Unique Academy
1.79K subscribers
200 photos
6 videos
25 files
214 links
☆ Welcome to Unique Maths!
" LEARN UNIQUELY AND FLUENTLY " Join us for effective learning Process....

☆ Youtube Channal : https://www.youtube.com/@Uniquemathematic

☆ CEO : Yishak Debebe & Henok Debebe
Download Telegram
ማስታወቂያ

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።


ማሳሰቢያ፡-

1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
2. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።
4
Unique Academy
https://youtu.be/Kru60Q7ud00
He was one of our student!!

Rly proud of him
5👏2
እንኳን አደረሳችሁ!

💫 ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች መልካም የመስቀል በዓል!!
5🥰4
የ2017 የ 12ኛ ክፍል ዉጤት ተስተካክሏል::
እንደገና እየገባችሁ check አድርጉ!
👌9
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ከፈተናው ሲስተም ጋር ለመተዋወቅ የሚያግዛችሁ የሙከራ ፈተና (Demo Exam) ዛሬ መስከረም 19/2018 ዓ.ም 9፡00 ሰዓት ላይ ይሰጣል፡፡

በመሆኑም በምዝገባ ወቅት በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በመገኘት የሙከራ ፈተናውን በመውሰድ ልምምድ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳስበዋል፡፡
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በዚህም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች፥ ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ ያሟሉ ሆኖ የተወሰነ መሆኑን በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን መስከረም 20/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ደብዳቤ ያሳያል።

በመሆኑም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስተሩ ገልፀዋል።

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የደብዳቤውን ትክክለኛነት ያረጋገጠ ሲሆን፤ በዚህ ውሳኔ መሠረት 300 ነጥብ የነበረው የየኒቨርሲቲ መግቢያ ወደ 297 የተጠጋጋ መሆኑን ተረድተናል።
🥰4😁21
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ፣ በሁለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በቅድመ ምረቃ በመደበኛው መርሐግብ ለመግባት አመልክታችሁ የመግቢያ ፈተና የወሰዳችሁና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ምርጫችሁ ላደረጋችሁ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ፦

ኢንጂነሪንግ ትምህርት
ለወንዶች 69.5 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 65 እና ከዚያ በላይ

አፕላይድ ሳይንስ ትምህርት
ለወንዶች 57 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 50 እና ከዚያ በላይ

ይህ የመቁረጫ ነጥብ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቻ ነው።

የመቁረጫ ነጥብ ስሌት፥ የ12ኛ ክፍል ውጤት ወደ መቶ ፐርሰንት በመቀየር እና የመግቢያ ፈተና ውጤት ከመቶ ፐርሰንት በመውሰድ የሁለቱ ውጤቶች አማካይ (Average) የተማሪው/ዋ ውጤት እንደሆነ ተገልጿል።

የተማሪዎችን የምዝገባ ጊዜን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
7
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ።

ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል።

1.  በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።

2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።

የመቁረጫ ነጥብ ፦

➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216

➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204

➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198

➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198

➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
5
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ።

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ፦
Website:  https://student.ethernet.edu.et
Telegram bot: @moestudentbot አማራጮች ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።
Unique Academy
Photo
የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
👍73
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፦ በዋናው ግቢ
የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች፦ በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
➫ የስፖርት ትጥቅ።
4
በ2018 ዓ.ም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የፍሬሽማን ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
➫ የ12ኛ ክፍል ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ 6 ፓስፖርት መጠን ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና ትራስ ልብስ፣
➫ የስፖርት ትጥቅ።

የትምህርት ማስረጃዎች እና ፎቶግራፍ ስካን አድርጋችሁ በሶፍት ኮፒ ይዛችሁ መሔድ ይኖርባችኋል፡፡
6
💫 በ2018 ዓ. ም ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ጥሪ አለማድረጉን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥሪ እንዳደረገ የሚገልፅ ሐሰተኛ መረጃ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ እንደሚገኝ ለማወቅ መቻሉን ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል።

ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ምንም አይነት ጥሪ አለማድረጉን ያረጋገጠው ዩኒቨርሲቲው፤ ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትን ጊዜ በቅርቡ የሚገልፅ መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል፡፡
#MaddaWalabuUniversity

በ2018 ዓ.ም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት የመደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ስትከታተሉ ቆይታችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፍያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

በተጠቀሱት ቀናት በዩኒቨርሲቲው ዋና ካምፓስ በመገኘት ምዝገባ እንድታደርጉ የተባለ ሲሆን፤ ትምህርት ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዘዟቸው የሚገቡ፦
➫ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣
➫ ከ8-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

በ2018 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል፡፡
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለአንደኛ እና ሁለተኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም በ2017 ዓ.ም በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ስትከታተሉ ቆይታችሁ ወደ አንደኛ ዓመት ለመግባት ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ፣ በትምህርት ሚኒስቴር ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ አንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም የመመዝገቢያ ቀናት ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በቅጣት ምዝገባ እና ትምህርት የሚጀምረው ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ መጠኑ 3×4 ፎቶግራፍ (4)፣
➫ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣
➫ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡