ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
1.83K subscribers
842 photos
55 videos
20 files
394 links
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ።
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።

We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Download Telegram
ግጥም ሲጥም ፭ - Gitem Sitem 5

የክፍት መድረክ ክበብ

መግቢያው ላይ በመመዝገብ በቻ የፈለጋችሁትን፣ ልባችሁ ያላችሁንና ነፍሳችሁ የወደደችውን የምታቀርቡበት።
የመጀመሪያ ጊዜያችሁ ከሆነ በታላቅ ደስታ እንቀባላችኋለን። የመድረክ ልምድ ያላችሁ ከሆነ ደግሞ በታላቅ ደስታ እንቀበላችኋለን!

ተመዝግቡ - አቅርቡ!

An Open Mic Circle of Poetry and Fun

Sign up and perform whatever is in your heart!
If you are a first timer for stage, that's a win for us! If you are well experienced, that's still our win!
Share the stage with one of the amazing poets in town.

Sign up and perform

#gitemsitem #heransyoga #seifetemam #shifta
#ትሁት_ካልሆንክ_ጠቢብ_አይደለህም!
• እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ትሁት ካልሆንክ #ጥበብን_አታውቃትም__ጥበብም_አንተን_አታውቅህም
...
ጠቢብ የብርሐን ተምሳሌት ነው። ብርሐን ተፈጥሮው መብራት ነው። ፀሐይ የምትለየው በብርሐኗ ለሌሎች መትረፍ ነው። በመስጠት። ፅልመትን በመግፈፍ። የጠቢብ ባህርዩ የሌሎችን መልካምነትና ውበት ገላልጦና አጋልጦ ማሳየት ነው።

ፀሐይ ፅልመትን ስትገፍ፣ 'ጀብድ ሰራሁ' ብላ አትዘግብም። ጮሃም አትናገርም። ቅንነት ተፈጥሮዋ ነውና። ጠቢብም የልቦና ብርሐን ነውና፤ የሌሎችም ፅልመት በቅንነት ብርሐኑ፣ በፍቅር ፀሐዩ ገልጦ ውበታቸውን ያጎላል እንጂ ስለ ፅልመታቸው እየተረከ ገናናነቱን አይዘግብም።

መጀመሪያ ሰው ሆኖ መቅረብ ይቀድማል። ከዚያም ፍቅርና ብርሐናችንን መግለጥ። በፍቅርና በብርሐናችን ሁሉን ማቀፍ መቻል። ለሁሉ ማብራት፤ ሁሉን ማክበር። እኛ ብርሐን ነን አንልም። ሌሎች በብርሐናችን ያውቁናል እንጂ። እኛ ስለሰዎች ፅልመት አናወራም። ሰዎች ስለብርሐናችን ኃይል ይናገራሉ እንጂ።

ጠቢብነት በትህትና ይመዘናል። ሌሎችን አክብሮ በመውደድ ኃይል። ሁሉን መቀበል፣ ሁሉን መውደድ በመቻል ኃይል።

ጠቢብ ድክመት ነቃሽ አይደለም። ደካማውን አበርቺ፣ የተሰወረውን ጥንካሬ ነቅሶ አውጪ እንጂ። በትችት አይጠመድም። በማሳነስ ገዝፎ ለመታየትም አይሞክርም። ማግዘፍ እንጂ ማኮሰስ የባህርይ ገንዘቡ አይደለም።

ጠቡብ ቡድን የለውም። ፀሐይ መንደር መርጣ፣ ያ ክፉ ያኛው ደግ ብላ አዳልታ እንደማታበራ ሁሉ። ለበዳይም ለተበዳይ፣ ለገፊም ለተገፊም በእኩል ብርሐኗን ትለግሳለች። ተፈጥሮዋ መስጠት ብቻ ስለሆነ። #ትህትና

እውነት እውነት እልሃለሁ። ሰዎችን የምትጠላ፣ የምታበላልጥና ስህተታቸውም ነቅሰህ በጎአቸውን የምትጋርድ ከሆንክ፣ ጥበብን አታውቃትም፤ ጥበብም አንተን አታውቅህም።

#ትህትና__ትህትና
#የግዝፈቶች_አክሊል_የቅንነት_ካባ
#ባክህ__ልቤ_ግባ!

#ፍቅር_በሌለበት_ጥበብ
#ጥበብ_በሌለበትም_ፍቅር_የለም

ጠቢብ መጀመሪያ ሰው ነው። መጀመሪያ የሁሉ ወዳጅ። ሁሉን አክባሪ። ሁሉን አበርቺ። ሁሉን አግዛፊ። ሚዛኑ ለሐሜት የማይታዘዝ። ልቡ ለአድልዎ የማይታጠፍ። የእነእገሌ አደግዳጊ፣ የእነእገሌ ጠላት አይደለም። የጠቢብ ነፍስ ጥላቻን ትጠየፋለች። የጠቢብ ልብ ከፍቅር በቀር አይዘምርም። የጠቢብ ዐይኖች ከፅልመት ውስጥ ብርሐንን፣ ከድክመት ውስጥ ብርታትን፣ ከጥመት ውስጥ ቅንነትን፣ ከፀያፍ ውስጥ ውበትን መንጥረው ያያሉ።

ጠቢብ ሁሉን ያለ ጥቅም ይወዳል። ተሥፋን፣ ፍቅርን፣ ክብርን፣ ነፃነትን ይለግሣል። ለማቅናት አያፈርስም፤ የፈረሰውን ያቀናል እንጂ። ለመወደድ አይወድም። ለመቀበል አይሰጥም፤ መውደድ ሰጥቶ መውደድ ይበዛለታል እንጂ።

ጠቢብ ውዳሤ ከንቱን ይፀየፋል። በማዕረግ አይታሰርም። በስምና በክብር ኬላ ከሰዎች መነጠል አይፈልግም። የትም፣ እንዴትም፣ ከማንም፣ ከምንም፣ ሁሌም ሰው አክሎ መገኘት ይችልበታል። ጎዝጉዙልኝ፣ አንጥፉልኝም አይልም። በተገኘበት ድባቡ ይነግሣል እንጂ። ፍቅሩ፣ ትህትናውና አክብሮቱ በመገኛው አድባር ያደርጉታል እንጂ።

ጠቢብ ዋርካ አይደል? ሁሉን ሰብሳቢ። በግዝፈቱ የሚያስመካ። በቅርንጫፎቹ የሚያስጠልል። ጥላ የሚሆን፣ የሚያሳርፍ፣ ተራማጁንም፣ በራሪውንም፣ ተሳቢውንም፣ አመንዣጊውንም፣ ሁሉን የሚያስጠጋ - ዋርካ ጠቢብ አይደል? ጠቢብም ዋርካ። ነፋስ የማይጥለው ሥሩ ጥልቅ፤ ዝናብ የማይጥለው ግንዱ ጥብቅ።

ትሁት ካልሆንክ ጥበብ ትጠየፍሃለች። ፍቅርም፣ ፍትህም ብርሐንም አይበቅሉብህም።

#ትህትና_ትህትና
#የግዝፈቶች_አክሊል__የቅንነት_ካባ
#ባክህ_ልቤ_ግባ!

#ሠይፈ__ወርቅ
Forwarded from Poetic Saturdays
Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, August 7th 2021!

Please note that this event is 21 and over only.
As usual, we will start registration at 2: 00 pm.
Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth!
Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit.

All languages welcome.
All performance art forms welcome!

We are excited our audiences and honored our performing family is growing. So come by and witness the amazing talents brewing in our city.
Tell a friend!
.
.
.
#poetry #performanceart #openmic #artspace #poeticsaturday #saturday #words #open @gitemsitem @guac_on_addis @arada.et @linkupaddis @artsmailinglist @contemporary_nights @seifetemam @cttotheg @christooz @ye_getaneh_lij
ፍቅር ይሻለኛል እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የልቦለድ መጽሐፍ እሁድ ነሃሴ 2 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው፤ በኢክላስ ሕንፃ ዋልያ መጽሐፍ ቤት ይመረቃል። በዝግጅቱ ላይ ኤፍሬም ስዩም፣ ኢዘዲን ካሚል፣ ደምሰው መርሻ፣ አዳነ አረጋ፣ ዲበኩሉ ጌታ ፣ ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል ፣ ስላባት ማናዬ፣ አሸናፊ መለሰ እና ሌሎች ተጋባዦችም ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ እና ሁላችሁም እንድትታደሙ ተጋብዛችኋል።
ለግጥም ሲጥም የቴሌግራም ቤተሰቦች በልዩነት የተዘጋጀ የአጭር ግጥም ውድድር!!!

ወደ ዳሞቻ ተራራ የሚደረግ ጉዞን የሚያሸልም

ደንብ እና ሁኔታዎች
———————
1. ተወዳዳሪዎች የቴሌግራም ቻናላችን ተከታይ መሆን ይኖርባቸዋል።

2. ተወዳዳሪዎች ግጥማቸውን እራሳቸው በቀጥታ በቴሌግራም ወደ @seifetemam እስከ ሐሙስ ለሊት 6 ሰዓት ብቻ መላክ ይኖርባቸዋል።

3. ተወዳዳሪዎች ከ 18 ዓመት በላይ መሆን አለባቸው።

4. ግጥሙ በማንኛውም ርዕሰ ጉዳይ ላይ መሆን ሲችል ከ8 መስመር ያልበለጠ መሆን አለበት።

5. የተወዳዳሪዎቹ ግጥም በቻናሉ ከተለጠፈበት ሰዓት አንስቶ እስከ አርብ 6 ሰዓት (ከቀኑ) በብዙዎች የተወደደው ግጥም አሸናፊ ይሆናል።

መልካም ዕድል!

#ግጥምሲጥም #ዳሞቻ #ማትሪፕ #ጉዞ
A poetry contest for Gitem Sitem's telegram family!

With a chance to win a hiking trip to Damocha!

Terms and Conditions
———————
1. The contestant must be a member/follower of our channel.

2. The pieces should be submitted by contestants via telegram to @seifetemam until Thursday midnight.

3. Only those who are 18 years old and above are eligible.

4. There is no specific theme or topic for the contest but it should not be longer than 8 lines.

5. Poems with most likes until Mid day Friday will be the winner.

Good Luck!

#gitemsitem #damocha #ma_trip #hiking
😫ችግር😩
ችግር ይበርታ እና ይቸግር ጠንክሮ
ስልጣኔም አይዘግይ÷አያብዛ ቀጠሮ
ችግር ፈቺ ትውልድ ነገ እንዲኖረን
ችግርን ማግነን ነው ዛሬ የሚያስፈልገን🤔🤪
✍️ህሊና

@Hilina70
ኅልቆ - ሸለፈት
-------------------
የሚገለማ ~ ስጋ ታቅፌ
በምን ብልኃት ~ ልኑር አርፌ
ጥሎብኝ ቁልፈት ~ ክፉ ሸለፈት
ከላዬ ሰፍፎ ~ ልክ እንደ ገፈት
ዛሬ ብቆርጠው ~ ነገ ሊመዘዝ
ስንቴ ልቀንጠብ ~ ስንቴስ ልገረዝ?

#ዮናታን

@yonii_boss
የትም ቦታ ይጣለኝ
አደባባይ መሀል ቁና ሙሉ ቅማል ስቀምል ያውለኝ
መሪ ምርኩዝ ይንሳኝ
አውላላ ሜዳ ላይ ገደል ገባሁ እያልሁ ስደናበር ልገኝ
በጠራራ ጠሀይ ሚፋጅ አስፓልት ላይ እንደ እህል ልሰጣ
ዶፍ እየዘነበ መሸሸጊያ ልጣ
ታድያ እንዲህ ሲያደርገኝ አትሁኚ ጎኔ
አብረሺኝ ከሌለሽ ገሀነም ራሱ ገነቴ ነው ለኔ

@Fullof_memory
ጥላሸት በጥብጣ ድርብ መርፌ ይዛ፣
ህመሜን እንድችል በአረቄ አደንዝዛ፤
ድዴን ትወቅራለች ፥ ጉራማይሌ ጥርሴን፣
እንጃ ከዚህ ኋላ ፥ እህልም መቅመሴን።
ፈገግታ እየቆጠብኩ ፥ እኖራለሁ እንጂ ፣
እንዲህ ነው 'ሚያደርገኝ ጥለሽኝ ስትሄጂ ።
ጥርሴን ተነቅሼ ፥ ለሳቅ ለጨዋታ ፣
እንኳንስ ከንፈሬ ፥ ግንባሬ አይፈታ።

አስካለ ልቅና

@AskuAn
ቃና : ዘ : ገሊላ_..

በጎደለ : ቀኔ : የሞላውን : ውሀ
ሲያቅረኝ : ለመንኩት : እንዲሆን : አምሀ
እሱም : ቃሌን : ሰምቶ : ወይን : አደረገልኝ
ቀድቼ : ጠጥቼ : ጥማትን : : ሰከርኩኝ
_በል: እንግዲህ_
.....
አገባለሁ : ብዬ : የጠራሁት : ሚዜ : ተሞሽሯልና
ወይኑን : ውሀ : አርግልኝ : ስትመለስ : ቃና...
/***/
ናታን ኤርምያስ

@UniqueDY
እኔ እና አንቺ

አንቺ ማለት ጸሃይ፡ እኔ ጨረቃዋን
ባንቺ ብርሃን የምፈካ፡ ባንቺ መጥፋት የምባክን
አንቺ ሙሉ አለም፥ እኔ ትንሽ ድንኳን


ኢብራሂም አብዱ

@Ibrocr7
ጊዜ
በሰኮንዶች ድምር በደቂቃ መሄድ
በሰአታት ማለፍ በቀናቶች መንጎድ
በወራት መተካት በአመታቶች መክነፍ
በጊዜ ሽቅድድም በወቅታቶች ማለፍ
አካልም ይደክማል ደጋፊውን ይሻል
በወጣትነቱ የዘራውን ያጭዳል
ባሳለፈው ትላንት ጊዜ ፈራጅ ሁኖ ዛሬ ላይ ይቀጣል።

እምነት

@Enku41
የይሁዳ ከንፈር

ስለ አንተና እኔ
ትንቢት ባይፃፍም ነብይ ባይናገር
ልትሄድ መምጣትህን ልቤ ነግሮኝ ነበር

አንተ ይሁዳ ሆነህ
እኔ ሆኜ አምላክ

ባላንጣህ ባይገዛኝ በ"ዲናር" ባትሸጠኝ
በመጨረሻ እራት በመሳም ሸኘኸኝ...

በምህረት
ሐምሌ /2013ዓ .ም

@mihretengida
.................ፀ*ፀ*ቴ*
አዎን ፀፀቴ ነህ ንስሀ ያስገባኸኝ
ካምላኬ አጣልተህ ካምላኬ ያስታረከኝ
ጥፋቴን አልወቅሰው መርቶኛል ወደ
እውነት
ተመርጫለሁኝ ለትልቁ ደስታ በትንሹ
ክፋት

@Mekdiyemariyam
!?!
እርምጃችን ሁሉ ታንፆ በስጋት
መራቅ ለመጠጋት
ባዶ ተስፍ መጋት
ጀንበርን መናፈቅ እየሸሹ ንጋት
ምን ይሉት ነው ደግሞ?
ለመድረስ መጓጓት እርምጃን አቁሞ

✍️ቶፊቅ መሀመድ ( #አዲብ )

@Tufaw_muhe
ሠው ምንድን ነው

ታስበው ዘንድ ብሎ መዝሙር እንደፃፈው
ትመረምረው ዘንድ ብሎ እንደቀጠለው
እኔም ልጠይቅህ የሠማይ ፈጣሪ
የብርሃናት አባት የምድርም ቀማሪ፤
እድል ፈንታው ፈቅዶ ሞትን የሸለምከው
ይሄ ያንተ አምሣል፤ ጌታ ''ሠው'' ምንድን ነው?


26/11/13
ገጣሚ : ዳዊት:ጥዑማይ

@faberfortunae