HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
2.25K subscribers
1.99K photos
96 videos
51 files
3.81K links
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️

👇👇👇
http://www.youtube.com/@haileG2239
Download Telegram
🙏 እግዚአብሔር ስሙ በፍጥረት አንደበት ሁሉ የተመሰገነ ይሁን። ታቦታቱ ወደ ማደሪያቸው በሰላም ገብተዋል። በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላችሁ ቤተሰቦቼ በያላችሁበት የእግዚአብሔር ፍጹም ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን። አሁንም እንበርታ፣ እንጠንክር 🙏🙏 እንኳን አደረሳችሁ 🙏🙏
👍106
ከክፉው ተወልደው ሀገር የሰበሩ፤
ምድሪቷን አርክሰው ሕዝብ ያደናበሩ፤
ለጠላት ወግነው ለወገን ያልኖሩ፤
ዜጋን ያሰቃዩ እርግማን ያፈሩ፤
ጥፋትን አስፋፋተው እልቂትን የሠሩ፤
ታሪክን አምክነው ትውልድ ያሳፈሩ፤
ከዛር ተወልደው ነው ሁሉን ያከሰሩ።

እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን!!

ደስ የምል ቀን ነበር እግዚአብሔር ይመስገን 🙏🙏🙏🙏

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
4🥰1
"ዛሬ ወደ ዮርዳኖስ እንዴት ወረድን?"

እድሜ ዘመኑን በበረሃ የኖረው ቆዳ ለባሽ፣ ጠፍር ታጣቂው መናኝ ቅዱስ ዮሐንስ "ንስሐ ግቡ" እያለ በመስበክ የጌታን መንገድ ያዘጋጅ፣ ጥርጊያውንም ያቀና ነበር። በዮርዳኖስም ወንዝ ሲያጠምቅ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳ፣ በዮርዳኖስም ዙሪያ ባሉ አገራት የሚኖሩ ሰዎች ወደ እርሱ እየመጡ ኃጢአታቸውን በመናዘዝ ይጠመቁ ነበር። ራሱ አጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ "እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃለሁ" ሲል እንደ ተናገረ ጥምቀቱ ሰው በደሉንና ክፋቱን አስቦ በመጸጸት የሚጠመቀው "የንስሐ ጥምቀት" ነበር።

ንስሐ ለሚለው ቃል የግሪኩ አቻው ሜታኖያ (metanoia) ሲሆን ትርጉሙም የአስተሳሰብ ለውጥ (change of mind) ማለት ነው። ስለዚህ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ ይመጡ የነበሩት ተጠማቂዎች የቀድሞ ክፋታቸውን ትተው፣ በተቀደሰ ቁጭት ሕሊናቸውን ወደ ጽድቅ ለመመለስ እና ራሳቸውን ለመለወጥ የወሰኑ ነበሩ። አመጣጣቸውም በተሰበረ ልብ ነው።

ይሁን እንጂ ልባቸው እንደ ዐለት የጸና ፈሪሳውያን እና ሰዱቃውያን ግን እንደ ሌሎች ሰዎች በጸጸትና በትሕትና ሳይሆን በትዕቢት እንደ ታጀሩ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ መጡ። እንደ ቅዱስ ዳዊት የተሰበረ አጥንት (ልብ) ሳይኖራቸው፣ በኃጢአት ያረጀ ፊተኛው ልባቸውን በመጠየፍ "አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ" ብለው ሳይለምኑ፣ ታጥበው ብቻ ከበረዶ ይልቅ ነጭ ለመሆን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወረዱ።

ቅዱሱም መናኝ ባያቸው ጊዜ አመጣጣቸውን ያውቀዋልና "እናንተ የእፉኝት ልጆች" ሲል ገሰጻቸው። ከእፉኝት ጠባያት ውስጥ አንዱ ተናድፋ ወደ ውኃ (በቅርቧ ወዳለ ባሕር) መሸሿ ነው። ፈሪሳውያኑም እንዳሻቸው ክፋት አድርገው ሲያበቁ፣ የእርሱን የንስሐ ጥምቀት መሸሸጊያ ለማድረግ ወደ ዮርዳኖስ ያለ ምንም ጸጸት ይሮጣሉና እንዲህ አላቸው። እኛስ የዮርዳኖስ ባሕር ተምሳሌት ወደምትሆነው ጥምቀተ ባሕር እንዴት ወረድን? በንስሐ እና በጸጸት፣ የቀደመውን ክፋት ለመተው በቆረጠ የተለወጠ ሕሊና ወይስ እንዲሁ ባልተጸጸተ ፈሪሳዊና ሰዱቃዊ ሕሊና? ዛሬ ወደ ዮርዳኖስ እንዴት ወረድን?

እንኳን ለበዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!

በዲያቆን አቤል ካሳሁን

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
3
ራሳችንን መስሎ፣ የሚኖር፣ የሚተገብር እና የሚናገር ከባዱ የዓይነጥላ መንፈስ ፈተና || ያላወቅንበት ግን በብዙ የተጎዳንበት || በማለዳ ንቁ 2024 😭😭😭 https://youtu.be/kU13J02gLFo
👍3
ጉድ ነው! ጫትን በኪኒን መልክ ልያቀርቡልን ነው || ሽምግልና ባሕላዊ ነው ወይስ መንፈሳዊ? ሰው መሆን ያቃተው ትውልድ #ethiopia #orthodox 😰😰😭 https://youtu.be/BS1y-8S-6Y4
"እረኞች በግ ሆነው"
--
ሕመሙ፥ ለካ ለቤተ ክርስቲያን በዚህ ልክ ፍቅር አለን? ያሰኘ ነበር። ፍቅራችንን በሕመማችን ለካነው። በእርግጥ፥ ሕመማችን አልተፈወሰም። መለስ እንዳለ ነው። ካልጠብቅነው ቦታ ያልተጠበቀ ድርጊትም ተከትሎታል። እረኞቻችን የበጎችን ጥበቃ የፈለጉበት ከባድ ጊዜ። ቸሩ እረኛ እርሱ ቤቱን እስከ መጨረሻው ያብጀው። ያለፈውን ዓመት፥ ኦርቶዶክሳዊ ኅብረትን የሚያናጋና ክብረ ክህነትን ዝቅ የሚያደርግ አካሔድ ዳግም አያሳየን። የምንናፍቀው እንደ ኖኅ መርከብ ሁሉን እንደ ጠባዩ አቅፋ በምታኖረው ቤተክርስቲያን በአንድ ልብ መኖር ነው። አሁንም ፈጽሞ ይሰብስበን። በግፍ የወደቁት ግፉዓን በረከታቸው ይደርብን። አሜን።

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍3
የጋብቻ እርግማንና የመረጋገም ፍዳ || የጣዖት መንፈስ በእኛ ሕይወት || የባሕልና የእምነት ውጊያዎች || የእርግማን መንፈስ || በማለዳ ንቁ 2024 😭😰🙄 https://youtu.be/_-aP8LPYRp0
"መነኩሴ ሆይ!"

በእግዚአብሔር ዘንድ ከፍ ከፍ ትል ዘንድ መደላደልን መቀማጠልን ተው ለመነኩሴ አልታዘዘምና።

** ልብህን ፀጥ ማድረግ ባይቻልህ አንደበትህን ፀጥ ማድረግ ይቻልሃል፤ በጎ ምግባርን ክብርን ገንዘብ ታደርግ ዘንድ ከብዙ ሰዎች ጋር መኖርን ተው። ኃጢአት አብዝቶ ከሚመገብ ሆድ ይገኛልና። ቂመኛ ሰው ሥጋ የለበሰ ሰይጣን ነው።

ከሰይጣን ይልቅ ልማድህን ፍራ። መነኩሴ ከዚህ ዓለም በሞት ካልተለየ በቀር ፆር አይጠፋለትምና ትጋ። የምንኩስና ፍጹም ሥራ ራስን መንቀፍ ነው። ቁጡ ሰው ሙት ቢያስነሳ አትመኑት ከፀጋ ይደርሳል ጣዕም ይቀምሳል አትበሉት ሠርቶ ሠርቶ የተቆጣ ዕለት ያፈርሰዋልና። የሰይጣን ሽመቃው ከገዳም ማውጣት ነውና በበአትህ ጽና።

ውዳሴ ከንቱን ሽሽ ውዳሴ ከንቱ ምቀኝነትን፣ ፉክክርን፣ ተንኮልን፣ እኔ ያልኩት ይሁን ብሎ በነገር ማሸነፍን፣ መዳራትን፣ ቂም በቀልን፣ ሐሰትን፣ አጥብቆ ድፍረትን ወዘተ ... ሁሉ ፆር ያመጣል ተንኮሉ የበዛ ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ይጥላል።

መነኩሴ ሆይ! ነጭ ሐር ሳይሆን ትህትናን ልበስ። ሱባኤህን በትዕግስትና በአርምሞ ያዝ። ይበድሉህ አትበድል፣ ይክሰሱህ አትክሰስ፣ ይምቱህ አትምታ፣ ክፉውን ሁሉ በሀሰት ያውሩብህ ካንተ ክፉ አይውጣ፤ ያኔ ምድራዊ መልአክ ትሆናለህ።

(ከመጽሐፈ መነኮሳት (የበረሃው ምስጥር))

#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍43
ስንፈተ ሩካቤ እና የሐበሻ መድኃኒት ጣጣው || ስንፈተ ሩካቤ በሳይኮሎጂ ውጤት አለው? ስንፈተ ሩካቤ ከምን ይመጣል? መፍትሔውስ ምንድነው? #ethiopia 😰🙄 https://youtu.be/MRMajH_5-5E
«ሰው ራሱን ሳያውቅ የሚቀረው ስላልቻለ ብቻ አይደለም፡፡ ራሱን ማወቅ ስለማይፈልግም ጭምር ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ‹ራስን ማወቅ› ይዞ የሚያመጣው ጊዜያዊ ሕመም ወይም ትንሽ ስቃይ አለ፡፡ ወደ ራሳችን መመልከት ስንጀምር የማንፈልገውን ‹‹እኛነት›› በውስጣችን ልናገኘው እንችላለን፡፡ በዚህም መረበሽ፣ መቆጨት፣ ኃፍረት ይሰማን ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ስሜት ለማምለጥ ብለን ወደ ቅዠታዊ ዓለም ይሄድ ዘንድ ለራሳችን ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ ለእኛ ከማንም በላይ ጠላት የሚሆንብን ይህ በውስጣችን የተደበቀውና ማወቅ የማንፈልገው ‹‹ስውር እኛነታችን›› ነው፡፡ ስለዚህም በጊዜ ራስን መርምሮ አፋጣኝ መልስ መስጠት ያስፈልጋል፡፡»

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
8👍2