ፈሪ የሚያደርግ የዓይነጥላ መንፈስ እጮኛና ትዳር መያዝ እንፈራለን ከመናገር ይልቅ ማልቀስ ይቀናናል || ሰውነታችን ይንቀጠቀጣል፣ ያልበናል 😭😰🙄
https://youtu.be/Q0umAjAzA60
https://youtu.be/Q0umAjAzA60
YouTube
ፈሪ የሚያደርግ የዓይነጥላ መንፈስ || እጮኛና ትዳር መያዝ እንፈራለን || ከመናገር ይልቅ ማልቀስ ይቀናናል || ሰውነታችን ይንቀጠቀጣል፣ ያልበናል 😭😰🙄
ፈሪ የሚያደርግ የዓይነጥላ መንፈስ || እጮኛና ትዳር መያዝ እንፈራለን || ከመናገር ይልቅ ማልቀስ ይቀናናል || ሰውነታችን ይንቀጠቀጣል፣ ያልበናል 😭😰🙄
https://youtu.be/Q0umAjAzA60
https://youtu.be/Q0umAjAzA60
❤7👍1👏1
የጥምቀት በዓል 99% ራሳችንን ለማስደሰት የዓመጻ ሥራ የምንሰራበት ነው || ተግሳጽና ምክር በመምህር ዘበነ ለማ #ethiopia #orthodox #eotc 😭🙄
https://youtu.be/b9y_M_YWKBw
https://youtu.be/b9y_M_YWKBw
YouTube
የጥምቀት በዓል 99% ራሳችንን ለማስደሰት የዓመጻ ሥራ የምንሰራበት ነው || ተግሳጽና ምክር በመምህር ዘበነ ለማ #ethiopia #orthodox #eotc 😭🙄
የጥምቀት በዓል 99% ራሳችንን ለማስደሰት የዓመጻ ሥራ የምንሰራበት ነው || ተግሳጽና ምክር በመምህር ዘበነ ለማ #ethiopia #orthodox #eotc 😭🙄
https://youtu.be/b9y_M_YWKBw
https://youtu.be/b9y_M_YWKBw
+ ለምን ትቀናለህ? +
◈ በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡
◈ አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነገር ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ "ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ" ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡
◈ ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው "በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ" ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
◈ ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡
◈ ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡
◈ ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡
◈ ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ "ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ" ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
◈ የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ "እምቢየው አልገባም" እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡
◈ ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘"በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር" ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡
◈ የሰንበት መሻር፣ ለቄሣር ግብር መከፈል፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ "የቤትህ ቅናት በላኝ" እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡ ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡
◈ ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡ በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡
"በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን" (ሮሜ 13፡13)
በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
◈ በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡
◈ አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነገር ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ "ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ" ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡
◈ ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው "በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ" ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
◈ ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡
◈ ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡
◈ ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡
◈ ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ "ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ" ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
◈ የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ "እምቢየው አልገባም" እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡
◈ ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘"በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር" ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡
◈ የሰንበት መሻር፣ ለቄሣር ግብር መከፈል፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ "የቤትህ ቅናት በላኝ" እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡ ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡
◈ ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡ በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡
"በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን" (ሮሜ 13፡13)
በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍4
🌹 አቤቱ አምላካችን ሆይ፤ ክቡር መንግስት ያንተ ነውና፤ ከአለም አስቀድሞ ምስጋና፤ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ይገባል፤ ዛሬም ዘወትርም ለልጅ ልጅ፤ ለዘላለሙ የማይፈጸም።
🙏 አሜን 🙏
( ኪዳን ዘነግህ ዘመንፈቀ ሌሊት ክፍል 1 )
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🙏 አሜን 🙏
( ኪዳን ዘነግህ ዘመንፈቀ ሌሊት ክፍል 1 )
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
❤5👍5
◈ አጋንንትን ሁሉ የማሸነፍ ሥልጣን የተሰጠው ለሁሉ በስሙ ላሉ ክርስቲያኖች ነው፡፡ ለበቁ አባቶች፣ ለመነኮሳት፣ ለባሕታዊያን፣ ለካህናት ብቻ ተለይቶ የተሰጠ ሥልጣን አድርገን የምንገምት ሰዎች እንኖራለን፡፡ የለም የለም! ለሁሉ የእግዚአብሔር ሊሆኑ ለፈቀዱት ሁሉ ጠላታቸውን እንዲያሸንፉ ሰማያዊ ሥልጣን ተሰጥቶአል፡፡ እንደውምማ ይሄን የባሕሪይ ሥልጣን ሰዎች በእምነት አውቀውት ዲያቢሎሰን ማዘዝ ሲጀምሩ መመጻደቅ እንዳይጠልፋቸው ጌታ እንዲህ ሲል አስጠነቀቀ፤ "መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ሰለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ።" (የሉቃስ ወንጌል 10፥20) ከዚህ በመናፍስት ላይ ከተሰጠን ብዙ አይነት ሥልጣን መካከል፤ ክፉዎቹን በእምነት ገመድ ጠፍንጎ የማሰር ኃይል አንዱ ሆኖ ይገኛል፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍2
ሴቶችን በተለይ መልከኞችን ትዳር አልባ የሚያደርገው የዓይነጥላ መንፈስ ፈተና ባለ ትዳሮች ለየብቻ መቁረብ ይችላሉን? ወንድ አርቅ፣ የትዳር ጠንቅ 😭🙄
https://youtu.be/QALRUtTYT9Q
https://youtu.be/QALRUtTYT9Q
YouTube
ሴቶችን በተለይ መልከኞችን ትዳር አልባ የሚያደርገው የዓይነጥላ መንፈስ ፈተና || ባለ ትዳሮች ለየብቻ መቁረብ ይችላሉን? || ወንድ አርቅ፣ የትዳር ጠንቅ 😭🙄
ሴቶችን በተለይ መልከኞችን ትዳር አልባ የሚያደርገው የዓይነጥላ መንፈስ ፈተና || ባለ ትዳሮች ለየብቻ መቁረብ ይችላሉን? || ወንድ አርቅ፣ የትዳር ጠንቅ 😭🙄
https://youtu.be/QALRUtTYT9Q
https://youtu.be/QALRUtTYT9Q
👍4
ከመኪና አደጋ ከሞት የዳንኩበት ቀን || ብዙ ሰው ዲያብሎስ ያጠፋበትን ብቻ ያወራል || የምስጋና ሕይወት ያስፈልገናል በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia 🙏🙏 https://youtu.be/D6ycRyx8bfk
YouTube
ከመኪና አደጋ ከሞት የዳንኩበት ቀን || ብዙ ሰው ዲያብሎስ ያጠፋበትን ብቻ ያወራል || የምስጋና ሕይወት ያስፈልገናል በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia 🙏🙏
❤10
መናፍስት ሠራዊት እንዳይስቡ ምን እናድርግ? የርኩሳን መናፍስት መናበብ መናፍስትን እንዴት እንሠር? #ethiopia #sibket #orthodox 🙄😰🙏
https://youtu.be/SByj_AWxa2c?si=BVNnmtlc1Sy91TWy
https://youtu.be/SByj_AWxa2c?si=BVNnmtlc1Sy91TWy
YouTube
መናፍስት ሠራዊት እንዳይስቡ ምን እናድርግ? || የርኩሳን መናፍስት መናበብ || መናፍስትን እንዴት እንሠር? #ethiopia #sibket #orthodox 🙄😰🙏
መናፍስት ሠራዊት እንዳይስቡ ምን እናድርግ? || የርኩሳን መናፍስት መናበብ || መናፍስትን እንዴት እንሠር? #ethiopia #sibket #orthodox 🙄😰🙏https://youtu.be/SByj_AWxa2c?si=BVNnmtlc1Sy91TWy
👍1
የዛርና የቡዳ መንፈስ አመልን የማስቀየር፣ ስጦታን የማሳጣት ትግል ቡዳ በተፈጥሮ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ቡዳ ምንድነው? #ethiopia #eotc 😭
https://youtu.be/6hFGNTLxzgI?si=Xlh028-tMmQjzcUz
https://youtu.be/6hFGNTLxzgI?si=Xlh028-tMmQjzcUz
YouTube
የዛርና የቡዳ መንፈስ አመልን የማስቀየር፣ ስጦታን የማሳጣት ትግል || ቡዳ በተፈጥሮ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ || ቡዳ ምንድነው? #ethiopia #eotc 😭
የዛርና የቡዳ መንፈስ አመልን የማስቀየር፣ ስጦታን የማሳጣት ትግል || ቡዳ በተፈጥሮ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ || ቡዳ ምንድነው? #ethiopia #eotc 😭
https://youtu.be/6hFGNTLxzgI?si=Xlh028-tMmQjzcUz
https://youtu.be/6hFGNTLxzgI?si=Xlh028-tMmQjzcUz
👍2
ደም ካልፈሰሰ፣ እንባ ካልወረደ ደስ የማይላቸው ባለሥልጣናት አሉ || ሰው ያልሆኑ ሰዎች የደም ግብር ይፈልጋሉ #ethiopia #orthodox #tewahido
https://youtu.be/JM4V1m1Xxsg
https://youtu.be/JM4V1m1Xxsg
YouTube
ደም ካልፈሰሰ፣ እንባ ካልወረደ ደስ የማይላቸው ባለሥልጣናት አሉ || ሰው ያልሆኑ ሰዎች የደም ግብር ይፈልጋሉ #ethiopia #orthodox #tewahido
ደም ካልፈሰሰ፣ እንባ ካልወረደ ደስ የማይላቸው ባለሥልጣናት አሉ || ሰው ያልሆኑ ሰዎች የደም ግብር ይፈልጋሉ #ethiopia #orthodox #tewahido
https://youtu.be/JM4V1m1Xxsg
https://youtu.be/JM4V1m1Xxsg
🙏 እግዚአብሔር ስሙ በፍጥረት አንደበት ሁሉ የተመሰገነ ይሁን። ታቦታቱ ወደ ማደሪያቸው በሰላም ገብተዋል። በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላችሁ ቤተሰቦቼ በያላችሁበት የእግዚአብሔር ፍጹም ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን። አሁንም እንበርታ፣ እንጠንክር 🙏🙏 እንኳን አደረሳችሁ 🙏🙏
👍10❤6
ከክፉው ተወልደው ሀገር የሰበሩ፤
ምድሪቷን አርክሰው ሕዝብ ያደናበሩ፤
ለጠላት ወግነው ለወገን ያልኖሩ፤
ዜጋን ያሰቃዩ እርግማን ያፈሩ፤
ጥፋትን አስፋፋተው እልቂትን የሠሩ፤
ታሪክን አምክነው ትውልድ ያሳፈሩ፤
ከዛር ተወልደው ነው ሁሉን ያከሰሩ።
እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን!!
ደስ የምል ቀን ነበር እግዚአብሔር ይመስገን 🙏🙏🙏🙏
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ምድሪቷን አርክሰው ሕዝብ ያደናበሩ፤
ለጠላት ወግነው ለወገን ያልኖሩ፤
ዜጋን ያሰቃዩ እርግማን ያፈሩ፤
ጥፋትን አስፋፋተው እልቂትን የሠሩ፤
ታሪክን አምክነው ትውልድ ያሳፈሩ፤
ከዛር ተወልደው ነው ሁሉን ያከሰሩ።
እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን!!
ደስ የምል ቀን ነበር እግዚአብሔር ይመስገን 🙏🙏🙏🙏
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
❤4🥰1
"ዛሬ ወደ ዮርዳኖስ እንዴት ወረድን?"
እድሜ ዘመኑን በበረሃ የኖረው ቆዳ ለባሽ፣ ጠፍር ታጣቂው መናኝ ቅዱስ ዮሐንስ "ንስሐ ግቡ" እያለ በመስበክ የጌታን መንገድ ያዘጋጅ፣ ጥርጊያውንም ያቀና ነበር። በዮርዳኖስም ወንዝ ሲያጠምቅ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳ፣ በዮርዳኖስም ዙሪያ ባሉ አገራት የሚኖሩ ሰዎች ወደ እርሱ እየመጡ ኃጢአታቸውን በመናዘዝ ይጠመቁ ነበር። ራሱ አጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ "እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃለሁ" ሲል እንደ ተናገረ ጥምቀቱ ሰው በደሉንና ክፋቱን አስቦ በመጸጸት የሚጠመቀው "የንስሐ ጥምቀት" ነበር።
ንስሐ ለሚለው ቃል የግሪኩ አቻው ሜታኖያ (metanoia) ሲሆን ትርጉሙም የአስተሳሰብ ለውጥ (change of mind) ማለት ነው። ስለዚህ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ ይመጡ የነበሩት ተጠማቂዎች የቀድሞ ክፋታቸውን ትተው፣ በተቀደሰ ቁጭት ሕሊናቸውን ወደ ጽድቅ ለመመለስ እና ራሳቸውን ለመለወጥ የወሰኑ ነበሩ። አመጣጣቸውም በተሰበረ ልብ ነው።
ይሁን እንጂ ልባቸው እንደ ዐለት የጸና ፈሪሳውያን እና ሰዱቃውያን ግን እንደ ሌሎች ሰዎች በጸጸትና በትሕትና ሳይሆን በትዕቢት እንደ ታጀሩ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ መጡ። እንደ ቅዱስ ዳዊት የተሰበረ አጥንት (ልብ) ሳይኖራቸው፣ በኃጢአት ያረጀ ፊተኛው ልባቸውን በመጠየፍ "አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ" ብለው ሳይለምኑ፣ ታጥበው ብቻ ከበረዶ ይልቅ ነጭ ለመሆን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወረዱ።
ቅዱሱም መናኝ ባያቸው ጊዜ አመጣጣቸውን ያውቀዋልና "እናንተ የእፉኝት ልጆች" ሲል ገሰጻቸው። ከእፉኝት ጠባያት ውስጥ አንዱ ተናድፋ ወደ ውኃ (በቅርቧ ወዳለ ባሕር) መሸሿ ነው። ፈሪሳውያኑም እንዳሻቸው ክፋት አድርገው ሲያበቁ፣ የእርሱን የንስሐ ጥምቀት መሸሸጊያ ለማድረግ ወደ ዮርዳኖስ ያለ ምንም ጸጸት ይሮጣሉና እንዲህ አላቸው። እኛስ የዮርዳኖስ ባሕር ተምሳሌት ወደምትሆነው ጥምቀተ ባሕር እንዴት ወረድን? በንስሐ እና በጸጸት፣ የቀደመውን ክፋት ለመተው በቆረጠ የተለወጠ ሕሊና ወይስ እንዲሁ ባልተጸጸተ ፈሪሳዊና ሰዱቃዊ ሕሊና? ዛሬ ወደ ዮርዳኖስ እንዴት ወረድን?
እንኳን ለበዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!
በዲያቆን አቤል ካሳሁን
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
እድሜ ዘመኑን በበረሃ የኖረው ቆዳ ለባሽ፣ ጠፍር ታጣቂው መናኝ ቅዱስ ዮሐንስ "ንስሐ ግቡ" እያለ በመስበክ የጌታን መንገድ ያዘጋጅ፣ ጥርጊያውንም ያቀና ነበር። በዮርዳኖስም ወንዝ ሲያጠምቅ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳ፣ በዮርዳኖስም ዙሪያ ባሉ አገራት የሚኖሩ ሰዎች ወደ እርሱ እየመጡ ኃጢአታቸውን በመናዘዝ ይጠመቁ ነበር። ራሱ አጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ "እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃለሁ" ሲል እንደ ተናገረ ጥምቀቱ ሰው በደሉንና ክፋቱን አስቦ በመጸጸት የሚጠመቀው "የንስሐ ጥምቀት" ነበር።
ንስሐ ለሚለው ቃል የግሪኩ አቻው ሜታኖያ (metanoia) ሲሆን ትርጉሙም የአስተሳሰብ ለውጥ (change of mind) ማለት ነው። ስለዚህ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ ይመጡ የነበሩት ተጠማቂዎች የቀድሞ ክፋታቸውን ትተው፣ በተቀደሰ ቁጭት ሕሊናቸውን ወደ ጽድቅ ለመመለስ እና ራሳቸውን ለመለወጥ የወሰኑ ነበሩ። አመጣጣቸውም በተሰበረ ልብ ነው።
ይሁን እንጂ ልባቸው እንደ ዐለት የጸና ፈሪሳውያን እና ሰዱቃውያን ግን እንደ ሌሎች ሰዎች በጸጸትና በትሕትና ሳይሆን በትዕቢት እንደ ታጀሩ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ መጡ። እንደ ቅዱስ ዳዊት የተሰበረ አጥንት (ልብ) ሳይኖራቸው፣ በኃጢአት ያረጀ ፊተኛው ልባቸውን በመጠየፍ "አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ" ብለው ሳይለምኑ፣ ታጥበው ብቻ ከበረዶ ይልቅ ነጭ ለመሆን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወረዱ።
ቅዱሱም መናኝ ባያቸው ጊዜ አመጣጣቸውን ያውቀዋልና "እናንተ የእፉኝት ልጆች" ሲል ገሰጻቸው። ከእፉኝት ጠባያት ውስጥ አንዱ ተናድፋ ወደ ውኃ (በቅርቧ ወዳለ ባሕር) መሸሿ ነው። ፈሪሳውያኑም እንዳሻቸው ክፋት አድርገው ሲያበቁ፣ የእርሱን የንስሐ ጥምቀት መሸሸጊያ ለማድረግ ወደ ዮርዳኖስ ያለ ምንም ጸጸት ይሮጣሉና እንዲህ አላቸው። እኛስ የዮርዳኖስ ባሕር ተምሳሌት ወደምትሆነው ጥምቀተ ባሕር እንዴት ወረድን? በንስሐ እና በጸጸት፣ የቀደመውን ክፋት ለመተው በቆረጠ የተለወጠ ሕሊና ወይስ እንዲሁ ባልተጸጸተ ፈሪሳዊና ሰዱቃዊ ሕሊና? ዛሬ ወደ ዮርዳኖስ እንዴት ወረድን?
እንኳን ለበዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!
በዲያቆን አቤል ካሳሁን
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
❤3