተደላደለች ቅርንጫፏም ወደ ሰማይ (የረዘመች) እንደሆነች መልካም ዛፍ አድርጎ ምሳሌን እንዴት እንደገለጸ
አላየኽምን?” ኢብራሒም፡24

➲ዛፍ ስሩ ሲቆረጥ እንደሚሞተው ሁሉ ፣ ዲንም በተውሒድ ላይ ካልቆመ ህይዎት አይኖረውም፡፡ ሰዎችም በእርሱ ተጠቃሚ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ተውሒድ በዲኑ ውስጥ ያለው ቦታ ልክ የዛፉ ስር ለዛፉ መቆሚያ ፣ የቤት መሰረቱ ደግሞ ለህንጻው መቆሚያ እንደሚያገለግለው ማለት ነው፡፡

ተውሒድ፡ የነብያቶችና የሩሡሎች ጥሪ ዋናው መሽከርከሪያ ፣ የመልእክታቸው ትኩረት እንደሆነ ከሚጠቁሙ መረጃዎች መካከል የሚከተለው የነብዩ صلى الله عليه وسلم ትክክለኛሐዲስ ይገኛል፡-

▪️"ألأنبياء إخوة من عالت ، وأمهاتهم شتى ، ودينهم واحد"

➧“ነብያቶች ከአንድ አባት ፣ ከተለያዩ እናቶች የሆኑ ወንድማማቾች ናቸው፡፡ዲናቸው አንድ ነው፡፡” ሙስሊም 2365

➠በአባት አንድ ናቸው ማለት በተውሒድ አንድ ናቸው ፣ ሁሉም በተመሳሳይ ወደአላህ ተውሒድ ነው ጥሪ የሚያደርጉት ማለት ነው፡፡ እናቶቻቸው የተለያዩ ናቸው ማለት ደግሞ ህግና መመሪያቸው የተለያዩ ናቸው ማለት ነው፡፡

➲አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡

▪️ لِكُلٍّ جَعَلْنَا مِنكُمْ شِرْعَةً وَمِنْهَاجًا ۚ

“ከእናንተ ለሁሉም ህግንና መንገድን አደረግን፡፡” አል ማኢዳህ፡48

➲ሶስተኛ፡- ተውሒድ ለአካለ መጠን በደረሱ ሰዎች ላይ የመጀመሪያው ግዴታ መሆኑ ነው፡፡ ወደዚህ እምነት ለመግባት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው መጀመሪያ ግዴታ የሚሆንበት ተውሒድ ነው፡፡ወደአላህ ጥሪ ማድረግ የፈለገ ማንኛውም ሰው ጥሪው የሚጀምረው በተውሒድ ነው፡፡

ይህን የሚጠቁሙ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡ ከእነርሱ መካከል የሚከተለው የረሡል صلى الله عليه وسلم ሐዲስ ይገኝበታል፡-

▪️"أمرت أن أقاتل الناس حتى يشهدوا أن لا إله إلا الله"
“ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ብለው እስኪመሰክሩ ድረስ ሰዎችን ልጋደል ታዝዣለሁ፡፡” ቡኻሪ፡25 ሙስሊም፡22

▪️ሌላው መረጃ ሙዓዝ ረድየላህ አንሁ ወደየመን ሲላክ ረሡል صلى الله عليه وسلم ያስተላለፉት መልእክት ነው፡፡

▪️إنك تقدم على قوم أهل كتاب ، فليكن أول ما تدعوهم إليه عبادة الله" الحديث

➲“ወደመጽሐፍ ባለቤቶች ትሄዳለህ፡፡ የመጀመሪያው ጥሪህ የአላህ ዒባዳ (አምልኮ) ይሁን፡፡” ቡኻሪ፡ 1458 ሙስሊም፡19 በሌላ ዘገባ፡-

▪️"إنك تقدم على قوم من أهل الكتاب ، فليكن أول ما تدعوهم إلى أن يوحدوا هللا تعالى"

➧“ወደመጽሐፍ ባለቤቶች ትሄዳለህ፡፡ የመጀመሪያው ጥሪህ አላህን (በአምልኮ) ብቸኛ እንዲያደርጉ ይሁን፡፡” ቡኻሪ፡7373 በሌላ ዘገባ፡-
▪️"إنك ستأتي قوما أهل الكتاب ، فإذا جئتهم ، فادعهم إلى أن يشهدوا أن لا إله إلا الله ، وأن محمدا رسول الله"

“ወደመጽሐፍ ባለቤቶች ትሄዳለህ ፤ያገኘሀቸው ጊዜ ከአላሀ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የሌለ መሆኑን ፤ሙሀመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን እንዲመሰክሩ ጥሪ አድርግላቸው፡፡” ቡኻሪ፡ 1496 ሙስሊም፡19



ኢንሻአላህ ይቀጥላል


【አንብብ በማንበብ ብዙ እውቀት ይገኛል】📚📚📚📚📚
La tehzen
➧የእውቀት ፍሬው ተግባር ነው ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➛ክፍል ዘጠኝ አምስተኛው፡ - ሰለፎቹ ባወቁት ለመስራት ተሸቀዳዳሚ ነበሩ ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➲ይህን ደረጃ ከሚያብራሩ ነጥቦች መካከል፡ የሰለፎች አስደናቂ ባህሪያቸው ነው፡፡ሰለፎቹ ተግባርን በቋሚነት ለመፈጸም ይሽቀዳደሙ ነበር፡፡ ከረሡል صلى الله عليه وسلم የሰሙትን ፈጥነው ለመተግባር ይቸኩሉ ነበር፡፡…
➲የእውቀት ፍሬው ተግባር ነው
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

➛ክፍል አስር
➭➭➭➭➭➭➭

➧ረሡል የዚህ ተመሳሳይ ለአቡደርዳእ አደራ እንዳሉት እንደሚከተለው ግልጽ አድርጓል፡-“ወዳጀ እስካለሁ ድረስ እንዳልተዋቸው በሶስት ነገሮች አደራ ብሎኛል” ከዚያም ከላይ የተዘረዘሩ ሶስት ነገሮችን አወሳ፡፡ ሙስሊም፡722

➠እድሜው አነስተኛ የሆነው ዑመር ብን አቢ ሰለማህ ረድየላህ አንሁ የዚህ ተመሳሳይ ተናግሯል፡- “ረሡል ተንከባክበው የሚያሳድጉኝ ትንሽ ልጅ ነበርኩ፡፡ እጀ በየማዕዱ ከዚያም ከዚህም ይንቀሳቀስ ነበር፡፡ የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم የሚከተለውን ምክር መከሩኝ፡፡

▪️"يا غلام! سم الله، وكل بيمينك، وكل مما يليك"
“አንተ ልጅ ሆይ! ቢስሚላህ ብለህ ብላ ፣ በቀኝህ እጅህ ብላ ፣ የፊት የፊትህን ብላ፡፡”

ቡኻሪ ደግሞ የሚከተለውን ጨምረዋል፡-

"فما زالت تلك طعمتي بعد"

“ከዚያ በኋላ አመጋገቤ (እንደመከሩኝ) ከመሆን አልተወገደም” ቡኻሪ፡5376 ሙስሊም፡2022 በህጻንነቴ ይህን ምክር ከመከሩኝ ጀምሮ ማለቱ ነው፡፡

➧ልጆች በተደጋጋሚ - አንድ ጊዜ ፣ ሁለት ጊዜ ፣ ሶስት ጊዜ - ሲምመከሩ ምክርን አይቀበሉም፡፡ ይህ ትንሽ ሶሃባ ግን በአንድ ጊዜ የተመከረውን ምክር ተቀብሎ የሚከተለውን ንግግር መናገሩን አስተውል! “ከዚያ በኋላ አመጋገቤ (እንደመከሩኝ) ከመሆን አልተወገደም”

➲ይህ ፣ ሰለፎቹ በአንድ በኩል ምን ያክል ለመልካም ነገር እንደሚሽቀዳደሙ ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እስከሚሞቱ በአንድ መልካም ስራ ላይ እንዴት እንደሚዘወትሩ ያስረዳል፡፡ የደጋግ ሰለፎችን ታሪክ ብናጠና በዚህ ትርጉም ላይ በርከታ ታሪኮችን ማቅረብ እንችላለን፡፡

▪️ለምሳሌ፡- የሱፍያን አስ'ሰውርይን -ረሂመሁሏህ- ንግግር እንከታተል፡-

▪️"ما بلغني حديث عن رسول الله – صلى الله عليه وسلم – إلا عملت به"

➧“ከረሡል صلى الله عليه وسلم አንድም ሐዲስ አይደርሰኝም በእርሱ የምሰራበት ቢሆን እንጅ፡፡”ዓምር ብን ቀይስ አልመላዒይ - ረሂመሁሏህ - ደግሞ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

▪️"إذا بلغك الحديث عن رسول الله – صلى الله عليه وسلم – فاعمل به ولو مرة تكن أهله"
“የረሡል ሐዲስ ከደረሰህ አንድ ጊዜ እንኳ ቢሆን በእርሱ ስራ ፣ ከ (ሱና) ባለቤቶች ትሆናለህና፡፡”

➲“አንድ ጊዜ እንኳ ቢሆን በእርሱ ስራ” ማለት ሱናዎችን በተመለከተ ነው፡፡ ፈርድና ዋጅቦችን ግን አንድ ጊዜ መስራቱ ከ (ሱና) ባለቤቶቹ አያደርገውም፡፡

➧ኢብን አልቀይም - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን የአቢ ኡማማህ ሐዲስ
እንደሚከተለው አስተላልፈዋል፡-

"من قرأ آية الكرسي دبر كل صالة مكتوبة لم يكن بينه وبين الجنة إلا أن يموت"

“ከሶላት በኋላ አየተል ኩርስይ የቀራ ሰው ሞት እንጅ በእርሱ እና በጀነት መካከል ምንም (የሚጋርደው) የለም፡፡” ነሳኢይ ፈልዓመሊ አል የውሚ ወለይላ፡ 100 ሐዲሱን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል ሲልሲለቱ አል ሐዲስ አስ ሶሂህ፡972

▪️“ሸይኹል ኢስላም - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን እንደተናገረ ደረሰኝ ይላል የእርሱ ደረሳ የሆነው ኢብን አልቀይም - ረሂመሁሏህ -
"ما تركتها عقيب كل صالة"

“(አየተል ኩርስይን) ከየሶላቱ መጨረሻ አንድም ትቻት አላውቅም፡፡” ዛዱ አል ማኣድ፡ 1/ 285 ከኢማም አህመድ - ረሂመሁሏህ - ደግሞ የሚከተለው ተወርቷል፡-
"ما كتبت حديثا إلا عملت به"

“አንድም ሐዲስ አልጽፍም የምሰራበት ቢሆን እንጅ፡፡” ከዚያም የሚከተለውን ተናገሩ፡-
▪️"حتى إنني سمعت أن النبي صلى الله عليه وسلم احتجم وأعطى الحاجم دينارا فاحتجمت وأعطيت الحاجم دينارا"

➭“ነብዩ صلى الله عليه وسلم ዋግምት ታግመው ላገማቸው አካል አንድ ዲናር መስጠታቸውን ስሰማ ፣እኔም ዋግምት ታገምኩና ለአጋሚው አንድ ዲናር ሰጥቻለሁ፡፡

➲ይህ ነው እንግዲህ ሰለፎች ለመልካም የነበራቸው ጉጉት ፤ በአንድ መልካም ስራ
ላይ የነበራቸው መዘውተር፡፡ አንድን እውቀት ፈጥነው ወደተግባር ይቀይሩታል፡፡ ከዚያም ቋሚ ደንበኛ ይሆናሉ፡፡


➛ኢንሻአላህ ይቀጥላል◉◉◉

【አንብብ በማንበብ ብዙ እውቀት ይገኛል】📚📚📚
La tehzen
➲ከተውሂድ አርማዎች ➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ➭ክፍል ሶስት ➻➻➻➻➻➻ ➲የተውሒድ መለያዎችና ትሩፋቶች ➧ተውሂድ ፦ የነብያቶች እና የሩሡሎች ጥሪ መሰረት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ህዝቦቻቸው ከመልእክተኞች ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያደምጡት ቃል የተውሒድን ቃል ነው፡፡ ወደአላህ ጥሪ ሲያደርጉ አንድ ብለው የሚጀምሩት በተውሒድ ነው፡፡ ምክንያቱም የኢስላም እምነት በእርሱ ላይ…
➧ከተውሂድ አርማዎች
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭

➻ክፍል አራት
➫➫➫➫➫

➲የተውሒድ መለያዎችና ትሩፋቶች
➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻

➧ተውሒድ፡ ለአካለ መጠን በደረሱ ሰዎች ላይ የመጀመሪያው ግዴታ ነው፡፡ ሰዎች ወደዚህ ዲን መጀመሪያ የሚገቡት በእርሱ ነው፡፡ የዲኑ መሰረት ተውሒድ ነው ፤ ዲኑ በእርሱ ላይ ይቆማል ፤ በእርሱም ላይ ይጀመራል።

➲አራተኛው፡- ሰላም ለማግኘትም ይሁን በሁለቱ አገር ወደቅኑ ጎዳና ለመመራት
ምክንያቱ ተውሒድ ነው፡፡

➲አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡

▪️الَّذِينَ آمَنُوا وَلَمْ يَلْبِسُوا إِيمَانَهُم بِظُلْمٍ أُولَٰئِكَ لَهُمُ الْأَمْنُ وَهُم مُّهْتَدُونَ

“እነዚያ ያመኑና እምነታቸውን በበደል ያልቀላቀሉ እነዚያ ለእነርሱ ጸጥታ አላቸው፡፡ እነሱም የተመሩ ናቸው፡፡” አል አንዓም፡82

➠ጸጥታ ወይም ሰላም በአላህ እጅ ነው፡፡አላህ - ሱብሃነሁ ወተዓላ - ዲኑን ፍጹም ለእርሱ ብቻ ለሚያጠሩ የተውሒድ ሰዎች እንጅ ጸጥታን ለማንም አይሰጥም፡፡ከዚህ በላይ የጠቀስነው የቁርኣን አንቀጽ በወረደ ጊዜ ሶሃቦች -ረዲየሏሁ ዓንሁም-በጣም ተጨነቁ፡፡ ወደረሡል صلى الله عليه وسلم በመምጣት የሚከተለውን ጥያቄ አቀረቡ፡-
▪️"يا رسول الله ! أينا لم يظلم نفسه؟"

“የአላህ መልክተኛ ሆይ! ማንኛችን ነን ነፍሳችንን የማንበድለው?”ይህ ማለት “ከእኛ መካከል አንድም ሰው አይኖርም ፤ ነፍሱን የሚበድል ቢሆን እንጅ” ማለታቸው ነው፡፡ ወይም “እያንዳንዳችን ነፍሳችንን እንበድላለን በመሆኑም ከጸጥታም ይሁን ከመመራትምንም አይነት ድርሻ አይኖረንም” ማለታቸው ነው፡፡
➲ከዚያም ነብዩ صلى الله عليه وسلم የሚከተለውን ምላሽ ሰጡ፡-
"ليس ذاك"
➧“ነገሩ እንደዚያ (እናንተ እንደተገነዘባችሁት) አይደለም”

“በቁርኣን አንቀጹ ላይ የተጠቀሰው በደል ፣ እናንተ የተገነዘባችሁት ዓይነት በደል
አይደለም፡፡” “የዚያ ጥበበኛና ደግ የሆነው ባሪያ - ሉቅማን - የተናገረውን ንግግር አላነበባችሁምን?” አሏቸው፡፡

▪️إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ

➲ማጋራት ታላቅ በደል ነውና” ያለውን (አስታውስ)” (ሉቅማን፡ 13)

➧በዚህ አንቀጽ የሚገኘውን “ዙልም” ሽርክ ወይም ማጋራት በሚለው የአላህ መልክተኛ صلى الله عليه وسلم ተርጉመውታል፡፡ ቡኻሪ፡6937

ይህ የቁርኣን አንቀጽ ምንም ሳያጋራ በአላህ ያመነ ሰው በሁለቱም አገር ጸጥታና መመራት እንዳለው ይጠቁመናል፡፡ የተውሒድ ሰው ከሆነ በሁለቱም አገር አላህ ጸጥታን እና መመራትን ይሰጠዋል፡፡ ይህ ደግሞ የተውሒድ ልዩ ገጽታው ነው፡፡

➲አምስተኛው፡- በሌሎች እምነቶች ተቃራኒ እርስ በርስ ከመጋጨትና ከመዋዥቅ ነጻ የሆነ እምነት ነው፡፡
➲ለዚህ ማስረጃው የሚከተለው ቁርኣናዊ አንቀጽ ነው፡

▪️وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا
“ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡” አን ኒሳእ፡82

➲ሰዎች በሚፈጥሯቸው እምነቶች ውስጥ በአብዛኛው እርስ በርስ የሚጣረሱና የሚምታቱ ነገሮች ይገኙበታል፡፡ከአላህ ኪታብና ከረሡል صلى الله عليه وسلم ሱና የመነጨ ትክክለኛና ጥልቅ የሆነ እምነት ፣ ሰላማዊ የሆነ ዓቂዳ ከሆነ ግን ከዚህ ሁሉ ነጻ ነው፡፡




ኢንሻአላህ ይቀጥላል
🖊🖊ኑርአህሠድ

【አንብብ በማንበብ ብዙ እውቀት ይገኛል】📚📚📚📚📚


https://t.me/httpsLatahzen
La tehzen
🍁ረመዳን ሽህሩን ሙባረክ🍁② ================== ★ የረመዳን ወር የትኩረት አቅጣጫዎች★ ① ልቦናዎች የሚደብቁትን ሁሉ የሚያየውና የሚያውቀው አላህ ሱ,ወ የኢማናችንን ጥንካሬ በዚህ ፆም ሊፈትነን እንደፈለገ በመገንዘብ ከፋተኛ ትኩረት መስጠት። ② ረመዳንን ስንፆም በኒያ (አስበንና ወስነን) መሆን አለበት ምክንያቱም ማንኛውም ኢባዳ ያለኒያ ስለማይሆን። ③ ቀኑን በሙሉ በመኝታ ከማሳለፍ…
🍁ረመዳን ሸህሩን ሙባረክ🍁

★ የረመዳን ወር አቀባበል★

ታላቁ እንግዳችን የተከበረው የረመዳን ወር ለመቀበል ሁሉም በየፊናው ተፍተፍ እያለ ይገኛል።
ከፊሉ ቤቱን በማፅዳት ፣ሌላው የምግብ አይነቶችን በመሸመት፣ ሌላው ደግሞ ይሩን ትሩፋት ለመጠቀም እቅድ እያወጣ… እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ለመሆኑ ይህ አያሌ የፈጣሪ ትሩፋትን በውስጡ ይዞ የመጣውን ይህን ወር ለመቀበል ትክክለኛው መንገድ የትኛው ነው?
በወሩ ውስጥ ያሉትን እያንዳንዱን የኢባዳ ወቅቶችን ሁሉ አሟጦ ለመጠቀም ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? በነዚ በተከበሩ ጊዜያት ውስጥ በኸይር ነገሮች መሽቀዳደም ያስፈልጋል አላህ እንዲህ ይላል፦"وفي ذلك فليتنافس المتنافسون"

"በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ"
በመሆኑም ከዚ በመቀጠል 💦የረመዳንን ወር በተሻለ መንገድ ለመቀበል የሚረዱ ነገሮችን በተወሰነ እናያለን።
1, ዱዓ መዱረግ፦ በፆም በሰላትና በዚክር ላይ እንድንጠነክር አላህ በሙሉ ጤንነትና አቅም ላይ ሆነህ ረመዳንን ወር እንዲያደርስህ ከአሁኑ ዱአ አድርግ አነስ ኢብን ማሊክ ረ,ዐ ነብያችን ሰ,ዐ,ወ የረጀብ ወር ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር ብለዋል "اللهم بارك لنا في رجب وشعبان وبلغنا رمضان"

"አለህ ሆይ ረጀብንና ሻእባንን ባርክልን ረመዳንን አድርሰን"

2,ምስጋና ማቅረብ በረመዳን ወር ከደረስክ ምስጋና አቅርብ ኢማሙ ነወዊይ አል አዝካር በሚለው ኪታባቸው ላይ እንዲ ብለዋል"አንድ አዲስ ፀጋን ያገኘ ወይም አንድ ችግር የተወገደለት ሰው ለአላህ ምስጋና ለማቅረብ ሱጁድ አድርጎ በሚገባው መልኩ ማወደስ ይገባዋል"
3, መደሰት፦ነብያችን ሰ,ዐ,ወ የረመዳን ወር ሲመጣ እንዲህ በማለት ሶሀቦችን ያበስሩ ነበር"جاءكم شهر رمضان مبارك كتب عليكم صيامه فيه تفتح ابواب الجنان وتغلق فيه ابواب الجحيم"

"የተባረከ የረመዳን ወር መጥቶላችሇል እሱን መፆም አላህ በናንተ ላይ ደንግጓል በረመዳን ወር የጀነት በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ"

4, ንሰሀ መግባት፦የረመዳንን ወር ከወንጀል ሁሉ ለመራቅና ለመፅዳት ወደ ወንጀል ላከመመለስ መወሰንና እውነተኛ ተውበት ማድረግ ና ወደአላህ ለመመለስ ቆርጠን ልንነሳ ይገባናል።

5,ሰለረመዳን መማር፦ሙእሚን አላህን መገዛት ያለበት በእውቀት ላይ ተመስርቶ ነው።አላህ በባሮቹ ላይ ግዴታ ያደረጋቸውን ነገሮችና አፈፃፀሙን አለማወቅ ማንኛውንም ሙስሊም ይቅርታ ሊደረግለት የማይችል ጉዳይ ነው። አላህ እንዲ ይላል"فاسائلو اهل الذكر ان كنتم لا تعلمون"
"የማታውቁ ከሆናችሁ የሚያውቁትን ጠይቁ"

ወላሁ ተዐላ አዕለም ።

https://t.me/httpsLatahzen

ኑርአህመድ ሙሀመድ 🖊🖊
#እናት

በሁሉም ጭንቅላት በሁሉም ልቦና
በየአንዳንዱ አእምሮ በየአንዳንዱ ህሊና
አንዲት እንስት አለች አንዲት የሴት ጀግና

እናት
በትንሽ ወረቀት በሰለለ ቡእር
ስለናት በስንኝ ለመጻፍ ስሞክር
ንቀት መስሎ ታየኝ ክብሩዋን የምዳፈር

የማዬን
ተስፋዋን ምኞትዋን ወይስ መልካምነት
ደግነትዋን ፍቅርዋን ወይስ እሩህሩህነት
በስንኝ አስሬ በቃል አትሬ የማሳንስባት
የቱን ልተው የቱን ብዬ
ምኑን ላንሳ ምኑን ጥዬ
ማን ጽፎ እንደጨረሰ ልጨርሰስ ነው ስለምዬ
ቃላት ማሳመሩም ግጥሙም ይቅርባት
ምንም ሳልናገር ዝም ብዬ ልውደዳት
እምዬ የኔ እናት