HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
2.25K subscribers
1.99K photos
96 videos
51 files
3.81K links
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️

👇👇👇
http://www.youtube.com/@haileG2239
Download Telegram
◈ አስተውሉ! የጸሎት ትኩረት የጥንካሬ ጉልበት አግኝቶ ሳይደክም እንድንተጋ ለአምላክ ካለ ፍቅር የሚጀምር ፈቃድ እና ስለ ጽድቅ ሕይወት የመዋደቅ ቁርጥ ውሳኔ ከኛ ይጠበቃል፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ አብዛኞቻችን እነዚህ የሉንምና መንፈሱ እፉዬ ገለባን የመሸከም ያህል ንቆ ይጫወትብናል፡፡
 
◈ የጸሎት አሳብ ከተመስጦአችን እያፈነገጠ እንዳይበታተን የምናስርበት መንፈሳዊ ገመድ፤ አስቀድመን ጸሎት ለማድረግ የምንፈልግበት የመነቃቃት ጉልበት ላይ ይመረኮዛል፡፡ ጸሎት እንደ ውኃ ጠምቶን እንደ ምግብ ርቦን ከሆነ ልንጸልይ የፈለግነው፤ የጸሎት አሳባችንም የመበተን ዕድሉ ጠባብ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ፈልጎ የሚያደርገውን ነገር ሲያደርግ፤ ትኩረቱን በሚያደርገው ነገር ላይ ለመሰብሰብ አይቸገርም፡፡

◈ አንድ እናት ልጆቿን ጠዋት ቁርስ የማብላት ኃላፊነት እንደሚሰማት ሁሉ፤ ጸሎትም ላይ ይሄ ይሰማት፡፡ አንድ አባት ቤተሰቡን የማስተዳደር ኃላፊነት በትከሻው እንዳለ እንደሚያስብ ሁሉ ጸሎትንም እንዲሁ ያክብረው፡፡ አንድ ተማሪ ትምህርቱን የማጥናት ኃላፊነት ቢያንስ ለፈተና ግድ ሆኖ እንደሚታየው ሁሉ ጸሎትንም እንዲህ ይየው፡፡ ምንም ውስብስብ ነገር የለውም፤ ለሥጋ የምናስበውን ያህል ለነፍስም እናስብለት፡፡

◈ እነዚህን ጠላቶች በመዋጋቱ ረገድ የመጀመሪያው ቀዳሚ መፍትሔ፤ ወደ ጸሎት ቤት እንደገባን በቀጥታ መደበኛውን ጸሎት ከማድረስ አስቀድሞ መናፍስቱን በሰማያዊ ስሞች ማሰር ያስፈልጋል፡፡
#በርቱ 🙏

#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!

#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍4
🌹 የሰማዕቷ የቅድስት አርሰሜ ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ጸንቶ ይኑር። ቃልኪዳንዋ አይለየን 🌹 ታህሳስ 6 ቅዳሴ ቤቷ ይከብራል። 🙏🙏 እንኳን አደረሳችሁ 🌹
28
"ኃይል የሌለውን ምንኛ ረዳኸው!
ብርታት የሌለውን ክንድ ምንኛ አዳንኸው!" ኢዮ 26፥2
🥰4😢2
ጥያቄ 1: ከጌታችን መድኃኂታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ልደት አስቀድሞ የሚመጡ ሦስቱ እሑዶች ስያሜያቸው ምንድን ነው? ሁላችሁም ተሳተፉ።
Anonymous Quiz
13%
ሀ፡ ስብከት፣ ኒቆዲሞስ፣ ደብረ-ዘይት
62%
ለ፡ ስብከት፣ ብርሃን፣ ኖላዊ
20%
ሐ፡ ቅድስት፣ ዘወረደ፣ መፃጉዕ
4%
መ፡ ምኩራብ፣ ገብርሔር፣ ብርሃን
👍2
ጥያቄ 2፡ የሰው ልጅ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ መፈጠሩ ግልጽ ሲሆን ዕድሜውም እንዲሁ በዐራት ደረጃዎች የተከፈለ ነው። በዚህም መሠረት ከሃያ እስከ ዐርባ ዓመት ያለው ጌዜ የትኛውን ባሕርይ ያመለክታል? የራሳችሁን አሳብም መጻፍ ይቻላል።
Anonymous Quiz
71%
ሀ፡ የእሳት
9%
ለ፡ የውሃ
11%
ሐ፡ የነፋስ
9%
መ፡ የመሬት
👍1
ጥያቄ 3፡ በገጠሩ ሀገራችን ኢትዮጵያ እናቶች ልጆች ሲታመሙ ወይም ጭንቀት ሲይዛቸው መድሐኒት ነው በማለት ለቡዳ፣ ለዓይነጥላ በማለት አንገት፣ ክንድ፣ ጭን ላይ ኪታብ ወይም እጄ-ሰብ ያስራሉ? በጬሌ ይዳብሳሉ። የግል ምልከታችሁን ጻፉ?
Anonymous Poll
62%
ሀ፡ እውነት (ችግሩ ለመናፍስት በማለዳው እንሰጣለን)
14%
ለ፡ ሐሰት (እንዲህ የሚባል ነገር የለም)
33%
ሐ፡ በትክክል እኔም ገጥሞኛል፣ ተዳብሻለሁ፣ አስሪያለሁ።
5%
መ፡ የግል አሳባችሁን ጻፉ
1
ጥያቄ 5: ስለ ስንበተ-ክርስቲያንና ስለ ዕለተ ምጽአት የሚናገረው የቅዳሴ ክፍል?
Anonymous Quiz
31%
ሀ፡ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
22%
ለ፡ ቅዳሴ ማርያም
28%
ሐ፡ ቅዳሴ አትናቴዎስ
19%
መ፡ ቅዳሴ ባስልዮስ
👍1
ጥያቄ 6፡ የልጅ በሕሪይን የሚያላብስ የሚያስለቅስ፣ ጣፋጭ ነገር ከረሜላ ወይም ስኳር አብዝተን እንድንጠቀም የሚያደርግ፣ የተቆራረጡ ልብሶች ወይም እርቃን እንድንሆን የሚያደርግ የቤተሰብ ዛር መንፈስ የቱ ነው። ትልቅ ሆነን እንደ ልጅ የሚያደርግ መንፈስ? እድሜያችን ገፍቶ እንኳን ቀለም መቀባት፣ ልፕስቲክ፣ ሰው ሰራሽ ጸጉር መቀጠል? እንዲህ የሚያደርጉ መንፈሶች በብዛት የትኛው ነው?
Anonymous Quiz
4%
ሀ፡ ሼህ አምበሶ
11%
ለ፡ አውልያ የከራማ መንፈሶች
77%
ሐ፡ ሙጬ ወይም ሙጫዮ
4%
መ፡ ጨንገር አባ ላፋ
3%
ሠ፡ የግል አሳባችሁን ጻፉ
"እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው" (ወደ ሮሜ ሰዎች 1፥28)

የሮሜውን መልእክት ገልብጠን [በታቃራኒው] እናንብበው፡፡

"እግዚአብሔርን ለማወቅ በወደዱት መጠን እግዚአብሔር የሚገባውን ያደርጉ ዘንድ ለሚረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው"፡፡ ለማወቅ በወደዱት መጠን የሚለው ቦታ ፍላጎት የሚባለውን የጠባይ ክፍል ይጠቁማል፡፡

ስለዚህ መልእክቱ የሚለን፤ "ወደ እግዚአብሔር ለመጠጋት በፈለጋችሁት ልክ፥ እግዚአብሔር ትክክለኛውን ነገር ልታደርጉ የምትችሉበት አቅም ይሆናችኋል" ነው፡፡

#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
👍3👏2
◈ አስተውሉ! ጸሎት የማድረስ ፍላጎታችን ደካማና የሰለቸ ከሆነ፤ መናፍሰቱ እዚህች ጠባይ ውሰጥ በመግባት ከመንፈስ ቅዱሰ የሚሰነዘረው ጥቃት እንዳያቃጥላቸው መከ'ለል ይችላሉ፡፡ ምን ማለት ነው፤ መንፈስ ቅዱስ እኛንም መናፍስቱንም በአንድነት ደርቦ አያጠቃምና፥ ተጻራሪዎቹን ከእኛ ውስጥ ሳሉ ለብቻቸው እንዲያገኛቸው እኛን ከፊት አድርገው ከተከለሉበት የባሕሪይ መጋረጃ መውጣት አለባቸው፡፡ እኛ ጸሎት ማድረግ የማንፈልግ ስንሆን መናፍስቱም ጸሎትን አይፈልጉምና በዚህ ባሕሪይ ስንታይ አንድ ሆነናል፡፡ ይህም ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ክፉዎቹን እየለየ እንዳያቃጥላቸው ራሳችን ጠበቃ ሆንንበት ተብሎ ሊታሰብ ይችላል፡፡ እኛ ጸሎት የማድረስ እውነተኛ ልባዊ ፍላጎት ካለን ግን፤ ከውስጥ ያለው የጠላት ባሕሪይ መንፈሳዊነትን የማይፈልግ ነውና፤ ይሄ የመፈለግና ያለመፈለግ ባሕሪያት ጥል ከአካላችን ላይ ተቃራኒ ስበቶችን ይፈጥራል፡፡ በዚህ ጊዜመናፍስቱን ብናስር፣ እንዲጸልዩ ብናስገድድ፣ ቅዱሳንን ብንጠራ መስተቃርኑን የበለጠ የሰፋ ያደርገዋልና የጠላት መደበቂያ በሚከተለው በትግሉ ሂደት እየፈረሰ እየፈረሰ ይመጣል፡፡ በአጭር አማርኛ መንፈሱ መገለጥ ይጀምራል፡፡ (አንቀጹ ተደጋግሞ ይነበብ!)

#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
3👍2
◈ እንደ ቸርነትህ ◈

እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን(፪)
እንደምህረትህም ይቅርታን ስጠን(፪)
ከኃጢአቴም አንጻኝ ከክፉ በደሌ(፪)

ለዚያች ክፉ ኃጢአት እንዳልሆናት ሎሌ(፪)
እኔስ አበሳዬ በደሌን ሳውቀው(፪)
ከቶ የሚያድነኝ ቸርነትህ ነው(፪)

አንተን ብቻ በደልኩ ክፉም አደረግሁ(፪)
አሁን ይቅር በለኝ ከፊትህ ወደቅሁ (፪)
ከፊትህ ወድቄ ስለምን አንተን(፪)

መውደቄን ተመልከት አምላከ ብርሃን(፪)
አሁን ትባርክ ዘንድ ጉባኤያችንን ጸሎታችንን
ጌታ ሆይ ላክልን መንፈስ ቅዱስን

ጰራቅሊጦስን
አሁን ትጠብቅ ዘንድ ሀገራችንን ኢትዮጵያን
ጌታ ሆይ ላክልን ቅዱስ ሚካኤልን ቅዱስ ገብርኤልን።

ሊቀመዘምራን ኪነጥበብ
======//======

#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
🙏11😢2
"የምንለወጠው ምን ስናደርግ ነው?"

❖ በታመምህ ጊዜ ድካም ይሰማሃል፤ ብርታት ያንስሃል፤ ፊትህም ይገረጣል፤ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህን በአግባቡ ማከናወን ይሳንሃል፤ በዚህ ጊዜም ሕመምህ ምን ያህል እንደ በረታ ሰዎች ያስተውላሉ፤ መታከም እንደሚገባህም ይነግሩሃል፤ ስለዚህ ወደ ሐኪም ትኼዳለህ ወደ ሐኪም የምትኼደው ግን ሐኪሙ ምን እንዲያደርግልህ ነው? አሁን ለሚሰሙህ ስሜቶች የሚሽሩ መድኃኒቶችን እንዲሰጥህ ነው፡፡

❖ ኾኖም ይሰሙህ የነበሩ ስሜቶች ቢሻሉህም ሰውነትህ አሁንም እንደ ደከመ፣ ፊትህ እንደ ገረጣ ከቀረ፣ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህንም በአግባቡ ማከናወን ከተሳነህ በተሰጠህ ሕክምና ደስተኛ ትኾናለህን? አትኾንም። “እውነታው ምንድን ነው?” ስንል ወደ ሐኪሙ የኼድከው የበሽታህን ምንጭ ለመታከም ሳይኾን የበሽታህን ምልክቶች ለማስታገሥ ስለኾነ ነው፤ በሌላ መልኩ ደግሞ የበሽታህ መንሥኤ እስካልታከመ ድረስ የበሽታህ ምልክቶች ለጊዜው ቢታገሡም ቅሉ ፈጽመው ሊወገዱ እንደ ማይችሉ ሐኪሙ በደንብ ያውቃል፡፡

❖ በክርስቶስ ክርስቲያን፣ በወልድ ውሉድ፣ በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳውያን የተባልን እኛም እግዚአብሔር መንፈሳዊ በሽታችንን እንዲያስወግድልን እንሻለን፤ እንደ እውነታው ግን ብዙዎቻችን ወደ እግዚአብሔር ቀርበን እንዲያስወግድልን የምንሻው ምልክቶቹን ነው፡፡

🔘 ለምሳሌ

❖ ችግርን፣ ኀዘንን፣ ቀቢጸ ተስፋንና የመሳሰሉትን እንዲያርቅልን እንፈልጋለን።

❖ እግዚአብሔር ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ የእነዚህ ምክንያት የኾነውንና ሥር የሰደደውን፣ ዋና ምክንያትም የኾነውን መንፈሳዊ በሽታችንን ሳይሽር እነዚህን ምልክቶች ሊያርቅልን አይፈልግም፤ ችግር የሚኾነውም ይህን ጊዜ ነው ምልክቶቹን እንዲያርቅልን ስንደክም ወደ ውሳጤያችን ገብቶ የችግሩን ምንጭ ሊያርቅልን የሚችለውን የእግዚአብሔርን ጸጋ (ኃይልን) አጥብቀን እንቃወማለንና፤ በውሳጤያችን የተሸሸገውን በሽታ ማስወገድ አንፈልግም፤ አመለካከታችን እንዲለወጥ አንፈቅድም፡፡

❖ እውነተኛ ለውጥ የሚመጣውና አማን በአማን የምንታከመው ግን የልባችንን ውሳጤ ለእግዚአብሔር ስንከፍትለትና እርሱም በዚያ በመረቀዘው ቁስላችን ላይ ጽኑ መድኃኒት ሲያስርልን ነው፤ እንዲለወጡ የምንፈልጋቸው ምልክቶች በእርግጥም የሚለወጡት ይህ በልባችን ውስጥ የተደበቀው መንፈሳዊ በሽታችን ሲጠፋ ነው፡፡

"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33)


በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

======//======

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
12👍1