ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
1.8K subscribers
847 photos
55 videos
20 files
397 links
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ።
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።

We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Download Telegram
የክፉ ሰው ምላስ*

ምሰሶው ተማግዶ ጎጆኣችን ነደደ
ውበት ትዝታው ላይ ፍም ሳት ወረደ
ጢሱ በአይን ሞላ ነበርን ሸፈነው
አሁን የቆምንበት ጥላሸት አመድ ነው ፡፡
ብለን ተክዘን ሳል
ካመዱ ላይ ቆመን
አንድ እውነት ገረመን
አንድ ሀቅ አመመን
እዚህ እኛ እውነት ላይ
እፍቅራችን ሞት ላይ
ነፋስ ስራው በዛ
ከአመዱ ቆንጥሮ ሰው ፊት እየነዛ ! ! !

©መቅደስ ሞገስ

#መቅደስ_ሞገስ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
Cork Cellar Wine Bar in partnership with Uncle Don Authentic Jamaican Jerk BBQ invites you to join us to Celebrate Kwanzaa from December 26-January 1. Happy Kwanzaa 🎊🎉

Poets invited!

https://t.me/GitemSitem
"የዮሴፍ ሰቦቃ አስደናቂ ሥዕሎች ከዕይታ ሳይወርዱ እንድታይዋቸው እጠቁማለሁ" ሲል ሰይፉ ወርቁ በ ጠብታ ማር - ጣፋጭ ሃሳቦች ግሩፑ ግብዣውን አቅርቧል!

ፈንዲቃ ካዛንቺስ በማንኛውም ሰዐት ከቀን እስከ ምሽት በሚመቻችሁ ሰዐት ሄዳችሁ ጎብኙት!


https://t.me/GitemSitem
https://www.nebeb.com/
እናንብብ፣ እንወያይ፣ ነፃ እንውጣ። lets read, let's discuss, let's get liberated.
|የተመኟት|
[በዜማ]
አ....ት..ራ....ወጡ
ከ...ትግል.. ውጡ
ተዓ`ምሯን አድምጡ
(ያገኟት... «አ...ሜን»)
|የተመኟት|
[በዜማ]
ሙት አታስታሙ
በድን አትሳሙ
መጥታለች ቁሙ
ተዓምሯን ስሙ።
(ያገኟት... «አ...ሜን»)
[[የተኛት]]
|በሹክሹክታ|
ከሽ... ኮሽ...
ከሽ..ከሽ...
ሿሿ... ሿሻ... ሻሻ
ደረት ማንከሽከሻ
ተንጋሎ እሚቆላ
ቡናማ ገላዋ
ባርያ ያደርገኛል፡ ጌትነትም ብሻ።
ደረት ማንከሽከሻ...
ቡናዋን ታቅፎ
በእሳት ላንቃ መሃል፡ ግራ ቀኝ ይሰግራል
ጠረኗ እየጤሰ፡ እንኳንስ ጎረቤት፥ መላዕክት ይጠራል
( ሚኻኤል ና ቡና ጠጣ!)
ከከከሽ... ከከከሽ
ከሰማይ ተልከሽ...
በእኩለ ሌሊት... በተክሌ ዝማሜ
ስንጋደድ ስትቆሚ... ስትንጋደጅ ቆሜ
ከጉልበቴ ቀድሞ እያጠረኝ እድሜ
ከምኔው ፃይ ወጣች? መንጋት "አፈር ድሜ!"
ከሽሽ...ሻ... ከሸሽ...ሻ
ደረት ማንከሽከሻ
ቡናዋ እህል ውሃ... ነፍስ መመለሻ...
ራብ ራብ ቢለኝ... ቢታጠፍ አንጀቴ
አካሌ ጎጆዋ... ገላዋ ማጀቴ
ብዬ ወደ እሳቷ ... እጄን መዘርጋቴ
ከዛ መፈጀቴ...
ይህች... የፍል ውሃ.. ይህች ትኩስ እህል
ጣዕሟን አልደርስበት፡
መልኳም ይርቀኛል፡መፋጀቷን ባኽል?!
ብረት ምጣድ ደረት
ቡናዋን ታቅፎ
በእሳት ላንቃ መሃል፡ ይተረማመሳል
ጠረኗ እየጤሰ፥ ሰማይ ላይ ይደርሳል
የስንት መ'ላክ ናላ፡ በአምሮት ይፈርሳል?
( ገብርኤል ና ቡና ጠጣ!)
ብረት ምጣድ ደረት
የሚጋፍ በወረት
ቡና የመሰለ ሰማያዊ መና
ያሳርር ጀመረ መቁላቱ ቀረና...
እሳት መልክ ይሰራል
ለቅጽበት ያዘሉት፡ ጀርባ ላይ ይቀራል
ለጌጥ የተኳሉት ተነቅሶ ይኖራል
ታዲያ ማን ይፈራል?
ከፍሬሽ ተተፋሽ.. ያረረውን ደፋሁ
ከማንከሽከሻዬ፡ እስክትወጪ ለፋሁ
አጠፋሪስ ቡናሽ፡
ቀልቤን አቦነነው፡ አቅሌን ስቼ ጠፋሁ።
አትውረጂ ልልሽ፡ ከየት ይምጣ ልሳን?
ግርጅፉን ሰውዬ፡
ጡትሽ ያደርገኛል፡ አንድ ፍሬ ህፃን
እያብረቀረቀ፡
ቆዳሽ ድንግዝግዙን፡ ሲያጠፋው አይቼ
ቢቀላቀልብኝ፡
ቀድቼ ሰጠሁት፡
ተጣለ ያሉትን፡ መላዕክ ጠርቼ
(ሳጥናኤል ና ቡና ጠጣ)
ረካሁ
ያጣሁትን ተካሁ
ከሞት እስከፍቅር፡
ያለውን ርቀት፡ በከንፈሬ ለካሁ
በስተገላሽ በኩል፡
ባንድ ሌት መላክም፡ ሰይጣንንም ነካሁ
ምን ቀረ ከእንግዲህ?
ምኞት ወዲያ ማዶ፡ እጣፈንታ ወዲህ
ምን በጀን ከእንግዲህ?
መላኩን ካወደው፡ ሰይጣኑን ከጠራ
ከሌቱ ቡናችን፡ ትውስታ እንቁጠራ!
ከማንከሽከሻው ላይ፡ ትዝታ እንቆንጥራ
ልክ እንደዛች ሌሊት፥
ይች ዘልዛላ ህይወት፡ እድሜዋ ይጠ`ራ!
(ትዝታ ና ቡና ጠጣ )

©ረድኤት አሰፋ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Koleka Putuma is a Cape Town-based performance poet whose poetry centres around her identity as a black woman in South Africa — a country with a long history of spoken word performance being used as a tool to reach social goals. Putuma continues this tradition through her work, facilitating writing and dialogue workshops at schools, community projects & interfaith programmes in the Cape Town area, plus supporting up and coming women artists through the theatre company she co-founded, Velvet Spine.

“Silence is a thing for us black women,” she said. “The goal for me is to write myself into something, be it into existence. Just to talk.” She’s already won the PEN SA Student Writing Prize for her poem, Water, and has been named one of Africa’s top 10 poets.

www.one.org
አቆነጃጀትሽ
ለማንም ያልገባ
ከማንም ያልኖረ
ተሸዋጅ ወንዶችን
ሁሉ እያባረረ
ምትኃቱ ሆኖ
ለሁሉ ሰው ግራ
ከረፈደ ኋላ
መልሶ ‘ሚጣራ

ሩዲ ፍራንሲስኮ
(ነጻ ትርጉም፦ በሰይፈ ተማም ተብዬው)
#rudy #rudy_francisco #poetry
#Creative_ Futures is back with the second round!

Are you up for joining the creative and innovation month program where you get to innovate while collaborating with other #creative practitioners in the #imagesector, with a chance to showcase your innovation, and win up-to 100,000 ETB.

If you are a creative in the image sector with an innovative project idea we invite you to Apply!