የመቆም ዑደት
የቅድም አያቴን አጽም ከአፈር አውጥተው
ቀጥ ብሎ መሄድን በሷ እንደጀመርነው
ይነግሩኛል ደፍረው
...እንደዚህ እያሉ
ከጥንቱ ጥንት ፊት ሰው ዝንጀሮ ሳለ
ዝንጀሮ ሰው ሁኖ መቆም ሰለጠነ
ለሱም ምልክቷ
ሙዝየም አኑረው ይቹትና አጥንቷ
ይህንን አምኜ ለእንግዳ ስናገር
ለመጣ ለሄደው ለኦባማ ሳይቀር
ቀድመን እንደሞቅነው የመቆምን ጀምበር
...ደሞ ከመንገዱ
ወይዘሪት ድንቄ እና እትዬ አረገዱ
ሸክም አጉብጧቸው 'በ' ን ሰርተው ሲሄዱ
እኔ ደሞ እላለሁ
ቀድመን እንደቆምን ቀድመን የወደቅነው
እኛው እንደጀመርን እኛው ልንጨርሰው
#seifetemam #አሁን
የቅድም አያቴን አጽም ከአፈር አውጥተው
ቀጥ ብሎ መሄድን በሷ እንደጀመርነው
ይነግሩኛል ደፍረው
...እንደዚህ እያሉ
ከጥንቱ ጥንት ፊት ሰው ዝንጀሮ ሳለ
ዝንጀሮ ሰው ሁኖ መቆም ሰለጠነ
ለሱም ምልክቷ
ሙዝየም አኑረው ይቹትና አጥንቷ
ይህንን አምኜ ለእንግዳ ስናገር
ለመጣ ለሄደው ለኦባማ ሳይቀር
ቀድመን እንደሞቅነው የመቆምን ጀምበር
...ደሞ ከመንገዱ
ወይዘሪት ድንቄ እና እትዬ አረገዱ
ሸክም አጉብጧቸው 'በ' ን ሰርተው ሲሄዱ
እኔ ደሞ እላለሁ
ቀድመን እንደቆምን ቀድመን የወደቅነው
እኛው እንደጀመርን እኛው ልንጨርሰው
#seifetemam #አሁን
ወዳጄን ምን ነካው
ከመንጋው መንጋጋ ፈልቅቆ እየወጣ
ተነጥሎም ሲቆም አጀቡን እያጣ
ለሞቀው ገበያ ምሽቱ ሲነጋ
እራሱን አሹሎ የሚሆን መንጋጋ
ለሌላኛው መንጋ
መሾሉስ ባልከፋ
መሳሉስ ባልከፋ
ወጀብ የፈጠረው ባጀብ እንዳይጠፋ
ወዳጄን ጥሩልኝ እናውራ በወጉ
ከመንጋው ቢጠፋ አይሸጥም በጉ
ሰይፈ ተማም 2008
ከመንጋው መንጋጋ ፈልቅቆ እየወጣ
ተነጥሎም ሲቆም አጀቡን እያጣ
ለሞቀው ገበያ ምሽቱ ሲነጋ
እራሱን አሹሎ የሚሆን መንጋጋ
ለሌላኛው መንጋ
መሾሉስ ባልከፋ
መሳሉስ ባልከፋ
ወጀብ የፈጠረው ባጀብ እንዳይጠፋ
ወዳጄን ጥሩልኝ እናውራ በወጉ
ከመንጋው ቢጠፋ አይሸጥም በጉ
ሰይፈ ተማም 2008
ቡሄ በሉ
ከ ሰይፈ ተማም
=======
ቡሄ የልጆች በዓል ነው። ልጅ እያለን ትዝ ይለኛል ከነ ሰይድ ጋራ ሆያሆዬ ስንጨፍር - እነ ጋሽ ጃፈር ቤት ሁሉ ብር ይሰጠናል እንጂ ተባረን አናውቅም።ሃገሪቷ ውስጥ የፈጠራ ችሎታ ማነሱን ከሚያመላክቱ ነገሮች አንዱ (ከዚህ ፅሁፍ ውጪ ማለት ነው)አዲስአባ ውስጥ እንዳሉ ታሪካዊ ህንፃዎች ያልታደሱት የሆያሆዬ ግጥሞች ናቸው።በቀን የሶስት ወይም የአራት ታክሲ ገቢ የሚያስገባ ልማታዊ ልጥጥ ሱቅ በር ላይ" እዛ ማዶ አንድ ካልሲእዚህ ማዶ አንድ ካልሲየዚህ ቤት ጌታ ባለታክሲ"ይህን ሲባል በየቀኑ እየተጋጨ እና በሹፌሩ ሰበብ እየታሰረ አማሮት የሸጠው ታክሲ አይኑ ላይ ድቅን ሲል የሆያሆዬ ባንዱን በንዴት ያፈራርሰዋል ልማታዊ ልጥጡ ይህን ሲያደርግ ያየ ለሃገርናባህል ተቆርቅሪ ነኝ ባይ አልፎ ሂያጅ በእርሱ የልጅነት ዘመን የተገጠሙ ቡሄ በሉ ግጥሞችን በውስጡ 'ሆ' እያለ በመስማት ላይ ሳለ ልማታዊ ልጥጡን ለባህል መጥፋት አንዱ ተጠያቂ አርጎ ኮንኖ ማስቲካውን ይለጥጣል።የግድ በየማዶው አንድ ነገር እንዲያሰፍር የተፈረደበት ቡሄበሉ ግጥም እንደምንም ብሎ ሌላ ማዶ ይቀጥላል...በሬ ላይ የቆሙትን ሶስት ሆያሆዬያን አዲስ ግጥም ያላቸው እንደሆን ጠየኳቸው ደሞዛቸው እንደ ግጥማቸው አሪፍነት እንደሚያድግም ነገርኳቸው"እዛ ማዶ አንድ ኮምፒተር" አሉ በወኔ እኔም ዘመኑን የመሰለ እንደ ቀበሌ ነው ወረዳ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ሊሰሩ ነው ብዬ ስጠብቅ"እዚ ማዶ አንድ ኮምፒተርየዚህ ቤት ጌታ ሊሄድ ነው አሜሪካን" ያቺን የሳንቲም አንድ ብር ከማግኘታቸው በፊት በሆዴ ያልኩትን ፊቴ ላይ ሳያዩ አይቀርም እኔም 'እድሜ ልኬን የሞከርኩት ዲቪ ለማስተዛዘኛ ኤምባሲው ጋር እንኳን አድርሶኝ አያውቅም' ነበር ያልኩት። ልጆቹ ከሄዱ በኋላ ሳስበው ግን በዚች ከልጥጦች ልጥጥነት፣ ከጠባቦች ጠባብነት፣ ከሙሰኞች ሙሰኝነት እና ከመሳሰሉት ውጭ ነገሮች ወይ በበጎ በማይለዋወጡበት ወይ ማንነትን የሚገልፁቱ ከዘመኑ ጋር በማይቀጥሉበት ሃገር እየኖሩ ምን ፍጠሩ ሊባሉ ኖሯል? እስኪ አስቡት ሁለት ወጣት ባልና ሚስት ያዩ ልጆች"እዛ ማዶ አንድ አሞራአዚ ማዶ ሌላ አሞራየኔማ እንትና ዛራና ቻንድራ" ቢሉ... የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው የቡሄ ግጥሞች ተጠቃሚው ጋር እንዳይደርሱ ተመልክቶ የማያውቀው የሚመለከተው አካል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - አንዳንድ የአዱስ አበባ ነዋሪዎች ሳይሆኑ እኔ ነኝ ያልኩት። ለዚህም ጎረቤቴ ብርሃኑ ላይ የተገጠመውን ማየት በቂ ነው።"እዛ ማዶ አንድ ብር እዚ ማዶ አንድ ብርየዚ ቤት ጌታ ባለባቡር"ከውስጥ የነበረው ብሬ ይህ ጊዜው ያለፈበት ግጥም አቅለሽልሾት "የዚህ ቤት ጌታ ኢሃዲግ ነው አሏቹ?" ብሎ ልጆቹ ላይ አስታውኮ ይህንን ሲል የሰማው አዋቂ ያለ እንደሆን ዙሪያውን በፍጥነት ገለማምጦ በሩን ጠርቅሞት ገባ። እኔም አዳዲስ እና ነባር እንዲሁም ሪሚክስ የተደረጉ ስራዎችን የሚያ ቀርቡ አባላት ያሉት የሆያሆዬ ባንድ በምናቤ አቋቋምኩለት...እዛ ማዶ የላም ወተት(እንዴ የወተት ላም ነች የላም ወተት? ወይስ የለም ወተት? ቆይ እስኪ እዚ ማዶ ይድገሙትእዚ ማዶ የላም ወተትየኔማ ብሬ አይዘውም አተትኢሽሽ አሁን ይሄ ሟርት ነው ሙገሳ?... እዛ ማዶ አንድ ዶሮእዚ ማዶ አንድ ዶሮየኔማ ብሬ ቴዲ አፍሮ(ኧረ ሳያፍር ነው አሪፍ...ደሞ ሊያሳስሩን ነው እንዴ..)እዛ ማዶ አንድ ጠመኔ'ዝምበል!' አለ ብሬ በንዴት'ኧረ አሪፍ አዲስ ግጥም ነው' የባንዱ መሪ ነበር።ብሬም እጁን እያወናጨፈ 'በቃ በቃ ኔ በምትባል ፊደል የሚገጥም ምንም ደህና ነገር የለም' አለ። ... ብሬ ደሞ ያበዛዋል ገና ለገና ወ*ኔ ሊሉ ነው ብሎ...
ቡሄ
2008
ከ ሰይፈ ተማም
=======
ቡሄ የልጆች በዓል ነው። ልጅ እያለን ትዝ ይለኛል ከነ ሰይድ ጋራ ሆያሆዬ ስንጨፍር - እነ ጋሽ ጃፈር ቤት ሁሉ ብር ይሰጠናል እንጂ ተባረን አናውቅም።ሃገሪቷ ውስጥ የፈጠራ ችሎታ ማነሱን ከሚያመላክቱ ነገሮች አንዱ (ከዚህ ፅሁፍ ውጪ ማለት ነው)አዲስአባ ውስጥ እንዳሉ ታሪካዊ ህንፃዎች ያልታደሱት የሆያሆዬ ግጥሞች ናቸው።በቀን የሶስት ወይም የአራት ታክሲ ገቢ የሚያስገባ ልማታዊ ልጥጥ ሱቅ በር ላይ" እዛ ማዶ አንድ ካልሲእዚህ ማዶ አንድ ካልሲየዚህ ቤት ጌታ ባለታክሲ"ይህን ሲባል በየቀኑ እየተጋጨ እና በሹፌሩ ሰበብ እየታሰረ አማሮት የሸጠው ታክሲ አይኑ ላይ ድቅን ሲል የሆያሆዬ ባንዱን በንዴት ያፈራርሰዋል ልማታዊ ልጥጡ ይህን ሲያደርግ ያየ ለሃገርናባህል ተቆርቅሪ ነኝ ባይ አልፎ ሂያጅ በእርሱ የልጅነት ዘመን የተገጠሙ ቡሄ በሉ ግጥሞችን በውስጡ 'ሆ' እያለ በመስማት ላይ ሳለ ልማታዊ ልጥጡን ለባህል መጥፋት አንዱ ተጠያቂ አርጎ ኮንኖ ማስቲካውን ይለጥጣል።የግድ በየማዶው አንድ ነገር እንዲያሰፍር የተፈረደበት ቡሄበሉ ግጥም እንደምንም ብሎ ሌላ ማዶ ይቀጥላል...በሬ ላይ የቆሙትን ሶስት ሆያሆዬያን አዲስ ግጥም ያላቸው እንደሆን ጠየኳቸው ደሞዛቸው እንደ ግጥማቸው አሪፍነት እንደሚያድግም ነገርኳቸው"እዛ ማዶ አንድ ኮምፒተር" አሉ በወኔ እኔም ዘመኑን የመሰለ እንደ ቀበሌ ነው ወረዳ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ሊሰሩ ነው ብዬ ስጠብቅ"እዚ ማዶ አንድ ኮምፒተርየዚህ ቤት ጌታ ሊሄድ ነው አሜሪካን" ያቺን የሳንቲም አንድ ብር ከማግኘታቸው በፊት በሆዴ ያልኩትን ፊቴ ላይ ሳያዩ አይቀርም እኔም 'እድሜ ልኬን የሞከርኩት ዲቪ ለማስተዛዘኛ ኤምባሲው ጋር እንኳን አድርሶኝ አያውቅም' ነበር ያልኩት። ልጆቹ ከሄዱ በኋላ ሳስበው ግን በዚች ከልጥጦች ልጥጥነት፣ ከጠባቦች ጠባብነት፣ ከሙሰኞች ሙሰኝነት እና ከመሳሰሉት ውጭ ነገሮች ወይ በበጎ በማይለዋወጡበት ወይ ማንነትን የሚገልፁቱ ከዘመኑ ጋር በማይቀጥሉበት ሃገር እየኖሩ ምን ፍጠሩ ሊባሉ ኖሯል? እስኪ አስቡት ሁለት ወጣት ባልና ሚስት ያዩ ልጆች"እዛ ማዶ አንድ አሞራአዚ ማዶ ሌላ አሞራየኔማ እንትና ዛራና ቻንድራ" ቢሉ... የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው የቡሄ ግጥሞች ተጠቃሚው ጋር እንዳይደርሱ ተመልክቶ የማያውቀው የሚመለከተው አካል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - አንዳንድ የአዱስ አበባ ነዋሪዎች ሳይሆኑ እኔ ነኝ ያልኩት። ለዚህም ጎረቤቴ ብርሃኑ ላይ የተገጠመውን ማየት በቂ ነው።"እዛ ማዶ አንድ ብር እዚ ማዶ አንድ ብርየዚ ቤት ጌታ ባለባቡር"ከውስጥ የነበረው ብሬ ይህ ጊዜው ያለፈበት ግጥም አቅለሽልሾት "የዚህ ቤት ጌታ ኢሃዲግ ነው አሏቹ?" ብሎ ልጆቹ ላይ አስታውኮ ይህንን ሲል የሰማው አዋቂ ያለ እንደሆን ዙሪያውን በፍጥነት ገለማምጦ በሩን ጠርቅሞት ገባ። እኔም አዳዲስ እና ነባር እንዲሁም ሪሚክስ የተደረጉ ስራዎችን የሚያ ቀርቡ አባላት ያሉት የሆያሆዬ ባንድ በምናቤ አቋቋምኩለት...እዛ ማዶ የላም ወተት(እንዴ የወተት ላም ነች የላም ወተት? ወይስ የለም ወተት? ቆይ እስኪ እዚ ማዶ ይድገሙትእዚ ማዶ የላም ወተትየኔማ ብሬ አይዘውም አተትኢሽሽ አሁን ይሄ ሟርት ነው ሙገሳ?... እዛ ማዶ አንድ ዶሮእዚ ማዶ አንድ ዶሮየኔማ ብሬ ቴዲ አፍሮ(ኧረ ሳያፍር ነው አሪፍ...ደሞ ሊያሳስሩን ነው እንዴ..)እዛ ማዶ አንድ ጠመኔ'ዝምበል!' አለ ብሬ በንዴት'ኧረ አሪፍ አዲስ ግጥም ነው' የባንዱ መሪ ነበር።ብሬም እጁን እያወናጨፈ 'በቃ በቃ ኔ በምትባል ፊደል የሚገጥም ምንም ደህና ነገር የለም' አለ። ... ብሬ ደሞ ያበዛዋል ገና ለገና ወ*ኔ ሊሉ ነው ብሎ...
ቡሄ
2008
የረሳሁት እኔ...
የዘነበው ዝናብ ካለሽበት ሃገር
ከጉንጬ ተንኖ ነው ናፍቆቴን ሊናገር
የነፈሰው ንፋስ ፊትሽን ‘ሚዳስስ
‘ኡፍ’ ያልኩት ትንፋሽ ነው ጭንቀቴ ሲባባስ
ያለሽበት ቦታ ምሽቱ ‘ማይመሸው
በሰቀቀን ሃሳብ
ያንቺን መምጣት ሳስብ
የኔቀን አጥሮ ነው
...
የሄድንበት መንገድ አንገትሽን ከእጄ
እጅሽ ከወገቤ
ልብሽን በልቤ
ፍቅርሽን አጥምጄ
ያረፍንበት ጥላ ካንደበት እርቀን አይኖችሽን ሳነብ
በመኖርሽ ስቄ በመኖሬ ስቀሽ ሃሴት ስንመገብ
በጠራራ ፀሃይ እንደምሽት መስለን
ደሞ በምሽቱ እንደፀሃይ ደምቀን
ተጓዥ መንገደኛው ካይን ያውጣቹ እያለ ከአይኑ ሲከተን
‘ባይኑ ሲከተለን
ጎርፍ ጭቃ ቁሩን መኖርሽ አስኪዶ
መኖሬም ወበቁን ንዳዱን አብርዶ
እኛ ዘንድ ተውበው ካፊያ ዶፍ በረዶ
ይህን እና ሌላ ካንቺ ጋር የሄዱ እየመላለሱ
የረሳሁት እኔን የማልረሳሽ አንቺን እየቀሰቀሱ
ማንኔተን ነቅሰው ፍቅር ነህ እያሉ እኔን አስታወሱ
#seifetemam #የረሳሁትእኔ
የዘነበው ዝናብ ካለሽበት ሃገር
ከጉንጬ ተንኖ ነው ናፍቆቴን ሊናገር
የነፈሰው ንፋስ ፊትሽን ‘ሚዳስስ
‘ኡፍ’ ያልኩት ትንፋሽ ነው ጭንቀቴ ሲባባስ
ያለሽበት ቦታ ምሽቱ ‘ማይመሸው
በሰቀቀን ሃሳብ
ያንቺን መምጣት ሳስብ
የኔቀን አጥሮ ነው
...
የሄድንበት መንገድ አንገትሽን ከእጄ
እጅሽ ከወገቤ
ልብሽን በልቤ
ፍቅርሽን አጥምጄ
ያረፍንበት ጥላ ካንደበት እርቀን አይኖችሽን ሳነብ
በመኖርሽ ስቄ በመኖሬ ስቀሽ ሃሴት ስንመገብ
በጠራራ ፀሃይ እንደምሽት መስለን
ደሞ በምሽቱ እንደፀሃይ ደምቀን
ተጓዥ መንገደኛው ካይን ያውጣቹ እያለ ከአይኑ ሲከተን
‘ባይኑ ሲከተለን
ጎርፍ ጭቃ ቁሩን መኖርሽ አስኪዶ
መኖሬም ወበቁን ንዳዱን አብርዶ
እኛ ዘንድ ተውበው ካፊያ ዶፍ በረዶ
ይህን እና ሌላ ካንቺ ጋር የሄዱ እየመላለሱ
የረሳሁት እኔን የማልረሳሽ አንቺን እየቀሰቀሱ
ማንኔተን ነቅሰው ፍቅር ነህ እያሉ እኔን አስታወሱ
#seifetemam #የረሳሁትእኔ
👍1
ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
ከዋጋም በላይ ነች
Priceless እንዲል ነጭ
ከምትወደው ሁሉ ነፍስህን አስበልጥ
ከፍ እንድታደርጋት ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
#seifetemam 2006 #ለህይወትህ_ዋጋ_አትስጥ
ከዋጋም በላይ ነች
Priceless እንዲል ነጭ
ከምትወደው ሁሉ ነፍስህን አስበልጥ
ከፍ እንድታደርጋት ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
#seifetemam 2006 #ለህይወትህ_ዋጋ_አትስጥ
አቋራጭ
የኔን መጥፎ 'ሚሻ መሆኑን እያየሁ
እንዴት እንደራሴ ጠላቴን ልውደደው
… ይልቅስ…
ከቃሉ እንዳልወጣ እንዳይቀየመኝ
እራሴን ጠልቼ ጠላቴን ባልወደው
አቋራጭ መሰለኝ
ሰይፈ ተማም 2004
#seifetemam #አቋራጭ
የኔን መጥፎ 'ሚሻ መሆኑን እያየሁ
እንዴት እንደራሴ ጠላቴን ልውደደው
… ይልቅስ…
ከቃሉ እንዳልወጣ እንዳይቀየመኝ
እራሴን ጠልቼ ጠላቴን ባልወደው
አቋራጭ መሰለኝ
ሰይፈ ተማም 2004
#seifetemam #አቋራጭ
ምርጫ
====
ቤት ሥራ ፤ ተፈንከት
ምርጫው የራስህ ነው ድንጋይ ሲወረወር
አናትህን ስትባል ግንባር እየሰጠህ ሕይወትህን ማማረር?
ወይ እየጠራረብህ በልክ እየሰተርህ ግንብህን ማበጀት አጥርህን መደርደር
#የጌታነህ_ልጅ
ነሐሴ 2009
====
ቤት ሥራ ፤ ተፈንከት
ምርጫው የራስህ ነው ድንጋይ ሲወረወር
አናትህን ስትባል ግንባር እየሰጠህ ሕይወትህን ማማረር?
ወይ እየጠራረብህ በልክ እየሰተርህ ግንብህን ማበጀት አጥርህን መደርደር
#የጌታነህ_ልጅ
ነሐሴ 2009
ሃሞተ ቢስ ጀግና
ዛሬ አዲስ አባ ውስጥ
ብዙ ሰው መሮታል
አፉ ሬት ሆኖታል
የሚጠጣው ድራፍት
መሪር እንደጅኑ
እንደጠላው ሁሉ
የሚበላውም ጫት
መሪር እንደኑሮ
የሚጣፍጥ መርሮ
ይህን ጀግና ትውልድ
እንደው በለበጣ
ሃሞተ ቢስ አሉት
ሃሞት እየበላ
ሃሞት እየጠጣ
#seifetemam
ዛሬ አዲስ አባ ውስጥ
ብዙ ሰው መሮታል
አፉ ሬት ሆኖታል
የሚጠጣው ድራፍት
መሪር እንደጅኑ
እንደጠላው ሁሉ
የሚበላውም ጫት
መሪር እንደኑሮ
የሚጣፍጥ መርሮ
ይህን ጀግና ትውልድ
እንደው በለበጣ
ሃሞተ ቢስ አሉት
ሃሞት እየበላ
ሃሞት እየጠጣ
#seifetemam
ፍቅርና ደሞዝ
ስራ ተቀጥሬ ከዋክብት ቆጠራ
እጅግ አደከመኝ እንዴት ብዬ ልስራ
ቆጥሬ ቆጥሬ እየተምታታብኝ
አልሰራህም ብለው ደሞዝ ከለከሉኝ
ስራዬ ፍቅር ነው ከዋክብት ውበቷ
ደሞዜም እሷው ነች በጄየገባች ለታ
(ለ...)
ሰይፈ ተማም 1996
ስራ ተቀጥሬ ከዋክብት ቆጠራ
እጅግ አደከመኝ እንዴት ብዬ ልስራ
ቆጥሬ ቆጥሬ እየተምታታብኝ
አልሰራህም ብለው ደሞዝ ከለከሉኝ
ስራዬ ፍቅር ነው ከዋክብት ውበቷ
ደሞዜም እሷው ነች በጄየገባች ለታ
(ለ...)
ሰይፈ ተማም 1996
ድምጽ፣ ሽታ፣ ጣዕም
ምስኪኑ ሰአሊ በወጠረው ሸራ
የሳላት ጉራንጉር የሳላት መንደሯ
ድምጽ የላትም ጭራሽ
ምኗም አይሰማም
ድምጽ ቀለም ሆኖ ከሸራው ላይ የለም
እነማማ እንትና ሰውን ሲቦጭቁ
እነ ጋሽ እከሌ አዳልጧቸው ሲወድቁ
ወይዘሮ እከሊት ጠበል ሲጠድቁ
የተሰማው ሁሉ የለም ከቀለሙ
የተጠጣው አቦል ከየት አለ ጣ'ሙ
ከየት አለ ሽታው የቡናው የጣኑ
ድምጽ ሽታ ጣዕም
በቀለም አይወጡም
በብሩሽ አይሰፍሩም
ወይስ
አይን የለም እነዚን ለማስፈር ከሸራ
አይን የለም እኒህን ለማየት ከሸራ
ምስኪኑ ሰዓሊ የሳላት መንደሯ
ስንቱን እንዳወጣች ስንቱን ነገር ቀብራ
ወይም
ድምጽ ሽታ ጣዕም ከዚህ ሰፈር የሉም
አይሰሙ አይሸቱ ጨርሶም አይጥሙም
እንደድሮ አይደሉም
ወይም...
ወይም ይጮሃሉ
ወይም የገማሉ
ወይም ይመርራሉ
ድምጽ ሽታ ጣዕም ኑሮነን እያሉ
ባለመሳል መስመር ሁሌ እየተሳሉ
#seifetemam #ድምጽሽታጣዕም
ምስኪኑ ሰአሊ በወጠረው ሸራ
የሳላት ጉራንጉር የሳላት መንደሯ
ድምጽ የላትም ጭራሽ
ምኗም አይሰማም
ድምጽ ቀለም ሆኖ ከሸራው ላይ የለም
እነማማ እንትና ሰውን ሲቦጭቁ
እነ ጋሽ እከሌ አዳልጧቸው ሲወድቁ
ወይዘሮ እከሊት ጠበል ሲጠድቁ
የተሰማው ሁሉ የለም ከቀለሙ
የተጠጣው አቦል ከየት አለ ጣ'ሙ
ከየት አለ ሽታው የቡናው የጣኑ
ድምጽ ሽታ ጣዕም
በቀለም አይወጡም
በብሩሽ አይሰፍሩም
ወይስ
አይን የለም እነዚን ለማስፈር ከሸራ
አይን የለም እኒህን ለማየት ከሸራ
ምስኪኑ ሰዓሊ የሳላት መንደሯ
ስንቱን እንዳወጣች ስንቱን ነገር ቀብራ
ወይም
ድምጽ ሽታ ጣዕም ከዚህ ሰፈር የሉም
አይሰሙ አይሸቱ ጨርሶም አይጥሙም
እንደድሮ አይደሉም
ወይም...
ወይም ይጮሃሉ
ወይም የገማሉ
ወይም ይመርራሉ
ድምጽ ሽታ ጣዕም ኑሮነን እያሉ
ባለመሳል መስመር ሁሌ እየተሳሉ
#seifetemam #ድምጽሽታጣዕም
ለአከራዬ ልጅ
መብራት የጠፋ ለት ሻማ ስታበሪ
ጥላሽን አየሁት ልብስ ስትቀይሪ
ልብስ የምታጥቢም ለት ጨምረሽ ከሳፋ
(መብራትስ ሁሌ ይሂድ ውሃ ግን አትጥፋ)
ጦረኞቹን አየሁ ሲሉ ቀና ደፋ
ቀና ደፋ እያልኩኝ ስሰራ የምታይ
እንዳያልፍብኝ ነው የናትሽ ቤት ኪራይ
ቤት ኪራይ ፍለጋ ጊቢያችሁ ስመጣ
አንቺን ብዬ ከፈልኩ ቤቱስ አያዋጣ
አያዋጣም ከቶ 'ማይከለል መስኮት የማይዘጋ በር
እናትሽ ሲወጡ ካልመጣሽ በስተቀር
#seifetemam #አሁን
@seifetemam @seifetemam
መብራት የጠፋ ለት ሻማ ስታበሪ
ጥላሽን አየሁት ልብስ ስትቀይሪ
ልብስ የምታጥቢም ለት ጨምረሽ ከሳፋ
(መብራትስ ሁሌ ይሂድ ውሃ ግን አትጥፋ)
ጦረኞቹን አየሁ ሲሉ ቀና ደፋ
ቀና ደፋ እያልኩኝ ስሰራ የምታይ
እንዳያልፍብኝ ነው የናትሽ ቤት ኪራይ
ቤት ኪራይ ፍለጋ ጊቢያችሁ ስመጣ
አንቺን ብዬ ከፈልኩ ቤቱስ አያዋጣ
አያዋጣም ከቶ 'ማይከለል መስኮት የማይዘጋ በር
እናትሽ ሲወጡ ካልመጣሽ በስተቀር
#seifetemam #አሁን
@seifetemam @seifetemam
🤩1
Forwarded from ቶኔቶር
Seife Temam:
አቻ
ቃላት ሳታረቁ
ነገር ሳታደቁ
ያላቻ ጋብቻ
ይቅር ብሎ ብቻ
አቻ ደሃ አጥተን
ይኸው ቆመን ቀረን
ሰይፈ ተማም
2007
#seifetemam
@TONETOR
@TONETOR
@TONETOR
አቻ
ቃላት ሳታረቁ
ነገር ሳታደቁ
ያላቻ ጋብቻ
ይቅር ብሎ ብቻ
አቻ ደሃ አጥተን
ይኸው ቆመን ቀረን
ሰይፈ ተማም
2007
#seifetemam
@TONETOR
@TONETOR
@TONETOR
አበቦቹ
ተናንሽ አበቦች የፍካት ጨረሮች
የብራ አለም ሰዎች
የንጹህ አገር ዜጎች
ለሃሴት አፎቱ
ለፍቅርም ቤቱ
ውበት ምልክቱ
. . . ትናንሽ አበቦች. . .
እንደጽገሬዳ የልብ ነጋሪ
እንደ አደይ አበባ ብሩህ ቀን አብሳሪ
ውስጠትን ሰርሳሪ
በውበት አሳሪ. . .
እነዚን አበቦች ለጌጥነት ያጨ
እነዚን አበቦች ለጌትነት ያጨ
ምንጩን አደረቀ ነገውንም ቀጨ
(ለልጆቻችን. . .)
#seifetemam
@seifetemam
ተናንሽ አበቦች የፍካት ጨረሮች
የብራ አለም ሰዎች
የንጹህ አገር ዜጎች
ለሃሴት አፎቱ
ለፍቅርም ቤቱ
ውበት ምልክቱ
. . . ትናንሽ አበቦች. . .
እንደጽገሬዳ የልብ ነጋሪ
እንደ አደይ አበባ ብሩህ ቀን አብሳሪ
ውስጠትን ሰርሳሪ
በውበት አሳሪ. . .
እነዚን አበቦች ለጌጥነት ያጨ
እነዚን አበቦች ለጌትነት ያጨ
ምንጩን አደረቀ ነገውንም ቀጨ
(ለልጆቻችን. . .)
#seifetemam
@seifetemam
የኔ ክረምት
የከረረን ጽልመት
በምናቤ ሳክም
በከረረ ክረምት
በነጠላ ሳዘግም
ጽልመቱም አልነጋ ክረምቱም አልባተ
ልቤን ከገላዬ መለየት አቃተ
@seifetemam
#seifetemam
የከረረን ጽልመት
በምናቤ ሳክም
በከረረ ክረምት
በነጠላ ሳዘግም
ጽልመቱም አልነጋ ክረምቱም አልባተ
ልቤን ከገላዬ መለየት አቃተ
@seifetemam
#seifetemam
👍1
አንዷ መንገድ
አንዲት መስመርብቻ
በዓይኔ ፊት አለች
ደሞም ከሷ ውጪ
ችክችክ እና ድልዝ
ለንባብ አይመች
ይቺ ደማቅ መስመር
ይቺ ደማቅ መንገድ
እራሷን ዘርግታ
ወደራሷ ምትወስድ
እራሷን አንድዳ
ነድዳ ‘ምትማገድ
ይኧው ከሷ ውጪ
ቅዠት ነው ድንብርብር
ሰልፍ የሳተ ጉንዳን
የማይቀድስ ደብር
ጭስ የሌለው እጣን
የሚያሳስቅ ቀብር
የሚታለም እውን
የሚላፋ ነብር
እውነትን ፈለኳት
እንኋት ደማምቃ
አየኋት ሳልለፋ
በመስመሯ መጥቃ
በጉልህ ተጽፋ
ማተርኩ ወደ ፍቅር
ትታያለች ዘልጋ
ክረምቱንም በጋ
ሌሊቱን ቀን አርጋ
መስመሯን አፍቅራ
ፍቅር መስመር ፈጥራ
ባ’ለም ካለው ሁሉ
በጎውን ተመኘው
በአንድነት አንድ ሁኖ
አንዲት መስመር ላይ ነው
ከዛች መስመር ውጭ
ሁሉ ችክችክ ሁሉ ድልዝ
ለንባብ አይመች
እውን አልባ ውጥንቅጥ
የ’ልም አለም አደንዛዥ
ያለ መስሎ ሚያጥጥ
ሰው በቁም ‘ሚያስቃዥ
ያባይ ስጋ ቅጥቅጥ
የበረሃ ሚራዥ
2008
@seifetemam #seifetemam
አንዲት መስመርብቻ
በዓይኔ ፊት አለች
ደሞም ከሷ ውጪ
ችክችክ እና ድልዝ
ለንባብ አይመች
ይቺ ደማቅ መስመር
ይቺ ደማቅ መንገድ
እራሷን ዘርግታ
ወደራሷ ምትወስድ
እራሷን አንድዳ
ነድዳ ‘ምትማገድ
ይኧው ከሷ ውጪ
ቅዠት ነው ድንብርብር
ሰልፍ የሳተ ጉንዳን
የማይቀድስ ደብር
ጭስ የሌለው እጣን
የሚያሳስቅ ቀብር
የሚታለም እውን
የሚላፋ ነብር
እውነትን ፈለኳት
እንኋት ደማምቃ
አየኋት ሳልለፋ
በመስመሯ መጥቃ
በጉልህ ተጽፋ
ማተርኩ ወደ ፍቅር
ትታያለች ዘልጋ
ክረምቱንም በጋ
ሌሊቱን ቀን አርጋ
መስመሯን አፍቅራ
ፍቅር መስመር ፈጥራ
ባ’ለም ካለው ሁሉ
በጎውን ተመኘው
በአንድነት አንድ ሁኖ
አንዲት መስመር ላይ ነው
ከዛች መስመር ውጭ
ሁሉ ችክችክ ሁሉ ድልዝ
ለንባብ አይመች
እውን አልባ ውጥንቅጥ
የ’ልም አለም አደንዛዥ
ያለ መስሎ ሚያጥጥ
ሰው በቁም ‘ሚያስቃዥ
ያባይ ስጋ ቅጥቅጥ
የበረሃ ሚራዥ
2008
@seifetemam #seifetemam