[ስለራሥ ጥላ እና ስለነጭ ድመት ምልኪ]
(ካልጻፍኳቸው፣ ደጋግሜ ጽፌ ቸል ካልኳቸው...)
ትዕይንት አንድ፤
ከመወራጨት ወደመዳህ
ከመዳህ ወደመንገድ ወደመራመድ
ከመቀልጠፍ እስከመንቀራፈፍ
እስከመንከርፈፍ
እግር አንድ ጉዞ አንድ መንገድ
ሙሉ ሕይወት ጀምሮ እስከማገባደድ...
_____
ባካና እግረኛ መሆኔን መች እክዳለሁ
እስከመቆም እራመዳለሁ
ምሥጋና ለራሴ
ዓለምን ለተሸከመ ሥጋና
እሱን ለተሸከመች ነፍሴ
[ለምሥጋና በቀናሁበት
ነጭ ድመት ጎኔ ቆማ
ድምጿን አጥፍታ ወይ ድምጿ ጠፍቷት
መንገዴን ትቼ ቆምኩ
ሠላም ልፈልግ የወጣሁበት ዘንድ
ሠላም አጥቼ ቀረሁ]
እርቃንን ውሸት ነው እያሉኝ
እውነቴን ኩታ አልብሼ
ስሞት ይሆነኛል ያልሁትን እንባ
ለባይተዋር መኖር አፍስሼ
ስመለስ
ጥላዬን በቀትር አጣሁት
[ድመቷ እንዳፈጠጠች ጎኔ ቆማለች
የቆመ የመሰለኝ በድኔ
ቀዝቃዛ መሬት ተደላድሏል]
የተሸከምኩት ዓለም ባዶ ነው
የተሸክምኩት እኔ ባይተዋር ነኝ
ሸክሙን አንስቼ ሳዝለው
በመቅለል ፈንታ ከበደኝ
[የሌለ ቢቀል ብዬ አለመሆንን ብመርጥ
ከመሆን የሚከብድ
እግሬን አንስቼ ብገፋ
ጥላ የሚያሳጣ
የማያደርስ መንገድ
ነጯ ድመት ቆረጠቺኝ!]
ባይተዋሬን ይዤ ብመጣ
ያንቺን ባይተዋር አልሞላ
ሸክሜን ይዤ መጥቼ
ከሸክም ውጪ አልሆንሽ
ምን ትያለሽ?
ዓለም፣ እኔ እንከብዳለን?
ይቅርብን
በእንባ እንባ ከማጠብ ውጪ
ምን እንተጋገዛለን?
______
መዝጊያ ትዕይንት፤
በወፋፍራሙ የተጻፈ
ድንጋይ ላይ የጠረበ
ያላፊ ሠው ጽሑፍ
እመኚኝ
ባዶው ከሙሉው ይከብዳል
ባይተዋር የሆነ ልቤ መሐል
ተቃርኖ ውሎ ካረፈደ
ሞት ያኔ ነው ይዞኝ የሄደ
ብርሃኔን አከሰምኩ
ጥላዬ ከመሬት ጠፋ
ብጎድል ብሞላ ሸክምሽ ነኝ
ምን ይዤ እመጣለሁኝ?
ዝም ከምንለው ውጪ ምን አለን?
ምን እንተጋገዛለን?
----
[ እውነት እንግዲህ ባይተዋርነቴ ነው
እርቃኔን ተንጋልዬ
ትዝታዋን ብቻ ተጎናጽፌ ተንጋልያለሁ
በድኔን እንዲሁ ተዉት
መች መቃብር ይችለኛል
አትቅበሩኝ እነሳለሁ
ተጎትቼ ተጠግቼ ሄጄ በሯን እመታለሁ]
© ማርቆስ
(ካልጻፍኳቸው፣ ደጋግሜ ጽፌ ቸል ካልኳቸው...)
ትዕይንት አንድ፤
ከመወራጨት ወደመዳህ
ከመዳህ ወደመንገድ ወደመራመድ
ከመቀልጠፍ እስከመንቀራፈፍ
እስከመንከርፈፍ
እግር አንድ ጉዞ አንድ መንገድ
ሙሉ ሕይወት ጀምሮ እስከማገባደድ...
_____
ባካና እግረኛ መሆኔን መች እክዳለሁ
እስከመቆም እራመዳለሁ
ምሥጋና ለራሴ
ዓለምን ለተሸከመ ሥጋና
እሱን ለተሸከመች ነፍሴ
[ለምሥጋና በቀናሁበት
ነጭ ድመት ጎኔ ቆማ
ድምጿን አጥፍታ ወይ ድምጿ ጠፍቷት
መንገዴን ትቼ ቆምኩ
ሠላም ልፈልግ የወጣሁበት ዘንድ
ሠላም አጥቼ ቀረሁ]
እርቃንን ውሸት ነው እያሉኝ
እውነቴን ኩታ አልብሼ
ስሞት ይሆነኛል ያልሁትን እንባ
ለባይተዋር መኖር አፍስሼ
ስመለስ
ጥላዬን በቀትር አጣሁት
[ድመቷ እንዳፈጠጠች ጎኔ ቆማለች
የቆመ የመሰለኝ በድኔ
ቀዝቃዛ መሬት ተደላድሏል]
የተሸከምኩት ዓለም ባዶ ነው
የተሸክምኩት እኔ ባይተዋር ነኝ
ሸክሙን አንስቼ ሳዝለው
በመቅለል ፈንታ ከበደኝ
[የሌለ ቢቀል ብዬ አለመሆንን ብመርጥ
ከመሆን የሚከብድ
እግሬን አንስቼ ብገፋ
ጥላ የሚያሳጣ
የማያደርስ መንገድ
ነጯ ድመት ቆረጠቺኝ!]
ባይተዋሬን ይዤ ብመጣ
ያንቺን ባይተዋር አልሞላ
ሸክሜን ይዤ መጥቼ
ከሸክም ውጪ አልሆንሽ
ምን ትያለሽ?
ዓለም፣ እኔ እንከብዳለን?
ይቅርብን
በእንባ እንባ ከማጠብ ውጪ
ምን እንተጋገዛለን?
______
መዝጊያ ትዕይንት፤
በወፋፍራሙ የተጻፈ
ድንጋይ ላይ የጠረበ
ያላፊ ሠው ጽሑፍ
እመኚኝ
ባዶው ከሙሉው ይከብዳል
ባይተዋር የሆነ ልቤ መሐል
ተቃርኖ ውሎ ካረፈደ
ሞት ያኔ ነው ይዞኝ የሄደ
ብርሃኔን አከሰምኩ
ጥላዬ ከመሬት ጠፋ
ብጎድል ብሞላ ሸክምሽ ነኝ
ምን ይዤ እመጣለሁኝ?
ዝም ከምንለው ውጪ ምን አለን?
ምን እንተጋገዛለን?
----
[ እውነት እንግዲህ ባይተዋርነቴ ነው
እርቃኔን ተንጋልዬ
ትዝታዋን ብቻ ተጎናጽፌ ተንጋልያለሁ
በድኔን እንዲሁ ተዉት
መች መቃብር ይችለኛል
አትቅበሩኝ እነሳለሁ
ተጎትቼ ተጠግቼ ሄጄ በሯን እመታለሁ]
© ማርቆስ
Forwarded from LinkUp Addis
Gitem Sitem and Krinfud Digitals are partnering up to organize a festival titles Hibrekal Festival on Saturday 09 April 2022 at Fana Park. The event will feature poetic performances, music, live art, short plays and other performances. Entrance fee is ETB 150. Stay tuned for more info. @linkupaddis
Forwarded from Getsh 🇪🇹🇪🇹metmku🇪🇹🇪🇹
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
The Mosaic Hotel is hosting a professional networking and inspirational event on Saturday 14 April 2022. The event, which will be titled Self-Reconciliation for Generation Building will be hosted by Fitsum Atnafwerk, and will feature prominent opinion leaders and social influencers. Doors will open at 4:30pm, and entrance fee is ETB 200.
@linkupaddis
@linkupaddis
Forwarded from ሊያ አበበ
"ትክክል"
~~
ትክክሉን ሁላ
ማነው ልክ ያረገው?
ልክ አይደለም ብሎስ
ማነው የደነገገው?
ሁሉም ትክክል ነው
ሁሉም እንደራሱ፣
በተረዳው መጠን
መልሱን መመለሱ፡፡
የማነው ትክክል
እነማን?የትኞች?
በወጣኸው ዳገት
ባለፍኩት መንገዶች፡፡
የየቅሉ መንገድ
ስህተት የተባለው፣
ያረከው ያረኩት
ሁሉም ትክክል ነው፡፡
በአንተነትህ መዝን
በእኔነቴ አውጣኝ፣
በዳገትህ ስፈር
በመንገዴ ለካኝ፡፡
ሊያ አበበ✍
ትክክሉን ሁላ
ማነው ልክ ያረገው?
ልክ አይደለም ብሎስ
ማነው የደነገገው?
ሁሉም ትክክል ነው
ሁሉም እንደራሱ፣
በተረዳው መጠን
መልሱን መመለሱ፡፡
የማነው ትክክል
እነማን?የትኞች?
በወጣኸው ዳገት
ባለፍኩት መንገዶች፡፡
የየቅሉ መንገድ
ስህተት የተባለው፣
ያረከው ያረኩት
ሁሉም ትክክል ነው፡፡
በአንተነትህ መዝን
በእኔነቴ አውጣኝ፣
በዳገትህ ስፈር
በመንገዴ ለካኝ፡፡
ሊያ አበበ✍
❤1
አታውቂም?
ጓደኛ መስታወት የኔነት ነጸብራቅ:
በሩቅም እያለ ከልብ ውስጥ የማይርቅ:
ጓደኛ ፈውስ ነው የሚስጥሬ አለም:
እንደ ብቸኝነት ከቶ የወጋኝ የለም:
እኔ አንቺን ካጣው ሞቴ ነው አታውቂም?
:
ኦ ኦ ኦ ትችላለህ አትበይኝ አልችልም ግድየለም:
አጉል ተስፋ አትስጪኝ ድጋሜ አልታመም:
ብቸኝነት ጎድቶኝ መቼም አላገግም:
አስበሽዋል...ሊያውም በድጋሜ ስጎዳ ስሰበር:
ምን የሚሉት ቁስል ወይ ላይድን ወይ ላይ ሽር:
አረ ወይኔ....ልቤ ለይ ሲወጣ እንዴትስ ሊረሳ:
ሰው የማጣት ቁስል ዘላቂ ጠባሳ::
ይድናል አትበይኝ ጊዜውን ጠብቆ:
ትዝታ እያለበት ቁስል መቼ ደርቆ:
ይታያል ብለሽ ነው ሰውን ያጣ አለም:
አንድም ባዶ ሸክም:
ሌላም
በቁሙ የሞተ መሆኑን አታውቂም???
©️ከ ሚኪ ሳ.
ጓደኛ መስታወት የኔነት ነጸብራቅ:
በሩቅም እያለ ከልብ ውስጥ የማይርቅ:
ጓደኛ ፈውስ ነው የሚስጥሬ አለም:
እንደ ብቸኝነት ከቶ የወጋኝ የለም:
እኔ አንቺን ካጣው ሞቴ ነው አታውቂም?
:
ኦ ኦ ኦ ትችላለህ አትበይኝ አልችልም ግድየለም:
አጉል ተስፋ አትስጪኝ ድጋሜ አልታመም:
ብቸኝነት ጎድቶኝ መቼም አላገግም:
አስበሽዋል...ሊያውም በድጋሜ ስጎዳ ስሰበር:
ምን የሚሉት ቁስል ወይ ላይድን ወይ ላይ ሽር:
አረ ወይኔ....ልቤ ለይ ሲወጣ እንዴትስ ሊረሳ:
ሰው የማጣት ቁስል ዘላቂ ጠባሳ::
ይድናል አትበይኝ ጊዜውን ጠብቆ:
ትዝታ እያለበት ቁስል መቼ ደርቆ:
ይታያል ብለሽ ነው ሰውን ያጣ አለም:
አንድም ባዶ ሸክም:
ሌላም
በቁሙ የሞተ መሆኑን አታውቂም???
©️ከ ሚኪ ሳ.
❤4👍1
ወሎ ሰፈር ግርጌ
ከጎተራ ራስጌ
ስሽከረከር ብውል ጠፍቶብኝ መንገዴ
በቀዝቃዛ ውሃ እንደ እሳት መንደዴ
ለሰው ልጅ ቢደንቀው አውሬ ማላመዴ
ይኸው እገኛለው
የአህያዬን በረት ለጅብ አጋርቼ
ነባቢቱን ስንቅ ዱዳውን አውርቼ
የሚሽቴን መቀነት ለውሽማ አውርሼ
ጫካ እባርካለሁ ህንጻ ላይ ቀድሼ
©️እስሩ ገብሩ
ከጎተራ ራስጌ
ስሽከረከር ብውል ጠፍቶብኝ መንገዴ
በቀዝቃዛ ውሃ እንደ እሳት መንደዴ
ለሰው ልጅ ቢደንቀው አውሬ ማላመዴ
ይኸው እገኛለው
የአህያዬን በረት ለጅብ አጋርቼ
ነባቢቱን ስንቅ ዱዳውን አውርቼ
የሚሽቴን መቀነት ለውሽማ አውርሼ
ጫካ እባርካለሁ ህንጻ ላይ ቀድሼ
©️እስሩ ገብሩ
👍1
የኅብረቃል ድምቀት የነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!!!
ፌስቲቫሉን ስፖንሰር በማድረግ እውን እንዲሆን ያገዘን ሐረር ቢራም ውሎ ይግባ!
ፈለክ በአጋርነት አብሮን ስለነበረም ከልብ እናመሰግናለን!
Shout out to the beautiful HibreQal crowed and all who were there!!! The turn out was great, it didn't look like a first edition!
Thank you Harar Beer for sponsoring our unique festival!
Felek Notebooks, we are proud to call you a partner in pulling off this one of a kind event!
#HibreQal_Festival #World_Poetry_Day #HibreQal2022 #Poetry
#Harar #Felek #Poetic_Saturdays #LinkUp_Addis
#Krinfud #GitemSitem
ፌስቲቫሉን ስፖንሰር በማድረግ እውን እንዲሆን ያገዘን ሐረር ቢራም ውሎ ይግባ!
ፈለክ በአጋርነት አብሮን ስለነበረም ከልብ እናመሰግናለን!
Shout out to the beautiful HibreQal crowed and all who were there!!! The turn out was great, it didn't look like a first edition!
Thank you Harar Beer for sponsoring our unique festival!
Felek Notebooks, we are proud to call you a partner in pulling off this one of a kind event!
#HibreQal_Festival #World_Poetry_Day #HibreQal2022 #Poetry
#Harar #Felek #Poetic_Saturdays #LinkUp_Addis
#Krinfud #GitemSitem
👍1🔥1
የኅብረቃል ድምቀት የነበሩት መባቻዎች ደብረማርቆስ ላይ ቀጣይ ድግስ አላቸው
ለምን ከከተማ ግርግር አፍታ ወስደን ወጣ ብለን የነሱን ልዩ ቀለም ታድመን በስጦታቸውም ተደምመን አንመለስም?
ለምን ከከተማ ግርግር አፍታ ወስደን ወጣ ብለን የነሱን ልዩ ቀለም ታድመን በስጦታቸውም ተደምመን አንመለስም?