La tehzen
94 subscribers
175 photos
111 videos
32 files
480 links
"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም"
ቁርዓን96:1

"ከመልካም ተግባር ምንንም አሳነሰህ አትመልከት፤ ወንድምህን
በብሩህ ፈገግታ መገናኘትን እንኳን"
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)


ሀሳብ አስታየት ካላችሁ👉👉👉 @Oufeyret
Download Telegram
━━━━━━✦✿✦━━━━━━
ነብዩ ﷺ በመሰደባቸው የተቆጣው ውሻ
━━━━━━✦✿✦━━━━━━

: ከሞጎላዊያን አንድ ባለስልጣን የክርስትናን ሃይማኖት ከተቀበለ ጥቂት ጊዜያት በኋላ ሀይማኖቱን መቀበሉን አስመልክቶ በተዘጋጀ ድግስ ከተወሰኑ ቄሳውስቶች ጋር ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። ከአቅራቢያቸው አንድ ለአደን የተዘጋጀ ውሻ ታስሯል።
: በወቅቱ ከነበሩ ቄሶች አንዱ ለዓለማት እዝነት የተላኩትን ታላቁን ነቢ ሙሀመድ ﷺ በመጥፎ ማንሳትና መተቸት ብሎም መሳደብ ጀምሯል። ታዲያ ይህንን ሲሰማና ሲታዘብ የነበረው ውሻ እጅግ ተቆጣ ፤ ወዲያውኑ በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸ ተሳዳቢውን ቄስ ዘሎ ነከሰውና አቆሰለው ፤ በአቅራቢያው የነበሩ ሰዎችም ተረባርበው አዳኑት ። ሰዎቹም፦ "ውሻው የምትናገረው ነገር አልተስማማውምና ሰለ ሙሀመድ (ﷺ) መጥፎ ከመናገር ተቆጠብ" ይሉታል ፤ ሰውየው ግን ፦ "አይ ችግሩ ከምናገረው አይመስለኝም ባይሆን በምናገርበት ወቅት እጄን ስዘረጋና ሳንቀሳቅስ ስለነበር እሱ ላይ የጠቆምኩበት መስሎት ነው" በማለት ስድብና ትችቱን ቀጠለ። ውሻው ግን ከመጀመሪያው በከፋ መልኩ በከፍተኛ ቁጣና ንዴት ዘሎ ጉሮሮውን በመንከስ ሰውየውን ገደለው።

👉 ይህ ክስተት በጊዜው የነበሩ ሰዎችን በከፍተኛ መልኩ አስገርሞ ነበር ፤ በዚህም ውሻ ምክንያት በወቅቱ ወደ 40 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች እስልምናን ተቀበሉ።

👉 ክስተቱን ታላቁ አሊም ኢብኑ ሀጀር "አዱረሩል ካሚናህ" በተባለው መፅሃፋቸው አስፍረውታል።

የአላህን ሰራዊቶች እርሱ እንጂ ማንም አያውቃቸውም


ﺍﻟﻠﻬﻢّ ﺻﻞِّ ﻋﻠﻰ ﻣﺤﻤّﺪ ﻋَﺒْﺪِﻙَ ﻭﻧَﺒِﻴِّﻚَ ﻭﺭﺳﻮﻟِﻚَ ﺍﻟﻨﺒﻲِّ
ﺍﻷمي"
➪ባለቤትሽን ስለ መልካምነቱ ማመስገንሽ ፍቅራችሁን ከማጎልበቱና እሱን
ለበለጠ መልካምነት ከማበረታታቱ ባሻገር አላህን ማስደሰት ነው!!
ﻗﺎﻝ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ‏(ﻻ ﻳﻨﻈﺮ ﺍﻟﻠﻪ ﺇﻟﻰ ﺍﻣﺮﺃﺓ ﻻ ﺗﺸﻜﺮ ﻟﺰﻭﺟﻬﺎ ﻭ ﻫﻲ ﻻ
ﺗﺴﺘﻐﻨﻲ ﻋﻨﻪ ‏) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﻨﺴﺎﺋﻲ ﻭ ﺻﺤﺤﻪ ﺍﻷﻟﺒﺎﻧﻲ ﻓﻲ ﺍﻟﺼﺤﻴﺢ 289
𒊹︎︎︎የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፤
«ከባሏ የማትብቃቃ ስትሆን ባሏን የማታመሰግን ሴት፣ አላህ በእዝነት አይኑ
አይመለከታትም።”
𑁍 ኢማሙ ነሳኢ ዘግበውታል፤ አልባኒም ሰሒህ ብለውታል
🔻የምፈራላችሁ ነገር ቢኖር ስሜትን መከተልንና ምኞትን ማስረዘም ነው።

🔻ሰሜትን መከተል ሐቅን እንዳንቀበል ያረጋል።
ምኞትን ማስረዘም አኺራን ያስረሳል።

🔻ዱንያ ጀርባዋን ሠጥታን እየሄደች ነው፤
አኺራ ፊቷን ወደኛ አዙራ እየመጣች ነው፤
የአኺራ እንጂ የዱንያ ሰው አትሁኑ ፤

🔺ዛሬ ሥራ እንጂ ምርመራ የለም፤
ነገ ምርመራ እንጂ ሥራ የለም።

🔺ዐልይ ኢብኑ አቡ ጧሊብ ረደሏሁ አንሁ
اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيرَاً، اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيراً، اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيراً، وَالْحَمْدُ لِلَّهِ كَثيراً، وَالْحَمْدُ لِلَّهِ كَثيراً، وَالْحَمْدُ لِلَّهِ كَثيراً، وَسُبْحَانَ اللَّهِ بُكْرَةً وَأَصِيلاً
🍃🌻
⛔️ከሰዋች ሁሉ ሌባ ማን ነው⁉️

♻️ነብዩ ( صلى الله عليه وسلم )፡- #በስርቆት አደገኛው ሰው ማለት ከሠላቱ ላይ የሚሰርቅ ነው፡፡; ሲሉ፦
🔰ሠሓቦች፡ «ከሰላቱ ላይ የሚሰርቀው እንዴት ነው?» በማለት ጠየቁ፡፡
♻️እሳቸውም፡ #ሩኩኡንም ሱጁዷንም በማጓደል ነው። በማለት መለሱላቸው
📚 (አህመድ 22642)

በሠላት ውስጥ የማይረጋጋ ሰው፣ በሠላቱ ሊመሰጥ አይችልም፡፡ ምክንያቱም መፍጠን መመሰጥን ስለሚጻረር ነው፡፡ እንደ አሞራ ጎንበስ ቀና ማለት ምንዳን ያሳጣል፡፡

ነብዩ ( صلى الله عليه وسلم ) ሠላትን ሲሰግዱ፣ በሩኩዓቸውም በሱጁዳቸውም ውስጥ፣ እያንዳንዱ መገጣጠሚያቸው ወደ ቦታው እስኪመለስ ድረስ በመረጋጋት ነበር፡፡ ሠላቱን ማሳማር ያልቻለውን ሰውዬ፣ በሠላቱ ውስጥ በሚፈፅማቸው ተግባሮችን በሙሉ በእርጋታና በዝግታ እንዲፈፅም አዘውታል፡፡ መቻኮልን ከልክለዋል፤ችኮላን ከአሞራ ውሃ አጠጣጥ ጋር አመሳስለውታል፡፡
🔰🔰የዕለቱ ሀዲስ🔰🔰

"▪️ከአቡሁረይራ በተዘገበ ሀዲስ ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፤

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ : ”...احْرِصْ عَلَى مَا يَنْفَعُكَ وَاسْتَعِنْ بِاللهِ وَلَا تَعْجَزْ، وَإِنْ أَصَابَكَ شَرٌّ فَلَا تَقُلْ لَوْ أَنِّي فَعَلْتُ كَذَا وَكَذَا قُلْ قَدَّرَ اللهُ وَمَا شَاءَ اللهُ فَعَلَ، فَإِنَّ لَوْ تَفْتَحُ عَمَلَ الشَّيْطَانِ“ رَوَاهُ مُسْلِم
ٌ
«በሚጠቅምህ ነገር ላይ ጉጉት ይኑርህ፤ በአላህ ታገዝ፤ አትሰላች፤ መጥፎ ነገር ባጋጠመህ ጊዜ፤ ‘ይህን ነገር እንዲህ ወይም እንዲያ ባደርገው ኖሮ…’ አትበል። ነገር ግን ‘አላህ የወሰነው ሆነ፤ አላህ የፈለገውን ይሰራል’ በል። ‘እንዲህ ቢሆን ኖሮ’ የሚለው ንግግር ለሰይጣን ስራ በር ይከፍታል» ሙስሊም ዘግበዉታል


📝አላህ ተቅዋን እና መልካም ስራን ያግራልን!

وصلَّى الله على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلَّم
የቲም

🏷የቲም ማለት:– ሴትም ሆነች ወንድ ለአቅመ አደም ሳይደርሱ አባታቸው የሞተባቸው ናቸው። እነሱም የሚታዘንላቸው የእዝነት ስፍራዎች ናቸው፣ ምክንያቱም ልባቸው በአባታቸው ሞት ተሰብራለች፣ አጋዥም ሆነ ተንከባካቢ ከአላህ በስተቀር የላቸውም።


⛔️የወላጅ አልባ (የቲም) ህፃናትን ሀቅ መብላትና እነሱንም መበደል ነው።‼️

⚠️4፥2 *"የቲሞችንም ገንዘቦቻቸውን ስጡ፡፡ መጥፎውንም በመልካሙ አትለውጡ፡፡ ገንዘቦቻቸውንም ወደ ገንዘቦቻችሁ በመቀላቀል አትብሉ እርሱ ታላቅ ኃጢአት ነውና"*፡፡

وَآتُوا الْيَتَامَىٰ أَمْوَالَهُمْ ۖ وَلَا تَتَبَدَّلُوا الْخَبِيثَ بِالطَّيِّبِ ۖ وَلَا تَأْكُلُوا أَمْوَالَهُمْ إِلَىٰ أَمْوَالِكُمْ ۚ إِنَّهُ كَانَ حُوبًا كَبِيرًا


﴿إِنَّ الَّذينَ يَأكُلونَ أَموالَ اليَتامى ظُلمًا إِنَّما يَأكُلونَ في بُطونِهِم نارًا وَسَيَصلَونَ سَعيرًا﴾ النساء ١٠
⚠️“እነዚያ የየቲሞችን ገንዘብ በመበደል የሚበሉ: በሆዶቻቸው ውስጥ የሚበሉት እሳት ብቻ ነው፣ እሳትንም በእርግጥ ይገባሉ።” (ኒሳእ 10)

⚠️ከ7ቱ አጥፊ ወንጀሎች አንዱ ነው።
የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
"ሰባት አጥፊ ወንጀሎችን ራቁ።" ሶሐቦች ምንድን ናቸው? ሲሉ ጠየቁ። የአላህ መልዕክተኛ: "በአላህ ማጋራት ፣ድግምት ፣በህግ ቢሆን እንጅ ያችን አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ መግደል፣ ወለድ መብላት ፣ #የየቲምን_ገንዘብ_መብላት፣ የጦርነት ቀን መሸሽ እና ጥብቅ፣ ከዝሙት የዘነጉ ምእምናትን መስደብ ናቸው።" አሉ። "

📚ቡኻሪ ዘግበውታል።

⚠️ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 22
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አላህ ሆይ! ምስክር ሁን! እኔ ያስጠነቀቁት ሁለት ድኩማን ጉዳይ አሉኝ፥ እነርሱም የቲም እና እንስት ናቸው"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ اللَّهُمَّ إِنِّي أُحَرِّجُ حَقَّ الضَّعِيفَيْنِ الْيَتِيمِ وَالْمَرْأَة


ነቢያችን"ﷺ" አባታቸው በሞት ያጡት እናታቸው ሆድ ውስጥ እያሉ ነበር፥ እናታቸውን ያጡት ደግሞ በተወለዱ በስድስት ዓመታቸው ነበር።
አምላካችን አላህ ስለ እርሳቸው የቲምነት ሲናገር፦
93፥6 *የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን?* ፡፡ أَلَمْ يَجِدْكَ يَتِيمًۭا فَـَٔاوَىٰ


🕸የቲምን መንከባከብ

የቲምን መንከባከብ በጎ አድራጎት እና ከአላህ ዘንድ አጅር አለው፥ በጀነት የነቢያችን"ﷺ" ጎረቤት ለመሆን ጉልህ ሚና አለው፦
4፥36 አላህንም አምልኩ፡፡ በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ *"በየቲሞችም፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በሩቅ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ባደረጓቸው ባሮች፣ መልካምን ሥሩ"*፤ አላህ ኩራተኛ ጉረኛ የኾነን ሰው አይወድም፡፡

وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا ۖ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا وَبِذِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينِ وَالْجَارِ ذِي الْقُرْبَىٰ وَالْجَارِ الْجُنُبِ وَالصَّاحِبِ بِالْجَنبِ وَابْنِ السَّبِيلِ وَمَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ مَن كَانَ مُخْتَالًا فَخُورًا

76፥8 *"ምግብንም ከመውደዳቸው ጋር ለድኻ፣ ለየቲምም፣ ለምርኮኛም ለእስረኛም ያበላሉ"*፡፡ وَيُطْعِمُونَ الطَّعَامَ عَلَىٰ حُبِّهِ مِسْكِينًا وَيَتِيمًا وَأَسِيرًا


عن سهلِ بن سعدٍ رضي اللَّه عنه قال: قال رسول اللَّه ﷺ:
(أَنَا وكافلُ الْيتِيمِ في الجنَّةِ هَكَذَا) وأَشَار بِالسَّبَّابَةِ وَالْوُسْطَى، وفَرَّجَ بَيْنَهُمَا.
📚رواه البخاري.

ከሰህል ቢን ሰዕድ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[እኔ እና የቲም ተንከባካቢ በጀነት ውስጥ እንደዚህ ነን።] በመጠቆሚያ ጣታቸውና በመሀል ጣታቸው ትንሽ ከፈት አድርገው ጠቆሙ።
📚ቡኻሪ ዘግበውታል ።

#ልቡ_የደረቀበት_ሰው_የቲሞችን_ያስጠጋ
አንድ ሰው ወደ አቢ ደርዳእ (ረዲየላሁ ዐንሁ) መጣና (ወሲያ) ምክር ብጤ ኑዛዜ ንገረኝ? አለው: አቢ ደርዳም እንዲህ አለው:– ለየቲም እዘን፣ ወዳንተም አስጠጋው፣ ከምግብህም አብላው፣ እኔ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘንድ አንድ ሰው መጥቶ ልቡ ስለመድረቁ ስሞታ ሲነግራቸው ሰምቼ የሚከተለውን ብለውታል:– (ልብህ እንዲረጥብ ከፈለግከ የቲምን ወዳንተ አስጠጋ፣ ፀጉሩን አባብሰው፣ ከምግብህም አብላው፣ ይህ ልብህን ያረጥበዋል፣ ጉዳይህንም ማሳካት ትችላለህ።) [ኢማሙ አህመድ 2/263፣ በይሀቂ በሹዐብ 11034 የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒ በሶሂሁል ጃሚዕ 1410 ሶሂህ ነው ብለውታል።]


============
አንዳንድ ለየቲሞች ኀላፊ የሆኑ ሰዎች (አላህ ይጠብቀንና) የየቲሞችን ገንዘብ ለራሳቸው ይበደሩታል፣ለራሳቸው ይጠቃቀሙበታል፣ ስራ የሚሰሩበት፣ የሚገባዩበት ለራሳቸው ነው፣ የየቲሞች ገንዘብ ግን ለነሱ የሚጨምር ነገር የለም። ይህ የከፋ ወንጀል ነውና እጅግ በጣም ልንጠነቀቅ ይገባል።
Audio
🔹ከካፊሮች ጋር መመሳሰል
🔹የፍቅረኛሞች ቀን ማክበር
🔹ኢስላማዊ አመት በአሎች

♦️በድጋሚ የተለቀቀ

🎙 አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/1672
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/1672
ዱንያ_አኼራ

🌺ሀሰን_አልበስሪ እንዲህ አሉ { የዱንያ እና የአኼራ ምሳሌ ልክ አንደ ምስራቅ እና ምዕራብ ነው። ወደ አንዳቸው መቅረብን ስትጨምር ከሌላኛው ደግሞ መራቅን ትጨምራለህ!!}

መልካም ምሽት😘
«ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ በመልካም ሥራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ፡፡ እነዚያም እነሱ የሚድኑ ናቸው፡፡» (ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 104)
🍁ረመዳን ሸህሩን ሙባረክ🍁
====================
★ ረመዳንን ከሌሎች ወሮች የሚለዮ 10 ነገሮች★


አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ሁላችንም እንደምናውቀው ውዱ የበረካ ወር የሆነው ረመዳን ለተጠቃሚዎች በበረካው ሊያምበሸብሻቸው አንድ ሁለት እያለነው ረመዳን በአመት ውስጥ ካሉ 12 ወራቶች አንዱ ነው እንዲሁም ቁርአን ውስጥ ከተጠቀሱት 4 የላቁ ወራትም አንዱ ነው። ረመዳን ከሌሎች ወሮች ለየት የሚያደርጉት ብዙ ነገሮች አሉ ከነዛም ዉስጥ
① ፆም መደንገጉ ፦ የረመዳንን ወር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች መሀከል አንዱና ዋነኛው ወሩን እንድንፆም መታዘዛችን ነው
ፆም አላህ ዘንድ በጣም ከፍተኛ ቦታ ካላቸው ኢባዳዎች መሀከል አንዱ ነው ፆም የሱና እና ዋጂብ የሚባሉ ክፍሎችም አሉት የሱና ፆም የሚባለው መፆም የተከለከለ ባቸው ጊዜያት ሲቀሩ በማንኛውም ቀን መፆም የሚቻል ሲሆን ዋጂብ ወይም ፈርድ(ግዴታ) የሚባለው ፆም ደግሞ አላህ በባሮቹ ላይ ግዴታ ያደረገው የፆም አይነት ነው አላህ ፆምን በኛላይ ግዴታ ማድረጉን ሲናገር እንዲ ይላል
(يا ايها الذن امن كتب عليكم اصيم كما كتب اللذين من قبلكم لعلكم تتقون)
(እናንተ ያመናችሁ ሆይ ፆም በናንተ ላይ ግዴታ ተደርጓል ልክ ከናንተ በፊት በነበሩት ግዴታ እንደተደረገው) ከዚ የቁርዓን አያ የምንማረው የመጀመሪያው ከኛበፊት በነበሩት ህዝቦች ላይ መደንገጉን እና በኛም ላይ መደንገጉን ነው።
② የቁርአን መውረድ፦ ቁርአን ለሰውልጆች መመሪያና ማስተማሪያ ነው እንዲሁም ከዚበፊት የሆኑ ፣አሁን እየሆኑያሉና ወደፊት የሚሆኑ ለኛ አስተማሪና አስጠንቃቂ የሆኑ ነገሮችን የያዘ ነው። የዚህ ዉድ ቁርአን በረመዳን መውረድ ረመዳንን ከሌሎች ወሮች ለየት ከሚያደርጉ ነገሮች መሀከል አንዱ ነው። እና እኛ በዚ በረመዳን ቁርአንን ልንቀራ ይገባናል
ቀደምት ደጋግ ቀደምቶች በረመዳን እስከ 60 ጊዜ ያኸትሙ ነበር።አኛስ?
③ የሰይጣን መታሰር፦ በረመዳን ወርየጀነት በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ አመፀኛ ሰይጣናትም ይታሰራሉ። ነብያችን ሰ,ዐ,ወ እንዲህ ይላوغلقت السماء، ابواب فتحت رمضان إذا دخل إذا رواية وفي الشياطين وسلسلت جهنم،ابواب الجنة ابواب فتحت رمضان جاء

" ረመዳን ሲገባ የሰማይ በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ ሰይጣናትም ይቀፈደዳሉ ።’’ በሌላ ዘገባም” የጀነት በሮች ይከፈታሉ” ብለዋል(ቡኻሪና ሙስሊም)

④ የስራዎች ምንዳ መደራረብ፦ በረመዳን ወር የሐሰናት ወይም የመልካም ስራዎች ምንዳ እጥፍ ድርብ ይሆናል። ነብዩ ሰ,ዐ,ወ ተጠይቀው ከሰደቃዎች ሁሉ በላጩ የቱ ነው ተብለው "በረመዳን የሚሰጥ ነው ብለዋል"
⑤ ከአንድሺ ሌሊቶች በላጭ የሆነችው ለይለትል ቀድር፦ አላህ ከአንድ ሺህ ሌሊቶች ያስበለጣት ሌሊት ናት እንዲሁም የአመቱን ጉዳዩች የሚፅፍባት የተበረከች ሌሊት ናት "ليلة القدر خير من الف شهر"
" ሌሊቶችም በላጭመወሰኛይቱ ሌሊት ከሺህ ናት"

⑥ መላኢኮች በብዛት ወደ መሬት መውረድ፦ አላህ አንዲ ይላል ፦تنزل الملاإكة والروح فيها بإذن ربهم من كل أمر"
"በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ "
⑦ ሱሁር (የሌሊት ምግብ) ፦ ሱሁር ካለፍት ህዝቦች ፆም የኛን የሚለይና ብዙ በረካዎችን የያዘነው ነብዩ ሰ,ዐ,ወ እንዲህ ይላሉ "تسحروا فإن في السحور بركة"
"ሱሁርን ብሉ ሱሁር መብላት
በረካ አለውና "
⑧ የተራዊህ ሰላት፦በረመዳን ብቻ በጀማአ የሚሰገደው የሱና ሰላት የሆነው ተራዊህ አንዱ ረመዳንን ለየት ከሚያደርጉ ነገሮች መሀከል አንዱ ነው። ከረመዳን ውጭ ይህ ሰላት አይሰገድም ።
⑨ የኡምራ ትሩፋት፦በረመዳን ወር ኡመራ ማድረግ ከነብዩ ሰ,ዐ,ወ ጋር ሀጅ እንደ ማድረግ ነው።"عمرة في رمضان تعدل حجة او قال حجة معي"
"በረመዳን የሚደረግ ኡምራ ከሀጅ ጋር እኩል ነው ወይም ከኔጋር ከሚሰራ ሀጅ እኩል ነው"ብለዋል
¹⁰ ወንጀል ማበሻ፦ረመዳን ወንጀል እንዲታበሱ ከሚያደርጉ ነገሮች መሀል አንዱና መሰረታዊው ነው።
" الصلوات الخمس ولجمعة الى الجمعة ورمضان الى رمضان مكفرات لما بينهن إذا اجتنبت الكبائر"
"ታላላቅ ወንጀሎች ከተራቁ አምስት ወቅት ሰላቶች ከጁምአ እስከ ጁምአ ከረመዳን እስከ ረመዳን በመሀከላቸው ያለውን ወንጀል ያስምራሉ"

አላህ ካለ ከረመዳን ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዩች ላይ ክፍል ሁለት ይቀጥላል።

@Nurahend




https://t.me/httpsIBNumuhammed
«ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ በመልካም ሥራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ፡፡ እነዚያም እነሱ የሚድኑ ናቸው፡፡» (ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 104)
📿የጧት ዚክር📿

سُبْحَانَ اللهِ وَبِحَمْدِهِ: عَدَدَ خَلْقِهِ، وَرِضَا نَفْسِهِ، وَزِنَةَ عَرْشِهِ وَمِدَادَ كَلِمَاتِهِ. (3× إذا أصبح)

‹‹ለአላህ ጥራት ይገባው፡፡ ምስጋናም፡፡ በፍጡራኑ ቁጥር ልክ፤ ነፍሱ በወደደችው ልክ፤ በዙፋኑ ክብደት ልክ፤ በቃላቱ ብዛት ልክ፡፡›› ሦስት ጊዜ

اَللَّهُمَّ إِنِّيْ أَسْأَلُكَ عِلْمًا نَافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلاً مُتَقَبَّلاً. (إذا أصبح)

‹‹ኣላህ ሆይ! ጠቃሚ እውቀትን, መልካም የሆነ ሲሳይን, ተቀባይነት ያለውን ተግባርን እጠይቅሀለሁ።
((سُبْحانَ رَبِّيَ الْعَظِيمِ))
🍃🌻
((سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا وَبِحَمْدِكَ، اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي)).
🍃🌻
🌿🌿🌿🍃ጥቆም🍃🌿🌿🌿

💫ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ:-

"አንድ ሰው ዕውር ካለ መሆኑም ጋ ዐይኖቹን ቢጨፍናቸው ምንም ነገር ማየት እንደ ማይችለው ሁሉ፤ቀልብም በሚሸፍናት የወንጀል ጨለማ ምክንያት ሐቅን መመልከት አትችልም።"

🔻አይን ኖሮን ከመታወር ቀልብ ኖሮን ከመደናበር እናስተውል።አላህም ይጠብቀን።
سورة الملك
القارئ عبدالعزيز الغنام
🌹ዉብ ቲላዋ

📚አይጠገብም የጌታችን ቃል

ስንደጋግመዉ የበለጠ ፍቅሩ የሚጨምር እደቁርዓን የለም!

🍃ሁሉም ሲበዛ ይመራል ቁርዓን ግን ይጣፍጣል በደጋገምነዉ ቁጥር!!

https://t.me/httpsLatahzen
#ጊዜህን ተጠቀምበት

➡️እስልምና ሙሉ የህይወት ህግ ነው እና ጊዜን ማባከን ወይም ጊዜን ማጥፋትን በማይጠቅሙ ነገሮች ላይ በጣም ከባድ በሆኑ ማስታወሻዎች ላይ ተናግሯል ። የመጨረሻው የአላህ መልእክተኛ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይኺ ወሰለም)ም አስጠንቅቀውናል።

➡️ማስጠንቀቂያው የጊዜ ብክነት የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅእኖ አስመልክቶ ሲሆን ከጥቅም ውጭ በሆኑ እና በሃራም እንቅስቃሴዎች ውስጥ ያለውን ጊዜ ፍጆታ መቀነስ ላይ አፅንዖት ሰጥቷል።

🍃እንደምናውቀው አለም በጊዜያዊነት የተፈጠረች እና የሁሉም ሙስሊም ፈተና ናት።

🍃ዓለም ጊዜያዊ ቦታ እና ከዚህ በኋላ ህይወት መሆኗን የመገንዘቡ እውነታ እራሱ ለዘላለም ሊቆይ የሚገባው ነገር ጊዜያችንን በተቻለ መጠን ጠቃሚ የማድረግ እውነታ ላይ ያጎላል።

🔑በወጣትነት ፣በጉልበት እና ሙሉ ህይወት ባለንበት ወቅት በእጃችን ከነበሩት የታላቁ አላህ ፀጋዎች አንዱን እናጠፋለን ይህም ጤናማ አካል ጥሩ ጤና እና ጊዜ ማለት ነው ።በተለይ በእርጅና እና በምንደክምባቸው ጊዜያት ረዘም ላለ ጊዜ ጥቅም በሚሰጡ ነገሮች ላይ ጊዜዎን ማዋል አስፈላጊ ነው።

💦ለመኖር በጣም የተገደበ ጊዜ ተሰጥቶናል ስለዚህ ከፍተኛ ጥረታችን በእስልምና አስተምህሮ እና በሱና መሰረት ህይወታችንን መምራት አለብን።

💦ህይወታችን ለታናናሾቻችን አርአያ እንዲሆንልን አብረን ዱዐእ እናድርግ።ይህም ለብዙዎች አበረታች ከሆነው የጥሩነት እና የጤንነት ስፋት በስተቀር ሌላ አይደለም።

✏️በበቂ ሁኔታ ልናመሰግነው የማንችለው የአላህ በረከቶች እና ፀጋዎች ብዛት ተሰጥቶናል ስለዚህ ህይወታችንን ጠቃሚ ማድረግ እና ለሌሎችም አዎንታዊ ተጽእኖ መፍጠር አለብን


➡️ አስቸጋሪነት ቀደም ሲል የሠራናቸው የብዙ መጥፎ ወይም ጥፋቶች ውጤቶች ናቸው።ህይወት ሊተነበይ የማይችል እና ሞት የቀን መቁጠሪያ ስለሌለው በተቻለ ፍጥነት ለኃጢአታችን ይቅርታ እንድንጠይቅ ይመከራል።


የጊዜ በረራ የግድ እና አስቀድሞ የተወሰነ ነው። እኛ ነን ወደ ኋላ የቀረን እና በሰአት መሮጥ የሚገባን።

የወዲያኛው ሕይወት ማለቂያ የሌለው የጊዜ መንገድ ተብሎ ታውጇል እናም አሁን ያለው ሕይወት ሌላ አይደለም ነገር ግን ወደፊት የሚሄድ እና በቅርቡ ያልፋል ጊዜያዊ ምዕራፍ ነው እናምአጽንዖታችን መሆን ያለበት ለቀጣዩ ሕይወት ለመዘጋጀት ነው።


عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ لِرَجُلٍ وَهُوَ يَعِظُهُ اغْتَنِمْ خَمْسًا قَبْلَ خَمْسٍ شَبَابَكَ قَبْلَ هَرَمِكَ وَصِحَّتَكَ قَبْلَ سَقَمِكَ وَغِنَاكَ قَبْلَ فَقْرِكَ وَفَرَاغَكَ قَبْلَ شُغُلِكَ وَحَيَاتَكَ قَبْلَ مَوْتِكَ‎


ረሱል አለይኺ ሰላት ወሰላም ከኢብኑ አባስ ተይዞ እንዳስተላለፉት፦«አምስት ነገሮች ከአምስት ነገር በፊት ተጠቀምባቸው።


🍃ወጣትነትህ ከእርጅናህ በፊት

🍃ጤናህ ከበሽታህ በፊት

🍃ሃብትህ ከድህነትህ በፊት

🍃ነፃ ጊዜህን ከመጠመድህ በፊት

🍃ህይወታችሁን ከመሞታችሁ በፊት» ብለዋል።

( አል ሀኪም) ዘግበውታል 📚📚


عَنْ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ نِعْمَتَانِ مَغْبُونٌ فِيهِمَا كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ الصِّحَّةُ وَالْفَرَاغُ‎

ኢብኑ አባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ)እንዲህ አሉ ረሱል (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ አሉ፦«ብዙ ሰዎች የሚያጡት ሁለት በረከቶች አሉ። (እነሱም) ጤና እና መልካም ለመስራት ነፃ ጊዜ ናቸው።»

(ቡኻሪ 8/421)