አበባዮሽ ስል ለምለም በል ደሃ
ብንሸለም መብራት ብንሸለም ውሃ
ፍሰሐ ተ.
ብንሸለም መብራት ብንሸለም ውሃ
ፍሰሐ ተ.
ዘመነ... በድጋሚ
ከአመራሩ ተባልተን
ከየጎረቤቱ ተዋርፈን
ሳሙና መምጠጥን
ለምዶ ገላችን
በመጋገሪያ ዕጦት
ተደፍቶ ሊጣችን
የዘር ሀረጋችን
ሰፍሮ ከመታውቂያችን
በበላይነት ስሜት
ታመን በዘር ምጥ በሽታ
.
.
.
እንኖር ይሆን ፤ እንኖር ይሆን
በዘመነ ማርቆስ
ዘመነ...በድጋሚ
በረከትአብ ፍ.
ከአመራሩ ተባልተን
ከየጎረቤቱ ተዋርፈን
ሳሙና መምጠጥን
ለምዶ ገላችን
በመጋገሪያ ዕጦት
ተደፍቶ ሊጣችን
የዘር ሀረጋችን
ሰፍሮ ከመታውቂያችን
በበላይነት ስሜት
ታመን በዘር ምጥ በሽታ
.
.
.
እንኖር ይሆን ፤ እንኖር ይሆን
በዘመነ ማርቆስ
ዘመነ...በድጋሚ
በረከትአብ ፍ.
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! የሽልማቱን አይነት እና መጠን ከነገ ወድያ አሳውቃለሁ ። ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! የሽልማቱን አይነት እና መጠን ከነገ ወድያ አሳውቃለሁ ። ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ጥንብ አንሳ
በዘመነ ጥንባት ሰው ከሰው ተሻትቶ በረከሰበቱ
ብዙኃን አሉና ሰውነታቸው ውስጥ ሞተው የሸተቱ
ወይ ልብህን አንፃ ሙታኑን ቀስቅሳ
ወይ ሆድህን ሙላ ሁንና ጥንብአንሳ
@seifetemam #seifetemam
በዘመነ ጥንባት ሰው ከሰው ተሻትቶ በረከሰበቱ
ብዙኃን አሉና ሰውነታቸው ውስጥ ሞተው የሸተቱ
ወይ ልብህን አንፃ ሙታኑን ቀስቅሳ
ወይ ሆድህን ሙላ ሁንና ጥንብአንሳ
@seifetemam #seifetemam
👍1
እሺ እንዴትናችሁልኝ? አዲሱ አመት አያያዙ የተመቻችሁ ይመስላል ። የግጥም ውድድራችን ተጀምሯል እስከ እሁድ አስር ሰዓት ይቆያል ። ግጥማችሁን በ @Seifdman አድርሱኝ ። ከመሳተፍ ማንበብን የምትመርጡ ከሆነ ለ 👍 እንዲሁም ለ 👎 በመምረጥ አሸናፊ ግጥሞችን እንለይ ። በድምጽ የተቀዱም ካሉ እቀበላለሁ ። መልካም ውድድር ።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
40 ልብ
አይ እታባ ...
እንዴት ቀለድሽ ባክሽ
ሆድ ሆዴን ቢበላው ይመጣል ማለትሽ
አልታይህ ቢለኝ የያኔው ተረትሽ
አልጨበጥ ቢለኝ የፊተኛው ተስፋሽ
ይኸው እታባዬ ...... ቧልተኛ ነሽ አልኩሽ
ቁጥር እንደው አያፍር .....
ደንደሱን አስፍቶ ደሞ እያጠበበ፤ ይከንፋል... ይበራል
ሺዘጠኙን በቅጡ ሳንኖር፤ ፪ሺ ሠፍቶ ያተራምሰናል
እሱ ምን አለበት..... እንዳባይ ይነጉዳል...
እኔ አለሁ እዚ በሀሳብ የምርድ
አርባዬን ቀርጥፌ አፋሽ የሆንኩ አመድ
እና እታባዬ.....
የታል ታድያ ያ ልብ የነገርሽኝ ቀድሞ
በ40 ዘመኔ የማገኘው ቆሞ... (አልያም ተጋድሞ)
ከብትንትን ኑሮ የሚገላግለኝ
ከ40 ልብ ህይወት የሚያሰናብተኝ
የታለ እታባ?? ... የታለ??...
አይ እታባ ...
እንዴት ቀለድሽ ባክሽ
ሆድ ሆዴን ቢበላው ይመጣል ማለትሽ
አልታይህ ቢለኝ የያኔው ተረትሽ
አልጨበጥ ቢለኝ የፊተኛው ተስፋሽ
ይኸው እታባዬ ...... ቧልተኛ ነሽ አልኩሽ
ቁጥር እንደው አያፍር .....
ደንደሱን አስፍቶ ደሞ እያጠበበ፤ ይከንፋል... ይበራል
ሺዘጠኙን በቅጡ ሳንኖር፤ ፪ሺ ሠፍቶ ያተራምሰናል
እሱ ምን አለበት..... እንዳባይ ይነጉዳል...
እኔ አለሁ እዚ በሀሳብ የምርድ
አርባዬን ቀርጥፌ አፋሽ የሆንኩ አመድ
እና እታባዬ.....
የታል ታድያ ያ ልብ የነገርሽኝ ቀድሞ
በ40 ዘመኔ የማገኘው ቆሞ... (አልያም ተጋድሞ)
ከብትንትን ኑሮ የሚገላግለኝ
ከ40 ልብ ህይወት የሚያሰናብተኝ
የታለ እታባ?? ... የታለ??...
ውዴ
ዝምታሽ ቢጨንቀኝ ቴክስትሽ ቢርቀኝ
ስልኬ ያለልማዱ ብሬን ቢምርልኝ
አፌን አሞጥሙጬ ልነግርሽ ቆረጥኩኝ
እቱ የኔ አበባ....
ዝምታሽ ከባድ ነው ሆድን ያሸብራል
ቀልብንም አርቆ አንጀት ያላውሣል.....
ብዬ እንዳልልሽ.... ብዬ እንዳልልሽ
ቃላት አይገዙ በቂ ስንኝ የለኝ
እኔም ካንቺ የባስኩ ስንኞች የከዱኝ
ብቻ....
ጀማሪ መሆኔ እንዳይነቃብኝ
ኝ ኝ ኝ ..... እያልኩኝ
መግጠሙ ደብሮኝ
የሆዴን ሣልሸና ልተኛ ወሠንኩኝ።
(እባክሽ አደራ እንዳትስቂብኝ.ኝ ኝ ኝ..)
ኖታ
ዝምታሽ ቢጨንቀኝ ቴክስትሽ ቢርቀኝ
ስልኬ ያለልማዱ ብሬን ቢምርልኝ
አፌን አሞጥሙጬ ልነግርሽ ቆረጥኩኝ
እቱ የኔ አበባ....
ዝምታሽ ከባድ ነው ሆድን ያሸብራል
ቀልብንም አርቆ አንጀት ያላውሣል.....
ብዬ እንዳልልሽ.... ብዬ እንዳልልሽ
ቃላት አይገዙ በቂ ስንኝ የለኝ
እኔም ካንቺ የባስኩ ስንኞች የከዱኝ
ብቻ....
ጀማሪ መሆኔ እንዳይነቃብኝ
ኝ ኝ ኝ ..... እያልኩኝ
መግጠሙ ደብሮኝ
የሆዴን ሣልሸና ልተኛ ወሠንኩኝ።
(እባክሽ አደራ እንዳትስቂብኝ.ኝ ኝ ኝ..)
ኖታ
እዬዬ
ከውዶቹ መሃል አንድ ሰው አነሰኝ
ሀዘን ሆዴ ገብቶ እያንሰፈሰፈኝ
ጠቆረብኝ ውስጤ ልቤም ጨላለመ
ያሸከምኩት ተስፋ በአፈር አከተመ
እዬዬ ለራሴ እዬዬ ለሃገሬ
ታናሼ ሲቀድመኝ እኔ ተገትሬ
እዬዬ ለቋሚ ውዱን ለሸኘ ሰው
ከተመረጠማ የአብስራ ድንቅ ነው
ሰይፈ
ከውዶቹ መሃል አንድ ሰው አነሰኝ
ሀዘን ሆዴ ገብቶ እያንሰፈሰፈኝ
ጠቆረብኝ ውስጤ ልቤም ጨላለመ
ያሸከምኩት ተስፋ በአፈር አከተመ
እዬዬ ለራሴ እዬዬ ለሃገሬ
ታናሼ ሲቀድመኝ እኔ ተገትሬ
እዬዬ ለቋሚ ውዱን ለሸኘ ሰው
ከተመረጠማ የአብስራ ድንቅ ነው
ሰይፈ
ግዝት
አድምጡኝ እንጂ አትስሙኝ
በክፋት ጥላቻ በህይወት ገላችሁ
ከነመፈጠሬም በቁሜ ረስታችሁ
የአፈሬን ሳጥን በቅርቡ አይታችሁ
እንዳታለቅሱልኝ ...
ኻላ እንዳላዝንባችሁ
አትክልት አይደለሁ እንባችሁ አይረባኝ
ከሞት አለምልሞ ህይወት አይዘራብኝ
እንዲያው ከንቱ ድካም እንዳይሆንባችሁ
መኖሬን ከድታችሁ ሞቴን ካመናችሁ
ያኔ... በበድኔ ዙሪያ እንዳላይ ከባችሁ
በቁሜ እያለሁ ይኸው ገዘትኳችሁ።
እንዳታለቅሱልኝ...!!!
ኖታ
አድምጡኝ እንጂ አትስሙኝ
በክፋት ጥላቻ በህይወት ገላችሁ
ከነመፈጠሬም በቁሜ ረስታችሁ
የአፈሬን ሳጥን በቅርቡ አይታችሁ
እንዳታለቅሱልኝ ...
ኻላ እንዳላዝንባችሁ
አትክልት አይደለሁ እንባችሁ አይረባኝ
ከሞት አለምልሞ ህይወት አይዘራብኝ
እንዲያው ከንቱ ድካም እንዳይሆንባችሁ
መኖሬን ከድታችሁ ሞቴን ካመናችሁ
ያኔ... በበድኔ ዙሪያ እንዳላይ ከባችሁ
በቁሜ እያለሁ ይኸው ገዘትኳችሁ።
እንዳታለቅሱልኝ...!!!
ኖታ