ኢላሂ
ዱዓችንን ማሳመር ባንችል እንኳ
ሓጃችንን አንተ ታውቃለህ ።
ምላሣችንን ቢንተባተብም
ሀሳባችንን ትረዳለህ።
አንደበታችን ቢተሳስርም
ምኞታችንን ታውቃለህ ።
የቱን ያህል ብናስመስልም
ውስጣችንን ታነባለህ።
ከኛ ጉዳይ ካንተ የተደበቀ ምን ነገር አለ!
ብናሳይህ ባናሳይህ ምን ይሳንሃል ጌታዬ
ደክሞኛል ደግፈኝ ያ ረቢ
ከፍቶኛል ጠግነኝ ፈጣሪዬ
ሆድ ባሠኝ ዳብሠኛ አካሚዬ!!!
ዱዓችንን ማሳመር ባንችል እንኳ
ሓጃችንን አንተ ታውቃለህ ።
ምላሣችንን ቢንተባተብም
ሀሳባችንን ትረዳለህ።
አንደበታችን ቢተሳስርም
ምኞታችንን ታውቃለህ ።
የቱን ያህል ብናስመስልም
ውስጣችንን ታነባለህ።
ከኛ ጉዳይ ካንተ የተደበቀ ምን ነገር አለ!
ብናሳይህ ባናሳይህ ምን ይሳንሃል ጌታዬ
ደክሞኛል ደግፈኝ ያ ረቢ
ከፍቶኛል ጠግነኝ ፈጣሪዬ
ሆድ ባሠኝ ዳብሠኛ አካሚዬ!!!
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የቢድዓ መልካም አለውን
💡ቢድዓ መስራት በውስጡ የያዘው ከባድ መልክት
💡ቢድዓ የሚሰሩ ሰዎች ግን ይህን መልእክት አስበውበታል?
💡የዑመር ኢብኑል ኸጣብን ንግግር መረጃ አድርገው የሚያቀርቡ ሰዎች ይህን ሳይሰሙ እንዳታልፉ!
💡ኢማሙ ማሊክ ስለ ቢድዓ ያሉትን ሰምተክ ታውቃለህን?
💡በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ
💡ቢድዓ መስራት በውስጡ የያዘው ከባድ መልክት
💡ቢድዓ የሚሰሩ ሰዎች ግን ይህን መልእክት አስበውበታል?
💡የዑመር ኢብኑል ኸጣብን ንግግር መረጃ አድርገው የሚያቀርቡ ሰዎች ይህን ሳይሰሙ እንዳታልፉ!
💡ኢማሙ ማሊክ ስለ ቢድዓ ያሉትን ሰምተክ ታውቃለህን?
💡በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ
አስገራሚ ቂሷ❗️
ዒሻእ ሰላት ተሰግዶ ጥቂት ደቂቃዎች እንዳለፉ አንድ ወጣት ከወደ ውጭ በኩል ይጮህና የመስጅዱን ጀማዓ ይጠራል።ሰዉ ግር ብሎ ልጁን ተከትሎ ሲወጣ አንድ እድሜው 20 ማይሞላ ልጅ ባቡር ገጭቶት አካሉን ለሁለት ከፍሎታል (ሱብሀን አላህ) ግን ሩሁ አልወጣችም ሊሞት ጣር ላይ ነበር በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለ ከተሰበሰቡት አንዱ ጎንበስ ብሎ የልጁን ጭንቅላት በእግሩ ላይ አስቀመጠው።
"ላ ኢላሀ ኢለላህ በል... ላ ኢላሀ ኢለላህ በል"
ይለውም ጀመር...
ልጁ ሩሁ ልትወጣ ጥድፊያ ላይ ናት ይፈራገጣል...እናም የአላህ ተውፊቅ ሆነና
ልጁ " ላ ኢላሀ ኢለላህ ሙሀመዱን ረሱሉላህ" እንዳለ ሰውነቱ ቀዘቀዘ ትንፋሹ ዳግም ላይመለስ ተቋረጠ ነፍሱም ወደ ፈጣሪዋ አመራች።
(ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን)
ተባብረው ልጁን ሰዎች ወደሚበዙበት አካባቢ ወሰዱት ቤተሰቡን ለማፈላለግ...
ሌሊቱ ጨለማማ ነበር ፅልመቱ ያስፈራል ብርሀናማ ቦታ ሁነው ልጁን የሚገልፁ ነገሮችን ልብሶቹን በመጠቀም ቤተሰቡን ያፈላልጉ ጀመር...
ድንገት በቦታው ከነበሩት አንዱ የአስክሬኑን እጅ ይዞ ፦"ይህ ልጅ ክርስቲያን ነው አንገቱ ላይ መስቀል ይኸው..." እያለ ጮኸ።
ሁሉም ግራ ተጋባ "ይህ ልጅ በተውሂድ ነው የሞተው ታድያ እኛው በሙስሊሞች መቃብር እንቅበረው ወይስ ለቤተሰቦቹ አስረክበን በክርስቲያኖች መቃብር ይቅበሩት?"
እያሉ ይወያዩ ጀመር..
ቤተስቦቹ ጋ ለመውሰድ ይወስኑና ተሸክመውት በእንባ ወደቤተሰቦቹ ጉዞ ጀመሩ።
ልጁ መስጅድ አካባቢ ስለሞተ አስክሬኑን ያጀቡት ሁሉም ሙስሊሞች ነበሩ።
ተሸክመውት ከአከባቢው ሲደርሱ አባቱም የልጁን ማረፍ ሰምቶ ሲገሰግስ አገኙት አባትየውም ሲያያቸው ተንሰቅስቆ ያለቅስ ጀመር (እንዴት አያልቅስ ተስፋ ይሆነኛል፣ረዳት ይሆነኛል፣መመኪያ ይሆነኛል ብሎ የሚጠብቀው ልጁ ከሰዎች ትከሻ ላይ ተጭኖ ሲመጣለት...)
ልጁን አቅፎ አምርሮ ያለቅሳል...
ይህ ሁሉ ሙስሊም ልጁን ተሸክሞ መምጣቱ ያስገረመው አባት እያለቀሰ ለተሰበሰበው ሰው እንዲህ አላቸው፦
"ይህን ስነግራችሁ በህፍረት ነው...ልጄ እንዲው ቁርአን መስማት ይወዳል። አዎ ልጄ በርግጥ ክርስቲያን ነው ነገር ግን የሙስሊሞችን ቁርአን መስማት ይወዳል።
ዘውትር ክፍሉ ስገባ ኢርፎን/earphone ከጆሮው አያለው...
"ምንድነው ምትሰማው?" ስለው
"ዘፈን ነው"ይለኛል
ከጆሮው ነቅዬ ሳዳምጥ ግን ቁርአን ነው።
በጣምም እቆጣው ነበር
ይሄን መስማት ካልተውክ እገድልሀለሁ እያልኩ ሁሌም አስጠነቅቀውም ነበር...
"ባባ እኔን መግደል አትችልም ቁርአን መስማትም አትከልክለኝ" ይለኝ ነበር..
በቦታው ያሉት ሁሉ እየተያዩ ይለቃቀሱ ነበር።
"ልጅህ እኮ በሸሀዳ ነው የሞተው" ብለው ሲነግሩት...ያ የልጁ መሞት ቅስሙን የሰበረው አባት ያ የልጁን ሬሳ አቅፎ ቁጭ ያለው አባት
እንባውን እያረገፈ ልጁን በስስት እያየ እንዲህ አለ፦
"ልጄ በመሰከረው ነገር እኔም እመሰክራለሁ ከአላህ ሌላ አምላክ እንደሌለ ሙሀመድም የ አላህ መልዕክተኛ እንደሆኑ እመስክራለሁ"
ከዚያም ሁሉም ጀማዓ ጀናዛውን ይዘው ወደ ሙስሊሞች መቃብር "ላ ኢላሀ ኢለላህ... ላ ኢላሀ ኢለላህ.... ላ ኢላሀ ኢለላህ" እያሉ አጅበው ወስደው ቀበሩት።
__________________________
ሙስሊም ሆኖ ኖሮ በኩፍር መሞትም አለና ካፊር ሆኖ ኖሮ በተውሂድ መሞትም አለና "አላህ ካቲማችንን ያሳምርልን"
ምንጭ፦ ﻫﻨﺎ ﺃﺑﻨﺎﺀ ﻋﺎﺋﺸﺔ ﺃﻡ ﺍﻟﻤﺆﻣﻨ
ዒሻእ ሰላት ተሰግዶ ጥቂት ደቂቃዎች እንዳለፉ አንድ ወጣት ከወደ ውጭ በኩል ይጮህና የመስጅዱን ጀማዓ ይጠራል።ሰዉ ግር ብሎ ልጁን ተከትሎ ሲወጣ አንድ እድሜው 20 ማይሞላ ልጅ ባቡር ገጭቶት አካሉን ለሁለት ከፍሎታል (ሱብሀን አላህ) ግን ሩሁ አልወጣችም ሊሞት ጣር ላይ ነበር በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለ ከተሰበሰቡት አንዱ ጎንበስ ብሎ የልጁን ጭንቅላት በእግሩ ላይ አስቀመጠው።
"ላ ኢላሀ ኢለላህ በል... ላ ኢላሀ ኢለላህ በል"
ይለውም ጀመር...
ልጁ ሩሁ ልትወጣ ጥድፊያ ላይ ናት ይፈራገጣል...እናም የአላህ ተውፊቅ ሆነና
ልጁ " ላ ኢላሀ ኢለላህ ሙሀመዱን ረሱሉላህ" እንዳለ ሰውነቱ ቀዘቀዘ ትንፋሹ ዳግም ላይመለስ ተቋረጠ ነፍሱም ወደ ፈጣሪዋ አመራች።
(ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን)
ተባብረው ልጁን ሰዎች ወደሚበዙበት አካባቢ ወሰዱት ቤተሰቡን ለማፈላለግ...
ሌሊቱ ጨለማማ ነበር ፅልመቱ ያስፈራል ብርሀናማ ቦታ ሁነው ልጁን የሚገልፁ ነገሮችን ልብሶቹን በመጠቀም ቤተሰቡን ያፈላልጉ ጀመር...
ድንገት በቦታው ከነበሩት አንዱ የአስክሬኑን እጅ ይዞ ፦"ይህ ልጅ ክርስቲያን ነው አንገቱ ላይ መስቀል ይኸው..." እያለ ጮኸ።
ሁሉም ግራ ተጋባ "ይህ ልጅ በተውሂድ ነው የሞተው ታድያ እኛው በሙስሊሞች መቃብር እንቅበረው ወይስ ለቤተሰቦቹ አስረክበን በክርስቲያኖች መቃብር ይቅበሩት?"
እያሉ ይወያዩ ጀመር..
ቤተስቦቹ ጋ ለመውሰድ ይወስኑና ተሸክመውት በእንባ ወደቤተሰቦቹ ጉዞ ጀመሩ።
ልጁ መስጅድ አካባቢ ስለሞተ አስክሬኑን ያጀቡት ሁሉም ሙስሊሞች ነበሩ።
ተሸክመውት ከአከባቢው ሲደርሱ አባቱም የልጁን ማረፍ ሰምቶ ሲገሰግስ አገኙት አባትየውም ሲያያቸው ተንሰቅስቆ ያለቅስ ጀመር (እንዴት አያልቅስ ተስፋ ይሆነኛል፣ረዳት ይሆነኛል፣መመኪያ ይሆነኛል ብሎ የሚጠብቀው ልጁ ከሰዎች ትከሻ ላይ ተጭኖ ሲመጣለት...)
ልጁን አቅፎ አምርሮ ያለቅሳል...
ይህ ሁሉ ሙስሊም ልጁን ተሸክሞ መምጣቱ ያስገረመው አባት እያለቀሰ ለተሰበሰበው ሰው እንዲህ አላቸው፦
"ይህን ስነግራችሁ በህፍረት ነው...ልጄ እንዲው ቁርአን መስማት ይወዳል። አዎ ልጄ በርግጥ ክርስቲያን ነው ነገር ግን የሙስሊሞችን ቁርአን መስማት ይወዳል።
ዘውትር ክፍሉ ስገባ ኢርፎን/earphone ከጆሮው አያለው...
"ምንድነው ምትሰማው?" ስለው
"ዘፈን ነው"ይለኛል
ከጆሮው ነቅዬ ሳዳምጥ ግን ቁርአን ነው።
በጣምም እቆጣው ነበር
ይሄን መስማት ካልተውክ እገድልሀለሁ እያልኩ ሁሌም አስጠነቅቀውም ነበር...
"ባባ እኔን መግደል አትችልም ቁርአን መስማትም አትከልክለኝ" ይለኝ ነበር..
በቦታው ያሉት ሁሉ እየተያዩ ይለቃቀሱ ነበር።
"ልጅህ እኮ በሸሀዳ ነው የሞተው" ብለው ሲነግሩት...ያ የልጁ መሞት ቅስሙን የሰበረው አባት ያ የልጁን ሬሳ አቅፎ ቁጭ ያለው አባት
እንባውን እያረገፈ ልጁን በስስት እያየ እንዲህ አለ፦
"ልጄ በመሰከረው ነገር እኔም እመሰክራለሁ ከአላህ ሌላ አምላክ እንደሌለ ሙሀመድም የ አላህ መልዕክተኛ እንደሆኑ እመስክራለሁ"
ከዚያም ሁሉም ጀማዓ ጀናዛውን ይዘው ወደ ሙስሊሞች መቃብር "ላ ኢላሀ ኢለላህ... ላ ኢላሀ ኢለላህ.... ላ ኢላሀ ኢለላህ" እያሉ አጅበው ወስደው ቀበሩት።
__________________________
ሙስሊም ሆኖ ኖሮ በኩፍር መሞትም አለና ካፊር ሆኖ ኖሮ በተውሂድ መሞትም አለና "አላህ ካቲማችንን ያሳምርልን"
ምንጭ፦ ﻫﻨﺎ ﺃﺑﻨﺎﺀ ﻋﺎﺋﺸﺔ ﺃﻡ ﺍﻟﻤﺆﻣﻨ
➧መልካም ጓደኛ
➫➫➫➫➫➫
➻ሁለት ውብ የሂወት ኡደቶችን ይለግሰሀል… "አንደኛው እዚህ ዱንያ ላይ ሲሆን" "ሁለተኛው ደግሞ ጀነት ውስጥ ይሆናል"
➧መልካም ጓደኞች «ወደ አሏህ መንገድ… ይጠሩሀል…» «ከጠፋህባቸው… ይፈልጉሀል…» ከተዘናጋህ… አስታውሱሀል»
«…በዱአቸው ውስጥ…ያካቱሀል»
«ልክ እንደ ከዋክብቶች… መርከብህ መንገድ ከሳተች…ይመሩሀል…» «ነገ ከአሏህ አርሽ ስር…ኢንሸአላህ…ይጠብቁሀል…» «ጀነት ውስጥ ፈልገውህ ካጡህ…
➧አሏህን ወደነሱ እንዲቀላቅልህ ይለምኑልሀል» "አሏህ ሶሊሆቹን አድርጎ ከሶሊሆቹ ያወዳጀን ከሶሊሆቹ ጓደኞቻችን አይነጥለን በያሉበት ይጠብቅልን "
#መንቁል
➛ያአላህ ምንኛ መታደል ነው እንደዚህ አይነት ጓደኛ ማገኘት አላህ ይወፍቀን እኛንም መልካሞች ያድርገን!!
➫➫➫➫➫➫
➻ሁለት ውብ የሂወት ኡደቶችን ይለግሰሀል… "አንደኛው እዚህ ዱንያ ላይ ሲሆን" "ሁለተኛው ደግሞ ጀነት ውስጥ ይሆናል"
➧መልካም ጓደኞች «ወደ አሏህ መንገድ… ይጠሩሀል…» «ከጠፋህባቸው… ይፈልጉሀል…» ከተዘናጋህ… አስታውሱሀል»
«…በዱአቸው ውስጥ…ያካቱሀል»
«ልክ እንደ ከዋክብቶች… መርከብህ መንገድ ከሳተች…ይመሩሀል…» «ነገ ከአሏህ አርሽ ስር…ኢንሸአላህ…ይጠብቁሀል…» «ጀነት ውስጥ ፈልገውህ ካጡህ…
➧አሏህን ወደነሱ እንዲቀላቅልህ ይለምኑልሀል» "አሏህ ሶሊሆቹን አድርጎ ከሶሊሆቹ ያወዳጀን ከሶሊሆቹ ጓደኞቻችን አይነጥለን በያሉበት ይጠብቅልን "
#መንቁል
➛ያአላህ ምንኛ መታደል ነው እንደዚህ አይነት ጓደኛ ማገኘት አላህ ይወፍቀን እኛንም መልካሞች ያድርገን!!
ኢላሒ ሰትረን‼
ኢብኑ አል-ቀይም "በሆነ ወንጀል ሰውን ያነወረ ሰው ያንን ወንጀል ሳይሰራው አይሞትም" ይላሉ።
መሳደብም ሆነ መሳለቅ መልካም አይደለም። ሰውን መሠተር ነው እንጂ ማዋረድ ትርፍ የለው።
...
ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ደግሞ
"በውሻ ባሾፍ እንኳ ውሻ እንዳልሆን ብዬ እፈራለሁ፡፡"
.
ደጋጎችና ጥንቁቆቹ እንዲህ ናቸው። በሰው ነውር ላይ ሙድ አይዙም፤ አላህ በፈተነው ሰው አያላግጡም፣ በአፈጣጠሩም ሆነ በእንከኑ አያሾፉም፣ ያጠፋውን ቀርበው ይመክሩታል እንጂ አያሙትም፣ አይስቁበትም።
...
ሷሊሖቹ ሰዎች የጠፉት እንዴት እንደጠፉ ሳይሆን ነጃ የወጡት እንዴት ነጃ እንደወጡ ነው ጭንቀታቸው። ዛሬ በሰው ወንጀል የምትስቁ ነገስ እናንተ ላለመሥራታችሁ ምን ዋስትና አላችሁ!!
አላህ ይሠትረን።
ኢብኑ አል-ቀይም "በሆነ ወንጀል ሰውን ያነወረ ሰው ያንን ወንጀል ሳይሰራው አይሞትም" ይላሉ።
መሳደብም ሆነ መሳለቅ መልካም አይደለም። ሰውን መሠተር ነው እንጂ ማዋረድ ትርፍ የለው።
...
ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ደግሞ
"በውሻ ባሾፍ እንኳ ውሻ እንዳልሆን ብዬ እፈራለሁ፡፡"
.
ደጋጎችና ጥንቁቆቹ እንዲህ ናቸው። በሰው ነውር ላይ ሙድ አይዙም፤ አላህ በፈተነው ሰው አያላግጡም፣ በአፈጣጠሩም ሆነ በእንከኑ አያሾፉም፣ ያጠፋውን ቀርበው ይመክሩታል እንጂ አያሙትም፣ አይስቁበትም።
...
ሷሊሖቹ ሰዎች የጠፉት እንዴት እንደጠፉ ሳይሆን ነጃ የወጡት እንዴት ነጃ እንደወጡ ነው ጭንቀታቸው። ዛሬ በሰው ወንጀል የምትስቁ ነገስ እናንተ ላለመሥራታችሁ ምን ዋስትና አላችሁ!!
አላህ ይሠትረን።
▪️ከሰለፎች ውስጥ አንዱ እንዲህ ብሏል።
♦️ሁለት ነገሮች፦
①) ሞትንና
②) አላህ ፊት መቆምን ማስታወስ
የዱንያን ጥፍጥና ቆርጠውልኛል፦
📚 لطائف المعارف [244]
♦️ሁለት ነገሮች፦
①) ሞትንና
②) አላህ ፊት መቆምን ማስታወስ
የዱንያን ጥፍጥና ቆርጠውልኛል፦
📚 لطائف المعارف [244]
▪️ቢሽር ቢን አልሀሪስ አላህ ይዘንለትና እንዲህ አሉ።
✅ ሰዎች ዘንድ እንድትወሳ ብለህ ምንም አትስራ። መጥፎ ስራህን (ሰዎች እንዳያውቁብህ) እንደምትደብቀው ሁሉ መልካም ስራህንም ደብቅ።
📚 [ سير اعلام النبلاء ]
✅ ሰዎች ዘንድ እንድትወሳ ብለህ ምንም አትስራ። መጥፎ ስራህን (ሰዎች እንዳያውቁብህ) እንደምትደብቀው ሁሉ መልካም ስራህንም ደብቅ።
📚 [ سير اعلام النبلاء ]
◾️ኢብኑ ኡሰይሚን አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል።
✅ አንድ ሴት ሸሪአዊ በሆነ መልኩ ሊያጫት ፈልጎ ሊያያት ለሚመጣ ሰው ሜካፓችን መጠቀም አይፈቀድላትም። ምክንያቱም ይህ ነገር ማታለልና የፊት ማጭበርበር ነው።
📚فتاوى نور على الدرب
✅ አንድ ሴት ሸሪአዊ በሆነ መልኩ ሊያጫት ፈልጎ ሊያያት ለሚመጣ ሰው ሜካፓችን መጠቀም አይፈቀድላትም። ምክንያቱም ይህ ነገር ማታለልና የፊት ማጭበርበር ነው።
📚فتاوى نور على الدرب
🟣 ዱንያን መተው ማለት
ብዙ ሰዎች ዱንያን መተው ማለት ደረቅ ነገር መመገብና ሸካራ ነገርን መልበስ ንፅህናን አለመጠበቅ ራስን መጣል አድረገው ይገምታሉ ይህ እይታ ስህተት መሆኑን ታላቁ ታብዕይ ሱፍያን አስሰውርይ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : –
قال سفيان الثوري رحمه الله تعالى :
" ليس الزهد بأكل الغليظ، ولبس الخشِن، ولكنّه قِصَر الأمل، وارتقاب الموت".
(سير أعلام النبلاء: ٦/٦٣٠)
" ዙህድ ( ዱንያን መተው ማለት ) ጠንካራ ነገር መብላትና ሸካራ ነገር በመልበስ አይደለም ።
ነገር ግን ዙህድ ማለት ምኞትን ማሳጠርና ሞትን መጠባበቅ ነው " ።
ሲየር አዕላሙ ኑበላእ ( 630 / 6 )
ብዙ ሰዎች ዱንያን መተው ማለት ደረቅ ነገር መመገብና ሸካራ ነገርን መልበስ ንፅህናን አለመጠበቅ ራስን መጣል አድረገው ይገምታሉ ይህ እይታ ስህተት መሆኑን ታላቁ ታብዕይ ሱፍያን አስሰውርይ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : –
قال سفيان الثوري رحمه الله تعالى :
" ليس الزهد بأكل الغليظ، ولبس الخشِن، ولكنّه قِصَر الأمل، وارتقاب الموت".
(سير أعلام النبلاء: ٦/٦٣٠)
" ዙህድ ( ዱንያን መተው ማለት ) ጠንካራ ነገር መብላትና ሸካራ ነገር በመልበስ አይደለም ።
ነገር ግን ዙህድ ማለት ምኞትን ማሳጠርና ሞትን መጠባበቅ ነው " ።
ሲየር አዕላሙ ኑበላእ ( 630 / 6 )
🌺
አቡበክር አስሰዲቅ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦
"እናንተ ሰዎች ሆይ! የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ ታነባላችሁ፡-
{ﻳَﺎ ﺃَﻳُّﻬَﺎ اﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮا ﻋَﻠَﻴْﻜُﻢْ ﺃَﻧﻔُﺴَﻜُﻢْ ۖ ﻻَ ﻳَﻀُﺮُّﻛُﻢ ﻣَّﻦ ﺿَﻞَّ ﺇِﺫَا اﻫْﺘَﺪَﻳْﺘُﻢ... }
{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁን (ከእሳት) ያዙ፤ (ጠብቁ)። በተመራችሁ ጊዜ የተሳሳተ ሰው አይጎዳችሁም…}5:105
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦
{ሰዎች ግፈኛን እየተመለከቱ (ከግፍ ተግባር እንዲቆጠብ) እጁን ካሊያዙት አላህ አጠቃላይ ቅጣት ያወርድባቸዋል ሲሉ አድምጫለሁ}
ቲርሙዚይ ዘግቦታ
አቡበክር አስሰዲቅ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦
"እናንተ ሰዎች ሆይ! የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ ታነባላችሁ፡-
{ﻳَﺎ ﺃَﻳُّﻬَﺎ اﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮا ﻋَﻠَﻴْﻜُﻢْ ﺃَﻧﻔُﺴَﻜُﻢْ ۖ ﻻَ ﻳَﻀُﺮُّﻛُﻢ ﻣَّﻦ ﺿَﻞَّ ﺇِﺫَا اﻫْﺘَﺪَﻳْﺘُﻢ... }
{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁን (ከእሳት) ያዙ፤ (ጠብቁ)። በተመራችሁ ጊዜ የተሳሳተ ሰው አይጎዳችሁም…}5:105
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦
{ሰዎች ግፈኛን እየተመለከቱ (ከግፍ ተግባር እንዲቆጠብ) እጁን ካሊያዙት አላህ አጠቃላይ ቅጣት ያወርድባቸዋል ሲሉ አድምጫለሁ}
ቲርሙዚይ ዘግቦታ
ዐብደላህ ኢብን ዐምር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ ነቢይ እንዲህ ብለዋል፡- ሙስሊም የሚባለው በምላሱና በእጁ ሙስሊሞችን ከመጉዳት የታቀበ (ነፃ የሆነ) ሰው ነው፡፡ ‹‹ሙሃጂር›› (ስደተኛ) የሚባለው ደግሞ አላህ የከለከለውን ነገር ሁሉ የተወ ነው፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል)
(ቡኻሪ ዘግበውታል)
💜 ከምትጠላው ነገር አላህ ሲያድንህ
ሱብሂ/ፈጅር ሰላትን ስለሰገድኩ ነው ፣
ሰደቃ ስለሰጠሁ ነው ፣ ዚክር ማዘውተሬ ነው
ወይም ጥሩ ጥሩ ስለማስብ ነው አትበል‥
⇘ አላህ በእዝነቱ አዳነኝ ብለህ አመስግን ።
(فَلَمَّا جَاءَ أَمْرُنَا نَجَّيْنَا صَالِحًا وَالَّذِينَ آمَنُوا مَعَهُ بِرَحْمَةٍ مِنَّا)
" ትዕዛዛችንም በመጣ ጊዜ ሷሊህንና እነዚያን ከሱ ጋር ያመኑትን ከእኛ በሆነው እዝነት አዳን ። "
[ሁድ 66]
ሱብሂ/ፈጅር ሰላትን ስለሰገድኩ ነው ፣
ሰደቃ ስለሰጠሁ ነው ፣ ዚክር ማዘውተሬ ነው
ወይም ጥሩ ጥሩ ስለማስብ ነው አትበል‥
⇘ አላህ በእዝነቱ አዳነኝ ብለህ አመስግን ።
(فَلَمَّا جَاءَ أَمْرُنَا نَجَّيْنَا صَالِحًا وَالَّذِينَ آمَنُوا مَعَهُ بِرَحْمَةٍ مِنَّا)
" ትዕዛዛችንም በመጣ ጊዜ ሷሊህንና እነዚያን ከሱ ጋር ያመኑትን ከእኛ በሆነው እዝነት አዳን ። "
[ሁድ 66]
💚 ህይወት የፈለገ ያህል ከባድ
ጭንቀተማና አድካሚ ብትሆንም
ሁለት ደስ የሚሉ ጣእምን የሚሰጧት
ነገሮች አሉ ‥ እንሱም
⇘ አላህን ማውሳት እና ለአላህ ብሎ
ከሚወድህ ልብ የሚመጣልህ ዱዓእ ነው ።
ጭንቀተማና አድካሚ ብትሆንም
ሁለት ደስ የሚሉ ጣእምን የሚሰጧት
ነገሮች አሉ ‥ እንሱም
⇘ አላህን ማውሳት እና ለአላህ ብሎ
ከሚወድህ ልብ የሚመጣልህ ዱዓእ ነው ።
አቡ ሙሳ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ሶስት ሰዎች ድርብ ሽልማት ይኖራቸዋል፡-
1) የመጻሐፍቱ ባለቤት (ክርስቲያን ወይም አይሁድ) ሆኖ ሳለ በተላከለት ነቢይ (በኢየሱስ ወይም በሙሴ) ያመነና በሙሐመድ ያመነ፡፡
2) የአላህንና የአሳዳሪውን ሐቅ የሚጠብቅ ባሪያ
3) ሴት ባሪያውን መልካም ስነ ምግባርና ጥሩ ትምህርት ካስተማረ በኋላ ነፃ በማውጣት ያገባ፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል)
1) የመጻሐፍቱ ባለቤት (ክርስቲያን ወይም አይሁድ) ሆኖ ሳለ በተላከለት ነቢይ (በኢየሱስ ወይም በሙሴ) ያመነና በሙሐመድ ያመነ፡፡
2) የአላህንና የአሳዳሪውን ሐቅ የሚጠብቅ ባሪያ
3) ሴት ባሪያውን መልካም ስነ ምግባርና ጥሩ ትምህርት ካስተማረ በኋላ ነፃ በማውጣት ያገባ፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል)
አውፍ እንባባል
ጥቂት ቀናት ቀረው ረመዳን ሊገባ
እርስ በርሳችንም ይኑረን ሙሀባ
ነሻጣም ይኑረን እንዳንሆን ጀዝባ
ተውበትንም እናርግ ረመዳን መጥቷል
አሁን ወዲያው ፈጥነን አውፍ እንባባል
በቅድሚያም ከራሴ እኔ እጀምራለው
ላስቀየሙኝን ሰዎች አውፈን ብያለው
አውፍ በዮችን ይወዳል ጌታችሁ
አውፍ በሉኝ እኔን ለአላህ ብለችሁ
ስሙንም እንስቼ እኔ ካማሁት
የሰውነት ክብሩን ከነካሁበት
አውፈን ይበለኝ በጥቂት ቃላት
ጥቂት ቀናት ቀረው ረመዳን ሊገባ
እርስ በርሳችንም ይኑረን ሙሀባ
ነሻጣም ይኑረን እንዳንሆን ጀዝባ
ተውበትንም እናርግ ረመዳን መጥቷል
አሁን ወዲያው ፈጥነን አውፍ እንባባል
በቅድሚያም ከራሴ እኔ እጀምራለው
ላስቀየሙኝን ሰዎች አውፈን ብያለው
አውፍ በዮችን ይወዳል ጌታችሁ
አውፍ በሉኝ እኔን ለአላህ ብለችሁ
ስሙንም እንስቼ እኔ ካማሁት
የሰውነት ክብሩን ከነካሁበት
አውፈን ይበለኝ በጥቂት ቃላት
💍::::::::::ትዳር /ጋብቻ:::: 💍
✍" ከናንተ መካከል በላጩ ሰው ለሚስቱ መልካም የሆነ ነው"
❥ነብዩ ስለላሁ አለይሂወሰለም ❥
💍 ኒካህ በማሰር ትዳር በመመስረት አላህን ታዘዙ ቃል የገባላችሁን ይሰጣችኋልና....💯💯
💍ጋብቻ በኔ ዘንድ የሚወደድ ተግባር ነው እኔ ለምወደው ነገር ጀርባውን የሰጠ ለኔ ጀርባውን እንደሰጠ ይቆጠራል "🚫
☞❥ብለዋል ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም.
👉 ከራሳችሁ የሆነችን ተጣማሪ ትረኩበት ዘንድ ማድረጉ ከታአምራቶቹ አንዱ ነው።👌
☞❥ 💍 ሚስትህን ውደዳት ጊዜም ሰጥተህ አስደስታት ግማሽ ዲንህን የምትሞላበትን ቀን መቸውም ቢሆን አትዘንጋ እርሷ #ሚስትህ ብቻ ሳትሆን ከአራህማን የተሰጠችህ ንግስናህ ነችና።
☞☞💍 ውዷ እህቴ አንችም ብትሆኝ ባልን ማክበርና መታዘዝና የአላህንና የረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ትዛዝን ከመጠበቅ ይቆጠራልና ለባልሽ መልካም ሁኚ።
❥☞አላህ የባሎችንም ሆነ የሚስቶችን ሀቅ ጠባቂወች ያድርገን... አሚን 🤲🤲
☞☞አላህ መልካምን ትዳር ይወፍቃችሁ.....አሚን
🤲🤲ኧረ አሚን በሉ💍 ከወደዱት #ሼር_ያድርጉ
✍" ከናንተ መካከል በላጩ ሰው ለሚስቱ መልካም የሆነ ነው"
❥ነብዩ ስለላሁ አለይሂወሰለም ❥
💍 ኒካህ በማሰር ትዳር በመመስረት አላህን ታዘዙ ቃል የገባላችሁን ይሰጣችኋልና....💯💯
💍ጋብቻ በኔ ዘንድ የሚወደድ ተግባር ነው እኔ ለምወደው ነገር ጀርባውን የሰጠ ለኔ ጀርባውን እንደሰጠ ይቆጠራል "🚫
☞❥ብለዋል ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም.
👉 ከራሳችሁ የሆነችን ተጣማሪ ትረኩበት ዘንድ ማድረጉ ከታአምራቶቹ አንዱ ነው።👌
☞❥ 💍 ሚስትህን ውደዳት ጊዜም ሰጥተህ አስደስታት ግማሽ ዲንህን የምትሞላበትን ቀን መቸውም ቢሆን አትዘንጋ እርሷ #ሚስትህ ብቻ ሳትሆን ከአራህማን የተሰጠችህ ንግስናህ ነችና።
☞☞💍 ውዷ እህቴ አንችም ብትሆኝ ባልን ማክበርና መታዘዝና የአላህንና የረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ትዛዝን ከመጠበቅ ይቆጠራልና ለባልሽ መልካም ሁኚ።
❥☞አላህ የባሎችንም ሆነ የሚስቶችን ሀቅ ጠባቂወች ያድርገን... አሚን 🤲🤲
☞☞አላህ መልካምን ትዳር ይወፍቃችሁ.....አሚን
🤲🤲ኧረ አሚን በሉ💍 ከወደዱት #ሼር_ያድርጉ
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከረጀብ ወር ጋር የሚያያዙ ደካማ ሐዲሦች
~~~
ከረጀብ ጋር ብዙ መሰረተ ቢስ ቅጥፈቶችና ደካማ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦
[1ኛ]፡-
رجب شهر الله وشعبان شهري ورمضان شهر أمتي
“ረጀብ የአላህ ወር ነው። ሸዕባን የኔ ወር ነው። ረመዷን ደግሞ የህዝቦቼ ወር ነው።” አልባኒ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ፡ 4400]
[2ኛ]፡- ረጀብ ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር፡-
اللهم بارك لنا في رجب وشعبان، وبلغنا رمضان
“አላህ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን። ረመዷንን አድርሰን።” ነወዊይ በ“አዝካር”፣ ዘሀቢይ በ“ሚዛን” ደካማ እንደሆነ ብይን የሰጡ ሲሆን አልባኒም “ደካማ ነው” ብለዋል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 4395]
[3ኛ]፡-
فضل شهر رجب على الشهور كفضل القرآن على سائر الكلام
“የረጀብ ወር በሌሎች ወራት ላይ ያለው ብልጫ ቁርኣን በሌሎች ንግግሮች ላይ እንዳለው ብልጫ ነው።” ኢብኑ ሐጀር “መሰረተ ቢስ ቅጥፈት ነው ብለዋል።
[4ኛ]፡-
خمس ليال لا ترد فيهن الدعوة أول ليلة من رجب، وليلة النصف من شعبان، وليلة الجمعة، وليلة الفطر، وليلة النحر
“አምስት ሌሊቶች በነሱ ውስጥ የተደረገ ዱዓእ አይመለስም። የመጀመሪያው የረጀብ ሌሊት፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት፣ የጁሙዐ ሌሊት፣ የዒደል ፊጥር ሌሊት እና የዒደል አድሓ ሌሊት ናቸው።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 1452] [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 2852]
[5ኛ]፡-
رجب شهر عظيم يضاعف الله فيه الحسنات، فمن صام يوما من رجب، فكأنما صام سنة، ومن صام منه سبعة أيام، غلقت عنه سبعة أبواب جهنم، ومن صام منه ثمانية أيام، فتحت له ثمانية أبواب الجنة، ومن صام منه عشرة أيام، لم يسأل الله شيئا إلا أعطاه إياه، …
“ረጀብ አላህ መልካም ምንዳዎችን የሚያነባብርበት ታላቅ ወር ነው። ከረጀብ አንድ ወር የፆመ ሰው አመት እንደፆመ ነው። ከሱ ሰባት ቀናትን የፆመ ሰባቱ የጀሀነም በሮች ይዘጉለታል። ከሱ ስምንት ቀናትን የፆመ ስምንቱ የጀነት በሮች ይከፈቱለታል። ከሱ አስር ቀናትን የፆመ አላህን የሆነ ነገር አይጠይቅም፣ እሱኑ የሰጠው ቢሆን እንጂ፣ …” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 5413]
[6ኛ]፡-
إن في الجنة نهرا يقال له رجب ماؤه أشد بياضا من اللبن وأحلى من العسل من صام يوما من رجب سقاه الله من ذلك النهر
“በጀነት ውስጥ ረጀብ የሚባል ወንዝ አለ። ውሃው ከወተት የነጣ፣ ከማር የጣፈጠ ነው። ከረጀብ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ ከዚያ ወንዝ ያጠጣዋል።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 1902]
[7ኛ]፡-
صوم أول يوم من رجب كفارة ثلاث سنين، والثاني كفارة سنتين، والثالث كفارة سنة، ثم كل يوم شهرا
“የረጀብን የመጀመሪያ ቀን መፆም የሶስት አመት ወንጀል ያብሳል። ሁለተኛው የሁለት አመት ያብሳል። ሶስተኛው ደግሞ የአመት ያብሳል። ከዚያም እያንዳንዱ ቀን የወር ነው።” አልባኒ ደካማ ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 3500፣ 5649]
[8ኛ]፡-
لا تغفلوا عن أول جمعة من رجب فإنها ليلة تسميها الملائكة الرغائب
“ከረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐ አትዘናጉ። እርሷ መላእክት ‘አረጋኢብ’ ብለው የሚጠሯት ሌሊት ነች።”
‘ሶላተ ረጋኢብን’ በተመለከተ ነወዊይ እንዲህ ብለዋል፡- “እርሷን የፈጠረን ሰው አላህ ይርገመው! እርሷ አስቀያሚ ቢድዐ ነች!” [ሸርሑ ሙስሊም] በተጨማሪም እሷንና የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሶላትን አስመልክተው “… ቢድዐና አስቀያሚ ፈጠራዎች ናቸው። በ‘ቁቱል ቁሉብ’፣ ‘ኢሕያእ ዑለሚዲን’ ኪታብ ውስጥ ስለተጠቀሱ ማንም እንዳይሸወድ። እነሱን በሚጠቁመው ሐዲሥም እንዲሁ (እንዳይሸወድ)። ምክንያቱም ሁሉም ውድቅ ነውና” ብለዋል። [አልመጅሙዕ፡ 3/548]
[9ኛ]፡-
أن رسول الله -ﷺ- لم يصم بعد رمضان إلا رجبًا وشعبان
“የአላህ መልእክተኛ ከረመዷን በኋላ ረጀብንና ሸዕባንን እንጂ አልፆሙም።” ኢብኑ ሐጀር በጣም ደካማ ነው ብለውታል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 12]
[10ኛ]፡-
من صلى المغرب في أول ليلة من رجب ثم صلى بعدها عشرين ركعة يقرأ في كل ركعة بفاتحة الكتاب، وقل هو الله أحد مرة، ويسلم فيهن عشر تسليمات، أتدرون ما ثوابه؟ قال: حفظه الله في نفسه وأهله وماله وولده، وأجير من عذاب القبر، وجاز الصراط كالبرق بغير حساب ولا عذاب
“በረጀብ የመጀመሪያ ሌሊት መግሪብን ሰግዶ ከዚያም በእያዳንዷ ረከዐ ፋቲሐንና ቁል ሁላሁ አሐድን አንድ ጊዜ እየቀራ፣ በአስር ተስሊማት እያሰላመተ ሃያ ረከዐ የሰገደ ሰው ምንዳው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አላህ በነፍሱም፣ በቤተሰቡም፣ በገንዘቡም፣ በልጁም ይጠብቀዋል። ከቀብር ቅጣትም ይጠበቃል። ሲራጥንም ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት እንደ ብልጭታ ያቋርጧል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/123] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 20]
[11ኛ]፡-
من صام من رجب وصلى فيه أربع ركعات ... لم يمت حتى يرى مقعده من الجنة أو يُرى له
“ከረጀብ ፁሞ፣ በሱ ውስጥ አራት ረከዓዎችን የሰገደ ሰው … በጀነት ውስጥ መቀመጫውን ሳያይ ወይም ሳይታይለት አይሞትም።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/124] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 21]
[12ኛ]፡-
إن شهر رجب شهر عظيم، من صام منه يومًا كتب الله له صوم ألف سنة ...
“የረጀብ ወር ታላቅ ወር ነው። ከሱ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ አንድ ሺ አመት ፆም ይመዘግብለታል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/206-207] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 26]
ከረጀብ ጋር የሚያያዙት ዘገባዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም። እነዚህን ለምሳሌ ያክል ይዘን ሌሎቹንም ጭምር በሚመዝን የዓሊሞች ንግግር ልቋጭ:—
1/ አልሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር - ረሒመሁላህ - “የረጀብን ወር ልዩ ብልጫም፣ መፆሙን ወይም ከፊሉን በተለየ እንዲፆም፣ ወይም ከሱ ውስጥ የተገደበን ሌሊት በሶላት ማሳለፍን፣… የሚጠቁም ለማስረጃነት የሚበጅ ትክክለኛ ሐዲሥ አልተላለፈም" ብለዋል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 6 እና 8]
2/ አልሓፊዝ አቡ ዐብዲላህ ሙሐመድ ኢብኑ አቢ በክር አዲመሽቂይ (691 ሂ.) ደግሞ “እያንዳንዱ የረጀብን ፆም እና ከፊል ሌሊቶቹን መስገድን የሚጠቁም ሐዲሥ ውሸት፣ ቅጥፈት ነው” ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 1/96]
ልብ በሉ! በዚህ ወር ውስጥ ፆምና ሶላት አይኑር ለማለት አይደለም። ወሩን ከሌሎቹ ወራት በተለየ መልኩ መያዝ አይገባም ነው አጠቃላይ ጭብጡ።
…
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
~~~
ከረጀብ ጋር ብዙ መሰረተ ቢስ ቅጥፈቶችና ደካማ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦
[1ኛ]፡-
رجب شهر الله وشعبان شهري ورمضان شهر أمتي
“ረጀብ የአላህ ወር ነው። ሸዕባን የኔ ወር ነው። ረመዷን ደግሞ የህዝቦቼ ወር ነው።” አልባኒ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ፡ 4400]
[2ኛ]፡- ረጀብ ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር፡-
اللهم بارك لنا في رجب وشعبان، وبلغنا رمضان
“አላህ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን። ረመዷንን አድርሰን።” ነወዊይ በ“አዝካር”፣ ዘሀቢይ በ“ሚዛን” ደካማ እንደሆነ ብይን የሰጡ ሲሆን አልባኒም “ደካማ ነው” ብለዋል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 4395]
[3ኛ]፡-
فضل شهر رجب على الشهور كفضل القرآن على سائر الكلام
“የረጀብ ወር በሌሎች ወራት ላይ ያለው ብልጫ ቁርኣን በሌሎች ንግግሮች ላይ እንዳለው ብልጫ ነው።” ኢብኑ ሐጀር “መሰረተ ቢስ ቅጥፈት ነው ብለዋል።
[4ኛ]፡-
خمس ليال لا ترد فيهن الدعوة أول ليلة من رجب، وليلة النصف من شعبان، وليلة الجمعة، وليلة الفطر، وليلة النحر
“አምስት ሌሊቶች በነሱ ውስጥ የተደረገ ዱዓእ አይመለስም። የመጀመሪያው የረጀብ ሌሊት፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት፣ የጁሙዐ ሌሊት፣ የዒደል ፊጥር ሌሊት እና የዒደል አድሓ ሌሊት ናቸው።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 1452] [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 2852]
[5ኛ]፡-
رجب شهر عظيم يضاعف الله فيه الحسنات، فمن صام يوما من رجب، فكأنما صام سنة، ومن صام منه سبعة أيام، غلقت عنه سبعة أبواب جهنم، ومن صام منه ثمانية أيام، فتحت له ثمانية أبواب الجنة، ومن صام منه عشرة أيام، لم يسأل الله شيئا إلا أعطاه إياه، …
“ረጀብ አላህ መልካም ምንዳዎችን የሚያነባብርበት ታላቅ ወር ነው። ከረጀብ አንድ ወር የፆመ ሰው አመት እንደፆመ ነው። ከሱ ሰባት ቀናትን የፆመ ሰባቱ የጀሀነም በሮች ይዘጉለታል። ከሱ ስምንት ቀናትን የፆመ ስምንቱ የጀነት በሮች ይከፈቱለታል። ከሱ አስር ቀናትን የፆመ አላህን የሆነ ነገር አይጠይቅም፣ እሱኑ የሰጠው ቢሆን እንጂ፣ …” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 5413]
[6ኛ]፡-
إن في الجنة نهرا يقال له رجب ماؤه أشد بياضا من اللبن وأحلى من العسل من صام يوما من رجب سقاه الله من ذلك النهر
“በጀነት ውስጥ ረጀብ የሚባል ወንዝ አለ። ውሃው ከወተት የነጣ፣ ከማር የጣፈጠ ነው። ከረጀብ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ ከዚያ ወንዝ ያጠጣዋል።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 1902]
[7ኛ]፡-
صوم أول يوم من رجب كفارة ثلاث سنين، والثاني كفارة سنتين، والثالث كفارة سنة، ثم كل يوم شهرا
“የረጀብን የመጀመሪያ ቀን መፆም የሶስት አመት ወንጀል ያብሳል። ሁለተኛው የሁለት አመት ያብሳል። ሶስተኛው ደግሞ የአመት ያብሳል። ከዚያም እያንዳንዱ ቀን የወር ነው።” አልባኒ ደካማ ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 3500፣ 5649]
[8ኛ]፡-
لا تغفلوا عن أول جمعة من رجب فإنها ليلة تسميها الملائكة الرغائب
“ከረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐ አትዘናጉ። እርሷ መላእክት ‘አረጋኢብ’ ብለው የሚጠሯት ሌሊት ነች።”
‘ሶላተ ረጋኢብን’ በተመለከተ ነወዊይ እንዲህ ብለዋል፡- “እርሷን የፈጠረን ሰው አላህ ይርገመው! እርሷ አስቀያሚ ቢድዐ ነች!” [ሸርሑ ሙስሊም] በተጨማሪም እሷንና የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሶላትን አስመልክተው “… ቢድዐና አስቀያሚ ፈጠራዎች ናቸው። በ‘ቁቱል ቁሉብ’፣ ‘ኢሕያእ ዑለሚዲን’ ኪታብ ውስጥ ስለተጠቀሱ ማንም እንዳይሸወድ። እነሱን በሚጠቁመው ሐዲሥም እንዲሁ (እንዳይሸወድ)። ምክንያቱም ሁሉም ውድቅ ነውና” ብለዋል። [አልመጅሙዕ፡ 3/548]
[9ኛ]፡-
أن رسول الله -ﷺ- لم يصم بعد رمضان إلا رجبًا وشعبان
“የአላህ መልእክተኛ ከረመዷን በኋላ ረጀብንና ሸዕባንን እንጂ አልፆሙም።” ኢብኑ ሐጀር በጣም ደካማ ነው ብለውታል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 12]
[10ኛ]፡-
من صلى المغرب في أول ليلة من رجب ثم صلى بعدها عشرين ركعة يقرأ في كل ركعة بفاتحة الكتاب، وقل هو الله أحد مرة، ويسلم فيهن عشر تسليمات، أتدرون ما ثوابه؟ قال: حفظه الله في نفسه وأهله وماله وولده، وأجير من عذاب القبر، وجاز الصراط كالبرق بغير حساب ولا عذاب
“በረጀብ የመጀመሪያ ሌሊት መግሪብን ሰግዶ ከዚያም በእያዳንዷ ረከዐ ፋቲሐንና ቁል ሁላሁ አሐድን አንድ ጊዜ እየቀራ፣ በአስር ተስሊማት እያሰላመተ ሃያ ረከዐ የሰገደ ሰው ምንዳው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አላህ በነፍሱም፣ በቤተሰቡም፣ በገንዘቡም፣ በልጁም ይጠብቀዋል። ከቀብር ቅጣትም ይጠበቃል። ሲራጥንም ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት እንደ ብልጭታ ያቋርጧል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/123] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 20]
[11ኛ]፡-
من صام من رجب وصلى فيه أربع ركعات ... لم يمت حتى يرى مقعده من الجنة أو يُرى له
“ከረጀብ ፁሞ፣ በሱ ውስጥ አራት ረከዓዎችን የሰገደ ሰው … በጀነት ውስጥ መቀመጫውን ሳያይ ወይም ሳይታይለት አይሞትም።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/124] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 21]
[12ኛ]፡-
إن شهر رجب شهر عظيم، من صام منه يومًا كتب الله له صوم ألف سنة ...
“የረጀብ ወር ታላቅ ወር ነው። ከሱ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ አንድ ሺ አመት ፆም ይመዘግብለታል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/206-207] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 26]
ከረጀብ ጋር የሚያያዙት ዘገባዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም። እነዚህን ለምሳሌ ያክል ይዘን ሌሎቹንም ጭምር በሚመዝን የዓሊሞች ንግግር ልቋጭ:—
1/ አልሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር - ረሒመሁላህ - “የረጀብን ወር ልዩ ብልጫም፣ መፆሙን ወይም ከፊሉን በተለየ እንዲፆም፣ ወይም ከሱ ውስጥ የተገደበን ሌሊት በሶላት ማሳለፍን፣… የሚጠቁም ለማስረጃነት የሚበጅ ትክክለኛ ሐዲሥ አልተላለፈም" ብለዋል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 6 እና 8]
2/ አልሓፊዝ አቡ ዐብዲላህ ሙሐመድ ኢብኑ አቢ በክር አዲመሽቂይ (691 ሂ.) ደግሞ “እያንዳንዱ የረጀብን ፆም እና ከፊል ሌሊቶቹን መስገድን የሚጠቁም ሐዲሥ ውሸት፣ ቅጥፈት ነው” ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 1/96]
ልብ በሉ! በዚህ ወር ውስጥ ፆምና ሶላት አይኑር ለማለት አይደለም። ወሩን ከሌሎቹ ወራት በተለየ መልኩ መያዝ አይገባም ነው አጠቃላይ ጭብጡ።
…
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور