ምስጢሩ
አንቺ እየከሳሽ እኔ መፋፋቴ
አንቺ አኅንብሰሽ እኔ መቃናቴ
ተርቦ አንጀትሽ ጠግቤ መብለቴ
ባዶ እግርሽን ሆነሽ እኔ መጫማቴ
አንቺ አፊሽ ደርቆ እኔ መጠጣቴ
አንቺ ሳትማሪ ተምሬ ማወቄ
ልፋትሽ ተረስቶ እኔ መደነቄ
ዕውቀትና ክብሬ ስጦታ ውበቴ
ሽልመት ማዓረጌ መልኬ ደም ግባቴ
የእኔ እኮ አይደለም የአንቺ ነው እማ እናቴ
አንቺ እየከሳሽ እኔ መፋፋቴ
አንቺ አኅንብሰሽ እኔ መቃናቴ
ተርቦ አንጀትሽ ጠግቤ መብለቴ
ባዶ እግርሽን ሆነሽ እኔ መጫማቴ
አንቺ አፊሽ ደርቆ እኔ መጠጣቴ
አንቺ ሳትማሪ ተምሬ ማወቄ
ልፋትሽ ተረስቶ እኔ መደነቄ
ዕውቀትና ክብሬ ስጦታ ውበቴ
ሽልመት ማዓረጌ መልኬ ደም ግባቴ
የእኔ እኮ አይደለም የአንቺ ነው እማ እናቴ
ይገርማል!
ይገርማል ሰው ሁሉ እራሱን አልቆ
ጌታውን ሲያረክስ፣
አኼራን ረስቶ ከታች ከላይ ሲሮጥ
ዱኒያን ሊያግበሰብስ፣
ያለ አቅሙ ሲኮፈስ ፤ ከላይ ሲንጠራራ፣
በሰው ለመወደድ ፤ የማይሆን ሲሰራ ....፤
ይገርማል ....፤
ከመሞት ላያመልጥ ፤ ላይረዳው ልጅ ሀብቱ፣
ይገርማል ሰው ሞኙ ፤ ጌታ ያዘዘውን ስራውን መርሳቱ!!
ይገርማል ሰው ሁሉ እራሱን አልቆ
ጌታውን ሲያረክስ፣
አኼራን ረስቶ ከታች ከላይ ሲሮጥ
ዱኒያን ሊያግበሰብስ፣
ያለ አቅሙ ሲኮፈስ ፤ ከላይ ሲንጠራራ፣
በሰው ለመወደድ ፤ የማይሆን ሲሰራ ....፤
ይገርማል ....፤
ከመሞት ላያመልጥ ፤ ላይረዳው ልጅ ሀብቱ፣
ይገርማል ሰው ሞኙ ፤ ጌታ ያዘዘውን ስራውን መርሳቱ!!
🌙ረመዷን 13✨
▒▒▒ ያኔ ~ አልቅስ ‼ ▒▒▒
👉 በነፍስህና በስሜትህ ተበልጠህ
ለትናንሽም ሆነ ለትላልቅ ወንጀሎች
በቀላሉ እጅ የሰጠህ ቀን።
👉 መልካም ነገርን እያየህ ከመሥራት
ስትሰንፍ ፣ መጥፎን ደግሞ መጥፎነቱን
እያወቅክ ስትዳፈር።
👉 ለሙዚቃ ፣ ለድራማና ለፊልም
ውስጥህ ሲነካ ፡ ለቁርዓን ልብህ
ሲደነደን።
👉 ለዱኒያና ለጥቅሞቿ ስትሮጥ
እንቅልፍ ስታጣ ለአኺራህ ግድ የለሽ
ስትሆን።
👉 ሶላትህ ትርጉም ስታጣብህ ፣
ሩኩዕና ሱጁድ ጎንበስ ቀና ስፖርታዊ
እንቅስቃሴ ብቻ ሲሆንብህ።
👉 ከዒባዳህ ጥፍጥና ስታጣ በአምልኮ
ተግባርህ እርካታን ከተነፈግክ።
👉 ጊዜህን ባልረባ ነገር ስትጨርስ ፡
ኸይር ሳትጨምር ቀን አልፎ ቀን ከተተካ።
👉 የተውባ በር ሁሌም ክፍት ሆኖ
ሳለ ለመግባት ድፍረት ስታጣ።
👉 የዓለማዊው ሕይወት ፍጻሜ መቃረቡን ስታውቅ በበቂ አለመዘጋጀትህን ስትረዳ።
@sineislam @sineislam ☀️
▒▒▒ ያኔ ~ አልቅስ ‼ ▒▒▒
👉 በነፍስህና በስሜትህ ተበልጠህ
ለትናንሽም ሆነ ለትላልቅ ወንጀሎች
በቀላሉ እጅ የሰጠህ ቀን።
👉 መልካም ነገርን እያየህ ከመሥራት
ስትሰንፍ ፣ መጥፎን ደግሞ መጥፎነቱን
እያወቅክ ስትዳፈር።
👉 ለሙዚቃ ፣ ለድራማና ለፊልም
ውስጥህ ሲነካ ፡ ለቁርዓን ልብህ
ሲደነደን።
👉 ለዱኒያና ለጥቅሞቿ ስትሮጥ
እንቅልፍ ስታጣ ለአኺራህ ግድ የለሽ
ስትሆን።
👉 ሶላትህ ትርጉም ስታጣብህ ፣
ሩኩዕና ሱጁድ ጎንበስ ቀና ስፖርታዊ
እንቅስቃሴ ብቻ ሲሆንብህ።
👉 ከዒባዳህ ጥፍጥና ስታጣ በአምልኮ
ተግባርህ እርካታን ከተነፈግክ።
👉 ጊዜህን ባልረባ ነገር ስትጨርስ ፡
ኸይር ሳትጨምር ቀን አልፎ ቀን ከተተካ።
👉 የተውባ በር ሁሌም ክፍት ሆኖ
ሳለ ለመግባት ድፍረት ስታጣ።
👉 የዓለማዊው ሕይወት ፍጻሜ መቃረቡን ስታውቅ በበቂ አለመዘጋጀትህን ስትረዳ።
@sineislam @sineislam ☀️
የረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሙስሊም ተማሪዎች
የዝሁር ሰላትን እንዲ ባማረ መልኩ ሰግደው ተመልሰዋል🥰🥰🥰🥰
እዩዋቸው እስኪ አያስቀኑም የኔ ውቦች😍
የዝሁር ሰላትን እንዲ ባማረ መልኩ ሰግደው ተመልሰዋል🥰🥰🥰🥰
እዩዋቸው እስኪ አያስቀኑም የኔ ውቦች😍
⇛ኢማንህ ከፍ ሲልና ከአላህ እርዳታ ዉጭ አንድም ነገር ሊሳካ እንደማይችል ሲገባህ ሁሉ ነገርህን ለፈጠረህ አምላክ ለአላህ ትሠጣለህ። የማትችለውንም የምትችለውንም ሁሉ አንድም ሳታስቀር ታስረክበዋለህ። ገር ነገር ጭምር ሊገራልህ የሚችለው አላህ ሲያገራልህ ብቻ ነውና።
⇛ኢላሂ ጉዳያችን ሁሉ አንተው አግራልን!
⇛ኢላሂ ጉዳያችን ሁሉ አንተው አግራልን!
አሏህ ሱበሀነሁ ወተዓላ በተከበረው ቃሉ እንድህ ይላል፦
۞ وَسَارِعُوا إِلَىٰ مَغْفِرَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا السَّمَاوَاتُ وَالْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡
(ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 133)
ዛሬ በማያልቀው ገዘባችን ለመልካም ስራ እንሽቀዳደም ።።።።።
۞ وَسَارِعُوا إِلَىٰ مَغْفِرَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا السَّمَاوَاتُ وَالْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡
(ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 133)
ዛሬ በማያልቀው ገዘባችን ለመልካም ስራ እንሽቀዳደም ።።።።።