🤩 የልወቅሽ ኢትዮዽያ ክላሲክስ 2ኛ መዳረሻችን በነበረችው ሀዋሳ ውብ የእረፍት ቀናት እና ሩጫ ውድድር ነበረን ✨
2018 ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን✨
ቀጣይ መዳረሻችን - ጅማ - ሚያዝያ 18 ቀን 2018ዓ.ም.
✨ይጎብኙ፣ ይሩጡ፣ ሀገርዎን ይወቁ ✨
#GreatEthiopianRun #DiscoverEthiopiaClassics #2026Registration #6CitiesSeries #LHHM
2018 ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን✨
ቀጣይ መዳረሻችን - ጅማ - ሚያዝያ 18 ቀን 2018ዓ.ም.
✨ይጎብኙ፣ ይሩጡ፣ ሀገርዎን ይወቁ ✨
#GreatEthiopianRun #DiscoverEthiopiaClassics #2026Registration #6CitiesSeries #LHHM
❤18👍2
በየወሩ የሚካሄደው የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ከየካቲት ወር ጀምሮ ተመልሷል።
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም.
በጉጉት የሚጠበቀውና በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ወርሃዊው 'እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ' የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ዳግም ተጀመረ። የፊታችን የካቲት 7 ቀን 2018ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ ውድድር፣ ከተለመደው የስፖርት እንቅስቃሴ እና ውድድር ባለፈ የፍቅረኛሞች ቀንን (Valentine's Day) ታሳቢ ያደረጉ ልዩ ዝግጅቶች ተካተዋል።
ሩጫ ወዳጆች ሁሉ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ባሉበት ቦታ ሆነው በሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ አማካኝነት በነፃ እና በቀላሉ መመዝገብ እንዲችሉ አድርጓል።
በተጨማሪም ወደ እንጦጦ ፓርክ የሚደረገውን ጉዞ ምቹ እና ቀላል ለማድረግ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ለተሳታፊዎች በመሄጃ መንገዳቸው ላይ ያሉትን የአዲስ አበባን አዳዲስ መዳረሻዎች እየጎበኙ ወደ ፓርኩ አድርሶ የሚመልስ የትራንስፖርት አገልግሎት በነፃ አዘጋጅቷል።
የወሩ የሩጫ መርሃ-ግብር «የእኔ አጋር ይሮጣል» (My Valentine is Running) በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ጥንዶች በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን መንገድ ታሳቢ አድርጎ ተዘጋጅተል። ይህንንም ለማበረታታት ጥንዶች የሚፎካከሩበትና አሸናፊዎች የሚሸለሙበት ልዩ ፉክክር አንዱ የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ ጥንዶች በኩሪፍቱ ሪዞርት ልዩ ሽልማቶች ይበረከቱላቸዋል።
ስለ ውድድሩ መግለጫ
የእንጦጦ ፖርክ ሲቢኢ ሩጫ በየወሩ የተለያየ ጭብጥ በመያዝ የሚዘጋጅ የ5ኪ.ሜ. የፓርክ ሩጫ ነው። ውድድሩ ማህበረሰቡ በስፖርት እንዲነቃቃ፣ ተፈጥሮን እንዲያደንቅ እና ሩጫን ቋሚ ልምምዱ እንዲያደርግ ዓላማ ያደረገ ወርሀዊ ውድድር ነው።
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም.
በጉጉት የሚጠበቀውና በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ወርሃዊው 'እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ' የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ዳግም ተጀመረ። የፊታችን የካቲት 7 ቀን 2018ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ ውድድር፣ ከተለመደው የስፖርት እንቅስቃሴ እና ውድድር ባለፈ የፍቅረኛሞች ቀንን (Valentine's Day) ታሳቢ ያደረጉ ልዩ ዝግጅቶች ተካተዋል።
ሩጫ ወዳጆች ሁሉ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ባሉበት ቦታ ሆነው በሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ አማካኝነት በነፃ እና በቀላሉ መመዝገብ እንዲችሉ አድርጓል።
በተጨማሪም ወደ እንጦጦ ፓርክ የሚደረገውን ጉዞ ምቹ እና ቀላል ለማድረግ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ለተሳታፊዎች በመሄጃ መንገዳቸው ላይ ያሉትን የአዲስ አበባን አዳዲስ መዳረሻዎች እየጎበኙ ወደ ፓርኩ አድርሶ የሚመልስ የትራንስፖርት አገልግሎት በነፃ አዘጋጅቷል።
የወሩ የሩጫ መርሃ-ግብር «የእኔ አጋር ይሮጣል» (My Valentine is Running) በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ጥንዶች በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን መንገድ ታሳቢ አድርጎ ተዘጋጅተል። ይህንንም ለማበረታታት ጥንዶች የሚፎካከሩበትና አሸናፊዎች የሚሸለሙበት ልዩ ፉክክር አንዱ የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ ጥንዶች በኩሪፍቱ ሪዞርት ልዩ ሽልማቶች ይበረከቱላቸዋል።
ስለ ውድድሩ መግለጫ
የእንጦጦ ፖርክ ሲቢኢ ሩጫ በየወሩ የተለያየ ጭብጥ በመያዝ የሚዘጋጅ የ5ኪ.ሜ. የፓርክ ሩጫ ነው። ውድድሩ ማህበረሰቡ በስፖርት እንዲነቃቃ፣ ተፈጥሮን እንዲያደንቅ እና ሩጫን ቋሚ ልምምዱ እንዲያደርግ ዓላማ ያደረገ ወርሀዊ ውድድር ነው።
❤7👍1
ለታላቁ ሩጫ አባላት በሙሉ!
ከእናንተ ቤተሰቦቻችን ጋር ሁሌም የምናሳልፋቸው ጊዜያት አስደሳች መሆናቸው ይታወቃል።
በመጪው ቅዳሜ ማለዳ በሚደረገው የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫችን ላይ ደግሞ እየተዝናናን ከታላቁ ሩጫ አባላት ጋር ዕውቅና የምንሰጣጥበት ልዩና አዝናኝ ዝግጅት ይኖረናል።
ስለሆነም በፎቶው ላይ በተጠቀሱት ዘርፎች ውስጥ የምትመርጧቸውን ዕጩ ተሸላሚዎች ለ @Zak_Abdu በመላክ እንድታሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን።
በየዘርፉ ከሚጠቆሙ ተሳታፊዎች መሐከል በተደጋጋሚ የተመረጡትን የመጨረሻ ዕጩዎች እናሳውቃለን።
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ!
ከእናንተ ቤተሰቦቻችን ጋር ሁሌም የምናሳልፋቸው ጊዜያት አስደሳች መሆናቸው ይታወቃል።
በመጪው ቅዳሜ ማለዳ በሚደረገው የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫችን ላይ ደግሞ እየተዝናናን ከታላቁ ሩጫ አባላት ጋር ዕውቅና የምንሰጣጥበት ልዩና አዝናኝ ዝግጅት ይኖረናል።
ስለሆነም በፎቶው ላይ በተጠቀሱት ዘርፎች ውስጥ የምትመርጧቸውን ዕጩ ተሸላሚዎች ለ @Zak_Abdu በመላክ እንድታሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን።
በየዘርፉ ከሚጠቆሙ ተሳታፊዎች መሐከል በተደጋጋሚ የተመረጡትን የመጨረሻ ዕጩዎች እናሳውቃለን።
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ!
❤9👍1
🚨 ማስታወቂያ 🚨
💫የእንጦጦ ፓርክ ሲ.ቢ.ኢ. ሩጫችን ወደ የሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ ተዘዋውሯል 💫
🤩ቀጣይ ሳምንት የካቲት 14 እንገናኝ🤩
✨እንጦጦ ፓርክ ሲ.ቢ.ኢ. ሩጫ✨
የካቲት 14 እንገናኝ!
#EntotoCBERun #GreatEthiopianRun
💫የእንጦጦ ፓርክ ሲ.ቢ.ኢ. ሩጫችን ወደ የሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ ተዘዋውሯል 💫
🤩ቀጣይ ሳምንት የካቲት 14 እንገናኝ🤩
✨እንጦጦ ፓርክ ሲ.ቢ.ኢ. ሩጫ✨
የካቲት 14 እንገናኝ!
#EntotoCBERun #GreatEthiopianRun
👍6❤2🤩2
የ2018 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. 23ኛውን ውድድር ምዝገባ ነገ ይጀመራል
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እሁድ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ2018 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ ውድድር ምዝገባ ዛሬ በይፋ አስጀምራል።
ይህ በየዓመቱ ለሴቶች ብቻ የሚዘጋጀው ሩጫ በቦሌ አትላስ ሆቴል አቅራቢያ በሚገኘው የተለመደ ስፍራ መነሻ እና መድረሻውን በማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር ውድድሩን ያካሒዳል። ውድድሩ የኢትዮጵያ ሴቶችን ስኬት በማብሰር እና ለሌሎች ተምሳሌት በማድረግ 23 ዓመታትን ተጉዟል።
ዛሬ በህያት ሬጀንሲ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተወከሉ የስራ ሃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የውድድሩ አምባሳደር አትሌት መሰረት ደፋር ተገኝተዋል።
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ፣ በውድድሩ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ከዚህም በላይ ማሳደግ እና ማስፋፋት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ዳግማዊት ሲናገሩ "የውድድሩን መመዝገቢያ ዋጋ ለሁሉም ሰው ተደራሽ እንዲሆን በማሰብ፣ ተመጣጣኝ ለማድረግ የምንችለውን ሁሉ እያደረግን ነው" ብለዋል። ኤም-ፔሳ (M-Pesa) መተግበሪያውን ተጠቅመው ለሚመዘገቡ የ15% ቅናሽ ፤ እንዲሁም ዳሽን ባንክ በሱፐር አፑ ለሚመዘገቡ የ10% ቅናሽ እንዳዘጋጁም አያይዘው ተናግረዋል።
የስያሜ አጋር የሆነውን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በመወከል የብራንድ እና ኮሙኒኬሽን ክፍል ሃላፊ የሆኑት ሔርሜላ ይልማ በበኩላቸው፡ "እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ የሴቶችን ጥንካሬ የምናንጸባርቅበት፣ ድምፃቸውን የምናሰማበት እና ስኬታቸውን የምናከብርበት የዚህ ዓመታዊ ውድድር ዋና ስፖንሰር በመሆናችን ትልቅ ኩራት ይሰማናል። ጠንካራ አጋርነታችንም ወደፊት እንደሚቀጥል ላረጋግጥ እወዳለሁ" ብለዋል።
የዘንድሮው ውድድር በዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ (DKT Ethiopia) የቀረበውን ‘በመላ ኑሪ - በኮንፊደንስ ሩጪ’ የሚል የውድድር መልዕክት ይተላለፍበታል። በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ ዳይሬክተር አዲቲያ ፑትራ "ዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ የውድድሩ የመልዕክት አጋር በመሆኑ ደስታ ይሰማዋል። ‘በመላ ኑሪ - በኮንፊደንስ ሩጪ’ የሚለው መሪ ቃል፣ በቂ ግንዛቤ ያለው፣ የስነ-ተዋልዶ ጤና ምርጫ በራስ መተማመንን እና ዕድሎችን ይፈጥራል የሚለውን ዕምነታችንን ያንጸባርቃል። በኢትዮጵያ ያልተሟላ የቤተሰብ ምጣኔ ፍላጎት አሁንም እንደ ፈተና ቢቀጥልም፣ ይህ አጋርነት የጤና ግንዛቤን ከማህበረሰብ ተሳትፎ ጋር ለማስተሳሰር ይረዳል" ብለዋል።
ለ23ኛው ዓመት የ2018 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ ምዝገባ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በኤም-ፔሳ፣ በዳሽን ሱፐር አፕ እና በአራት የሳፋሪኮም ሱቆች ይጀምራል። የዘንድሮው የውድድር መመዝገቢያ ዋጋ 590 ብር ነው። ውድድሩ በሳፋሪኮም፣ ኤም-ፔሳ፣ ዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ፣ ዳሽን ባንክ፣ አክቲቭ (Aktive)፣ የአየርላንድ ኤምባሲ፣ ዩኒሴፍ (UNICEF)፣ ፋብ ውበት ሳሙና፣ ቶፕ ውሃ፣ ህያት ሬጀንሲ፣ ኢ.ቲ.ቪ እና አፍራን ሆስፒታል አጋርነት የተዘጋጀ ነው።
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እሁድ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ2018 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ ውድድር ምዝገባ ዛሬ በይፋ አስጀምራል።
ይህ በየዓመቱ ለሴቶች ብቻ የሚዘጋጀው ሩጫ በቦሌ አትላስ ሆቴል አቅራቢያ በሚገኘው የተለመደ ስፍራ መነሻ እና መድረሻውን በማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር ውድድሩን ያካሒዳል። ውድድሩ የኢትዮጵያ ሴቶችን ስኬት በማብሰር እና ለሌሎች ተምሳሌት በማድረግ 23 ዓመታትን ተጉዟል።
ዛሬ በህያት ሬጀንሲ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተወከሉ የስራ ሃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የውድድሩ አምባሳደር አትሌት መሰረት ደፋር ተገኝተዋል።
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ፣ በውድድሩ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ከዚህም በላይ ማሳደግ እና ማስፋፋት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ዳግማዊት ሲናገሩ "የውድድሩን መመዝገቢያ ዋጋ ለሁሉም ሰው ተደራሽ እንዲሆን በማሰብ፣ ተመጣጣኝ ለማድረግ የምንችለውን ሁሉ እያደረግን ነው" ብለዋል። ኤም-ፔሳ (M-Pesa) መተግበሪያውን ተጠቅመው ለሚመዘገቡ የ15% ቅናሽ ፤ እንዲሁም ዳሽን ባንክ በሱፐር አፑ ለሚመዘገቡ የ10% ቅናሽ እንዳዘጋጁም አያይዘው ተናግረዋል።
የስያሜ አጋር የሆነውን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በመወከል የብራንድ እና ኮሙኒኬሽን ክፍል ሃላፊ የሆኑት ሔርሜላ ይልማ በበኩላቸው፡ "እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ የሴቶችን ጥንካሬ የምናንጸባርቅበት፣ ድምፃቸውን የምናሰማበት እና ስኬታቸውን የምናከብርበት የዚህ ዓመታዊ ውድድር ዋና ስፖንሰር በመሆናችን ትልቅ ኩራት ይሰማናል። ጠንካራ አጋርነታችንም ወደፊት እንደሚቀጥል ላረጋግጥ እወዳለሁ" ብለዋል።
የዘንድሮው ውድድር በዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ (DKT Ethiopia) የቀረበውን ‘በመላ ኑሪ - በኮንፊደንስ ሩጪ’ የሚል የውድድር መልዕክት ይተላለፍበታል። በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ ዳይሬክተር አዲቲያ ፑትራ "ዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ የውድድሩ የመልዕክት አጋር በመሆኑ ደስታ ይሰማዋል። ‘በመላ ኑሪ - በኮንፊደንስ ሩጪ’ የሚለው መሪ ቃል፣ በቂ ግንዛቤ ያለው፣ የስነ-ተዋልዶ ጤና ምርጫ በራስ መተማመንን እና ዕድሎችን ይፈጥራል የሚለውን ዕምነታችንን ያንጸባርቃል። በኢትዮጵያ ያልተሟላ የቤተሰብ ምጣኔ ፍላጎት አሁንም እንደ ፈተና ቢቀጥልም፣ ይህ አጋርነት የጤና ግንዛቤን ከማህበረሰብ ተሳትፎ ጋር ለማስተሳሰር ይረዳል" ብለዋል።
ለ23ኛው ዓመት የ2018 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ ምዝገባ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በኤም-ፔሳ፣ በዳሽን ሱፐር አፕ እና በአራት የሳፋሪኮም ሱቆች ይጀምራል። የዘንድሮው የውድድር መመዝገቢያ ዋጋ 590 ብር ነው። ውድድሩ በሳፋሪኮም፣ ኤም-ፔሳ፣ ዲ.ኬ.ቲ. ኢትዮጵያ፣ ዳሽን ባንክ፣ አክቲቭ (Aktive)፣ የአየርላንድ ኤምባሲ፣ ዩኒሴፍ (UNICEF)፣ ፋብ ውበት ሳሙና፣ ቶፕ ውሃ፣ ህያት ሬጀንሲ፣ ኢ.ቲ.ቪ እና አፍራን ሆስፒታል አጋርነት የተዘጋጀ ነው።
❤12👍2