Forwarded from Poetic Saturdays
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Day 3 of 31 Days of Poetry coming straight from Haileab Zeleke!
Forwarded from Poetic Saturdays
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Tsion brings us this beautiful piece on Day 12!
Forwarded from Events Ethiopia (Events Ethiopia Bot 🤖)
በልብ የቀበሩት
አይኖቿ ሲሰርቁኝ፤ እኔም ሰርቄያቸዉ፣
ምኞቴን አርግዤ፤ ትግል ገጠምኳቸዉ፣
የሚሸነፍ ጠፍቶ፤ ተዉ ሺሸኝ…! አልሸሽም…!
እንዳዉ ስንባባል፣
የጊዜ መቁጠሪያ፤ ለካ ጥሎን ሄዷል፡፡
በሱለይ አደም
አይኖቿ ሲሰርቁኝ፤ እኔም ሰርቄያቸዉ፣
ምኞቴን አርግዤ፤ ትግል ገጠምኳቸዉ፣
የሚሸነፍ ጠፍቶ፤ ተዉ ሺሸኝ…! አልሸሽም…!
እንዳዉ ስንባባል፣
የጊዜ መቁጠሪያ፤ ለካ ጥሎን ሄዷል፡፡
በሱለይ አደም
እኛ ቤት ሴት አለ
በአባዎች አለም እነ እማ ባቆሙት
መኩሪያዋ እልፍ ነው የሶስት ወንዶች እናት
የሶስት ወንዶች እናት
በወንዱም በሴቱም አለም እየገባች
ጾታዋን ተሻግራ ሁሉን እያሳየች
ወንድ ልጆችዋ ውስጥ ሴትነትን አየች
እኔ ትንሹ ነኝ የመጨረሻው ልጅ
ቃጭሌን አንቃጭላ ዱብ ያደረገችኝ
ይህ ቃጭል ሲንቃጨል
አባቴ ደስ አለው ወንድ ልጅ ሲደገም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልብ እንጂ ሴት አልተወለደም
ሴትነት ውስጤ አለ
ተፈጥሮ ከእናቴ ተማክረው የዘሩት
ቤተሰብ ከመንደር ተባብረውም ቢያጥሩት
በሰብዓዊ ለዛ የማሰቢያ ጥጌ
አጼ ሆኜ ሳለሁ ያረገኝ እቴጌ
ሴትነት ውስጤ አለ
የአንደበቴ አራሚ የኔነቴ አንዱ መልክ
የጉልበቴ ሚዛን የሰውነቴም ልክ
እወቀው አባቴ እወቀው ወንድሜ አንተም ውስጥ እኔም ውስጥ ሴትነት አለልክ
ይህን እጹብ ጸጋ ወንድሞቼ ስተው
እማዎች ባጸኑት መኖሪያ አለማቸው
አባ ሆነው ቀሩ ልክ እንደአባታቸው (የት አባታቸው)
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ!’ . . .
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ’ ብዬም የማልፎክር
በሴታዊ ገጼም ከቶም የማላፍር
ሴትነት ወንድነት ቅኝቴ ውስጥ የለም
ሰው መሆን ዜማዬ ለሁለቱም ቀሰም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልቤ እንጂ ሴት አልተወለደም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ወንዳወንድ ቀልቧ እንጂ ወንድ እናት አልሆነም
የተገደበ እንባ ኤሌትሪክ አልሰጠም
በአባቴ አዛኝነት ቤታችን አልሞተም
በኔ ቡና ማፍላት ጎረቤት አልሳቀም
ምክንያቱም . . .
የሶስት ወንዶች እናት ወንዶች ውስጥ ሴት እንጂ ሴት አልወለደችም
እነ እማ ባቆሙት በአባዎች አለም
እኛ ቤት ሴት አለ እኛ ቤት ሴት የለም
ሰይፈ ተማም 2011
በአባዎች አለም እነ እማ ባቆሙት
መኩሪያዋ እልፍ ነው የሶስት ወንዶች እናት
የሶስት ወንዶች እናት
በወንዱም በሴቱም አለም እየገባች
ጾታዋን ተሻግራ ሁሉን እያሳየች
ወንድ ልጆችዋ ውስጥ ሴትነትን አየች
እኔ ትንሹ ነኝ የመጨረሻው ልጅ
ቃጭሌን አንቃጭላ ዱብ ያደረገችኝ
ይህ ቃጭል ሲንቃጨል
አባቴ ደስ አለው ወንድ ልጅ ሲደገም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልብ እንጂ ሴት አልተወለደም
ሴትነት ውስጤ አለ
ተፈጥሮ ከእናቴ ተማክረው የዘሩት
ቤተሰብ ከመንደር ተባብረውም ቢያጥሩት
በሰብዓዊ ለዛ የማሰቢያ ጥጌ
አጼ ሆኜ ሳለሁ ያረገኝ እቴጌ
ሴትነት ውስጤ አለ
የአንደበቴ አራሚ የኔነቴ አንዱ መልክ
የጉልበቴ ሚዛን የሰውነቴም ልክ
እወቀው አባቴ እወቀው ወንድሜ አንተም ውስጥ እኔም ውስጥ ሴትነት አለልክ
ይህን እጹብ ጸጋ ወንድሞቼ ስተው
እማዎች ባጸኑት መኖሪያ አለማቸው
አባ ሆነው ቀሩ ልክ እንደአባታቸው (የት አባታቸው)
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ!’ . . .
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ’ ብዬም የማልፎክር
በሴታዊ ገጼም ከቶም የማላፍር
ሴትነት ወንድነት ቅኝቴ ውስጥ የለም
ሰው መሆን ዜማዬ ለሁለቱም ቀሰም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልቤ እንጂ ሴት አልተወለደም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ወንዳወንድ ቀልቧ እንጂ ወንድ እናት አልሆነም
የተገደበ እንባ ኤሌትሪክ አልሰጠም
በአባቴ አዛኝነት ቤታችን አልሞተም
በኔ ቡና ማፍላት ጎረቤት አልሳቀም
ምክንያቱም . . .
የሶስት ወንዶች እናት ወንዶች ውስጥ ሴት እንጂ ሴት አልወለደችም
እነ እማ ባቆሙት በአባዎች አለም
እኛ ቤት ሴት አለ እኛ ቤት ሴት የለም
ሰይፈ ተማም 2011
Forwarded from Арбитражница dooradas (🦋ሱራ ቢራቢሮ 🦋)
ብርዕ – በደም ዕንባ / ሙሉጌታ ተስፋዬ
በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ጥራና
ባፅሜ ቀሰም ብርዕ
በህይወት ማቅለሚያው
ጠርቤ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
የራሴ ጉልቻ … አንገቴ አለ ዘምበል
የደም ወዜ ጠለል … እንባዬ አለ ከምበል
በሞት ሞት ጣረሞት … <በልቤ ልብ በል!>
ሥጋት አንድውጋት
ነፍሴን ሲሰንጋት
በቅኔ እንቆቅልሽ … ቁልቁል ተቆልፌ
በእምነት … እምም እመ-እዝነት
በህልም ዓለም ሽምጥ ግልቢያ ተሰልፌ
ለሥጋ ታርቄ
ለገላ መርቄ
እርቃኔን ወጥቼ – ግቤኔን አስጥቼ
የጎኔን ጨረስኩት – ሆዴን ስሸነግል
ለነገ ራሴ ስንቅ – ልቃንጣዬ አገልግል።
ካምና ከታች አምናው
የጉልበት የጤናው
ቢታይ ሁለንተናው – <ሁሉ> ሁለመናው
የልቤ ልብ በል – ለልቤ ሲጠናው
ብቻ ላይኔ ብቻ – ላይኔ ለብረቱ – ላይኔ ብቻ ቀናው!
ለታይታ ለዝናው …
በሰው ፊት በሸንጎ ለወግ ማ’ርግ ዝናው!!
አዎ! በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ብራና
በብርዔ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
ደም እንባ – ደም እንባ – እንበለ እንባ ደም
ሕይወት እንጉርጉሮ – በአትም አይታደም።
(ለሚንቁኝ – ለማያውቁኝ)
29/7/84
ባለቅኔ ሙልጌታ ተስፋዬገ(አያ ሙሉ የወሎ አበጋር ወድ አለቃ ጅብ አይበላሽ)
🦋🦋👇🦋🦋
https://telegram.me/sufafel
✅🦋👆🦋✅
✍🦋 ሙሌዋ ✍ 🦋
🦋
በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ጥራና
ባፅሜ ቀሰም ብርዕ
በህይወት ማቅለሚያው
ጠርቤ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
የራሴ ጉልቻ … አንገቴ አለ ዘምበል
የደም ወዜ ጠለል … እንባዬ አለ ከምበል
በሞት ሞት ጣረሞት … <በልቤ ልብ በል!>
ሥጋት አንድውጋት
ነፍሴን ሲሰንጋት
በቅኔ እንቆቅልሽ … ቁልቁል ተቆልፌ
በእምነት … እምም እመ-እዝነት
በህልም ዓለም ሽምጥ ግልቢያ ተሰልፌ
ለሥጋ ታርቄ
ለገላ መርቄ
እርቃኔን ወጥቼ – ግቤኔን አስጥቼ
የጎኔን ጨረስኩት – ሆዴን ስሸነግል
ለነገ ራሴ ስንቅ – ልቃንጣዬ አገልግል።
ካምና ከታች አምናው
የጉልበት የጤናው
ቢታይ ሁለንተናው – <ሁሉ> ሁለመናው
የልቤ ልብ በል – ለልቤ ሲጠናው
ብቻ ላይኔ ብቻ – ላይኔ ለብረቱ – ላይኔ ብቻ ቀናው!
ለታይታ ለዝናው …
በሰው ፊት በሸንጎ ለወግ ማ’ርግ ዝናው!!
አዎ! በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ብራና
በብርዔ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
ደም እንባ – ደም እንባ – እንበለ እንባ ደም
ሕይወት እንጉርጉሮ – በአትም አይታደም።
(ለሚንቁኝ – ለማያውቁኝ)
29/7/84
ባለቅኔ ሙልጌታ ተስፋዬገ(አያ ሙሉ የወሎ አበጋር ወድ አለቃ ጅብ አይበላሽ)
🦋🦋👇🦋🦋
https://telegram.me/sufafel
✅🦋👆🦋✅
✍🦋 ሙሌዋ ✍ 🦋
🦋
Forwarded from Poetic Saturdays
አባ ዳኘው-አጤ ምኒልክና ባዕታ ማርያም
Jan 21, 2020
| Written by
ታመነ መንግስቴ
|
ታሪክ/ history
"አለ ወልድ አልነሳኝ
ስለቴን በከንቱ
የተገፋን ሰሚ
ባዕታ አለች እናቱ።"
ይች ስንኝ በወጣቱ የሙዚቃ ባለሙያ ዳን አድማሱ ዳምጠው "አራት ኪሎ" የተሰኘች አነጋጋሪ እና ቅኒያም ነጠላ ዜማ ውስጥ ያለች ናት።
ታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም እዚያው አራት ኪሎ ከግቢ ገብርኤል ከፍ ብላ ለእምየ ምኒልክ መታሰቢያ ትሆን ዘንድ በልጃቸውና በዘመኗ ኢትዮጵያን ንግስተ ነገስት ሆና ባስተዳደረቻት ዘውዲቱ ምኒልክ የተሠራች ናት።
የታላቁ ንጉስ ዓጤ ምኒልክ እና ባለቤታቸው የኢትዮጵያ ብርሃን -እቴጌ ጣይቱ ብጡል መቃብርም በዚችው ገዳም ነው።
ለዚህም ይመስላል ለዛሬው ትውልድ እንደ ማንቂያ ደወል የሚሆኑ፣እንደ ወይን ጠጅ የሚጣፍጡ የአባ ዳኘው-አጤ ምኒልክና ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ መልዕክቶች በአፀደ ገዳሟ በጉልህ ተፅፈው መነበባቸው።
እነሆ እንደ መነሻ፦አባ ዳኘው ጣሊያንን አፈር አስግጠው ካባረሩት በሗላ ስለ ህዝባቸው መዘመን አብዝተው ይጨነቁ ጀመር።ጠላታቸውን ያሸነፉት በበዛ የፈጣሪያቸው ድጋፍና በህዝባቸው ቀናኢነት እንጅ በተጠና የጦር ስልት፣በተለካ ጥበብ አለመሆኑን አሰቡ።እናም ዘመናዊ ትምህርትን ማስፋፋት የማይታለፍ ተግባራቸው መሆኑን አመኑ።እንዲህም አሉ።
"በጣም ወደ ሗላ የቀረን ህዝቦች ነንና፤ገና የምንሰራው ብዙ ስራ ስላለ ወጣቶቻችንን ማስተማር አለብን።"
ይሁንና አባ ዳኘውን እንዲህ ያሳሰባቸው የትምህርት ጉዳይ ከድፍን ምዕተ ዓመት(100ዓመት) በሗላም እንደነበረ አለ። ይሄን ያስተዋለው ዳን አድማሱ "በአራት ኪሎ" ዘፈኑ፦
"የአውራ ዶሮ ቁንጮ ስሙ ነው ኮኮን
ስንቱ ቆቡን ጫነ ያልተማረውን።"
እያለ የትምህርታችንን ውድቀት ያሽሟጥጠዋል።
እምየ ምኒልክ ተዓምር በሰሩባት አገር ያላቸው የህይወት ገመድ መመንመኑን እየተረዱ ነው።ሞት ብዙ ጊዜ ድል ያደረጉትን ንጉስ ሊወስዳቸው እየመጣ ይመስላል።እሳቸውም በዓለም የሚፀፀቱበት የለምና በፀጋ ተቀብለውታል ፤ግን በተጋደሉላት አገራቸው ኢትዮጵያ ከእሳቸው ህልፈት በሗላ የሚመጣው የስልጣን ሽኩቻ ለዳግም አድዋ ዳርጓት ኢትዮጵያን እንዳያሳጣ ይሰጋሉ።ስለሆነም መኳንንቱን ሰብስበው እንዲህ ሲሉ የመሰናበቻ መልዕክታቸውን አደረሡ፦
"እኔ እስካሁን በፍቅር እንዳኖርሗችሁ እናንተም በፍቅር ተስማምታችሁ እንድትኖሩ እለምናችሗለሁ።"
የምኒልክ ልጅ ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱም ምንም እንኳን ታሪካቸው በብልጣብልጡ እንደራሴያቸውና የሗላው ንጉሰ ነገስት ተፈሪ መኮነን የተጋረደ ቢመስልም በአገራቸው ጉዳይ የዋዛ ሴት አይደሉም።
በታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ያለው ነፍስ አለምላሚ መልዕክታቸው ይሄን ይመስላል፦
"መሪዎች በቤተ-መንግስት ቢቀመጡ፣ህዝቡም በየግል ቤቱ ቢቀመጥ መጠለያ ይባላል፤እንጅ የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ ናት!"
ሁሉንም መልዕክቶች አራት ኪሎ ከቤተ-መንግስቱ በስተ ምስራቅ ካለችው የታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ቅጥር ግቢ አገኘሗቸው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ይቆየን!
Copyright ©2020 All rights reserved | This site is owned by NConsults
Jan 21, 2020
| Written by
ታመነ መንግስቴ
|
ታሪክ/ history
"አለ ወልድ አልነሳኝ
ስለቴን በከንቱ
የተገፋን ሰሚ
ባዕታ አለች እናቱ።"
ይች ስንኝ በወጣቱ የሙዚቃ ባለሙያ ዳን አድማሱ ዳምጠው "አራት ኪሎ" የተሰኘች አነጋጋሪ እና ቅኒያም ነጠላ ዜማ ውስጥ ያለች ናት።
ታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም እዚያው አራት ኪሎ ከግቢ ገብርኤል ከፍ ብላ ለእምየ ምኒልክ መታሰቢያ ትሆን ዘንድ በልጃቸውና በዘመኗ ኢትዮጵያን ንግስተ ነገስት ሆና ባስተዳደረቻት ዘውዲቱ ምኒልክ የተሠራች ናት።
የታላቁ ንጉስ ዓጤ ምኒልክ እና ባለቤታቸው የኢትዮጵያ ብርሃን -እቴጌ ጣይቱ ብጡል መቃብርም በዚችው ገዳም ነው።
ለዚህም ይመስላል ለዛሬው ትውልድ እንደ ማንቂያ ደወል የሚሆኑ፣እንደ ወይን ጠጅ የሚጣፍጡ የአባ ዳኘው-አጤ ምኒልክና ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ መልዕክቶች በአፀደ ገዳሟ በጉልህ ተፅፈው መነበባቸው።
እነሆ እንደ መነሻ፦አባ ዳኘው ጣሊያንን አፈር አስግጠው ካባረሩት በሗላ ስለ ህዝባቸው መዘመን አብዝተው ይጨነቁ ጀመር።ጠላታቸውን ያሸነፉት በበዛ የፈጣሪያቸው ድጋፍና በህዝባቸው ቀናኢነት እንጅ በተጠና የጦር ስልት፣በተለካ ጥበብ አለመሆኑን አሰቡ።እናም ዘመናዊ ትምህርትን ማስፋፋት የማይታለፍ ተግባራቸው መሆኑን አመኑ።እንዲህም አሉ።
"በጣም ወደ ሗላ የቀረን ህዝቦች ነንና፤ገና የምንሰራው ብዙ ስራ ስላለ ወጣቶቻችንን ማስተማር አለብን።"
ይሁንና አባ ዳኘውን እንዲህ ያሳሰባቸው የትምህርት ጉዳይ ከድፍን ምዕተ ዓመት(100ዓመት) በሗላም እንደነበረ አለ። ይሄን ያስተዋለው ዳን አድማሱ "በአራት ኪሎ" ዘፈኑ፦
"የአውራ ዶሮ ቁንጮ ስሙ ነው ኮኮን
ስንቱ ቆቡን ጫነ ያልተማረውን።"
እያለ የትምህርታችንን ውድቀት ያሽሟጥጠዋል።
እምየ ምኒልክ ተዓምር በሰሩባት አገር ያላቸው የህይወት ገመድ መመንመኑን እየተረዱ ነው።ሞት ብዙ ጊዜ ድል ያደረጉትን ንጉስ ሊወስዳቸው እየመጣ ይመስላል።እሳቸውም በዓለም የሚፀፀቱበት የለምና በፀጋ ተቀብለውታል ፤ግን በተጋደሉላት አገራቸው ኢትዮጵያ ከእሳቸው ህልፈት በሗላ የሚመጣው የስልጣን ሽኩቻ ለዳግም አድዋ ዳርጓት ኢትዮጵያን እንዳያሳጣ ይሰጋሉ።ስለሆነም መኳንንቱን ሰብስበው እንዲህ ሲሉ የመሰናበቻ መልዕክታቸውን አደረሡ፦
"እኔ እስካሁን በፍቅር እንዳኖርሗችሁ እናንተም በፍቅር ተስማምታችሁ እንድትኖሩ እለምናችሗለሁ።"
የምኒልክ ልጅ ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱም ምንም እንኳን ታሪካቸው በብልጣብልጡ እንደራሴያቸውና የሗላው ንጉሰ ነገስት ተፈሪ መኮነን የተጋረደ ቢመስልም በአገራቸው ጉዳይ የዋዛ ሴት አይደሉም።
በታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ያለው ነፍስ አለምላሚ መልዕክታቸው ይሄን ይመስላል፦
"መሪዎች በቤተ-መንግስት ቢቀመጡ፣ህዝቡም በየግል ቤቱ ቢቀመጥ መጠለያ ይባላል፤እንጅ የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ ናት!"
ሁሉንም መልዕክቶች አራት ኪሎ ከቤተ-መንግስቱ በስተ ምስራቅ ካለችው የታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ቅጥር ግቢ አገኘሗቸው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ይቆየን!
Copyright ©2020 All rights reserved | This site is owned by NConsults
ከላይ👆🏻 የምታዩት ጽሁፍ መግቢያ ላይ የተጠቀሰው ስንኝ ከታች 👇🏽 በምታገኙት ተስተካክሎ ይነበብ
Forwarded from Poetic Saturdays
Can't get enough poetry in your life?! Come on down to Pallet (near "Yugo Church", Bole) on Thursday for a night of connection with our friends at Spittoon!
https://facebook.com/events/s/spittoon-poetry-reading-night/591908678309967/?ti=as
https://facebook.com/events/s/spittoon-poetry-reading-night/591908678309967/?ti=as
Facebook
Spittoon Poetry Reading Night
Spittoon Addis Ababa hosts regular literary events and is one of the branches of the Beijing-based Art Collective.
Spittoon is happy to present our first Poetry Reading Night in 2020. It will take...
Spittoon is happy to present our first Poetry Reading Night in 2020. It will take...
Forwarded from ራማ ምስሎች / Rama Pictures (Tarik Tag)
Ethiopian hiphop music remix
https://youtu.be/yTtoOjyqIhI
https://youtu.be/yTtoOjyqIhI
YouTube
Marvin Gaye Ft Tarik : Music Remix Ethiopian Hiphop
Ethiopia : America Marvin gaye music remix by Tarik 2020
Forwarded from Written Soul (Hermela)
Abstract
Utter silence
I listen
Whooshing sound of
cars
Some how it makes me calm
The moon lighting the darkness
Some how it heals
Some how the beauty
Puts me in trance
Some how it is easier
To bare my soul
To people I barely know
It is okay to be bare
And sometimes
it is okay
To wallow in pain
I want to live here
Here is just me
Here is just me alone
Here is my home
Do we have a meaning?
Do you have a meaning?
Do I?
We work, sleep and eat
Wake up to do it all again
What if this is hell?
What if hell is just like a broken
Record
Repitition of the same thing over and over
Suddenly you wouldn't know when it will be over
I say all this while I am sober
When you pause
Only eyes can see
Ears can hear
Fears dissapear
life reappear
And you exist
I crave this pause
The one that closed the door
Is my shadow
who likes to to oppose
He is in control
I suppose
Somehow they misunderstood
It is he who is talking
Not me
It is he who you seeing
Not me
"Me" is a misconstruction
Made by the perception of what I think is others perception of me
I really don't know what "Me" is
I don't know "I"
As soon as the word "I" exist
We perish
This abstract mind
Science couldn't decode
History couldn't record
This isn't my mind speaking
This isn't my body your witnessing
Just the formation of DNA
Manifestation of information
That lived for decade
-Anima
#Existence
Utter silence
I listen
Whooshing sound of
cars
Some how it makes me calm
The moon lighting the darkness
Some how it heals
Some how the beauty
Puts me in trance
Some how it is easier
To bare my soul
To people I barely know
It is okay to be bare
And sometimes
it is okay
To wallow in pain
I want to live here
Here is just me
Here is just me alone
Here is my home
Do we have a meaning?
Do you have a meaning?
Do I?
We work, sleep and eat
Wake up to do it all again
What if this is hell?
What if hell is just like a broken
Record
Repitition of the same thing over and over
Suddenly you wouldn't know when it will be over
I say all this while I am sober
When you pause
Only eyes can see
Ears can hear
Fears dissapear
life reappear
And you exist
I crave this pause
The one that closed the door
Is my shadow
who likes to to oppose
He is in control
I suppose
Somehow they misunderstood
It is he who is talking
Not me
It is he who you seeing
Not me
"Me" is a misconstruction
Made by the perception of what I think is others perception of me
I really don't know what "Me" is
I don't know "I"
As soon as the word "I" exist
We perish
This abstract mind
Science couldn't decode
History couldn't record
This isn't my mind speaking
This isn't my body your witnessing
Just the formation of DNA
Manifestation of information
That lived for decade
-Anima
#Existence
Forwarded from Арбитражница dooradas (C-ራክ)
ትሑት ምህላ
=========
አቤቱ ጌታ ሆይ ፣
የኢትዮጵያውያንን እምነት
የግሪክን ጥበብ መሻት
የአይሁድን ምልክት ጥማት
የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት-
ልክፍት
የሱፊን ተደሞ
የዜንን አርምሞ
የተመሥጦ መገለጥን ምትሐት ፣
......አጣምረህ ለነብሴ ሥጣት!
በዚህ፣ኃይሏ ግርማ
እንደ ጨለማ ፣ ቀለም ድንበርን ታሥማማ.....።
አሜን።
ዲበኩሉ ጌታ
ሰኔ ፳ ፳፻፰ ዓ.ም
-----------//----------
የምድር ዘላለም ድንቅ መፅሀፍ ነው በተገኘበት ይነበብ!! ያነበበ ብዙ ያተርፋል
#
@sufafel
@sufafel
@sufafel
=========
አቤቱ ጌታ ሆይ ፣
የኢትዮጵያውያንን እምነት
የግሪክን ጥበብ መሻት
የአይሁድን ምልክት ጥማት
የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት-
ልክፍት
የሱፊን ተደሞ
የዜንን አርምሞ
የተመሥጦ መገለጥን ምትሐት ፣
......አጣምረህ ለነብሴ ሥጣት!
በዚህ፣ኃይሏ ግርማ
እንደ ጨለማ ፣ ቀለም ድንበርን ታሥማማ.....።
አሜን።
ዲበኩሉ ጌታ
ሰኔ ፳ ፳፻፰ ዓ.ም
-----------//----------
የምድር ዘላለም ድንቅ መፅሀፍ ነው በተገኘበት ይነበብ!! ያነበበ ብዙ ያተርፋል
#
@sufafel
@sufafel
@sufafel
Forwarded from Deleted Account
በከፍታ መብረር ከመሬት ያርቃል ብለው የመከሩ ፡ ሠጎን እና ዶሮ ተመሬት አደሩ ። ሁለቱም ልክ ነው ያለችው ሦረኔ ትንሹን ተራምዳ፡ ትንሹን በራ ነው ፡ ሠማይ እን ምድርን የምታሥታርቀው ፡ በሠማዩ ነጥታ በምድሩ ጠቆረች ፡ ባለ ሁለት መልኳ
በመዘነቋ ነው ጅግራ የተባለች ። የጅግራም ትርጉሙ ፡ ከጃችን ሥያሜ "ጅ" እየጎተተ ከታች ካለው እግር ... ግንን እየሣበ ...
በመዘነቋ ነው ጅግራ የተባለች ። የጅግራም ትርጉሙ ፡ ከጃችን ሥያሜ "ጅ" እየጎተተ ከታች ካለው እግር ... ግንን እየሣበ ...
ማን ያውቃል?🙇♂️
በ ቶማስ አድማሱ @Mmiinnuu
. . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . .
ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል
ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል?
ለመውለድ ያቀደ ገና ከመውደዱ የምሩን ይሞታል?
ማን ያውቃል?
ባይኔ መኃሉ ላይ ካይኔ ጥቁሩ ላይ
ብሌኔን ታቅፈሽ በዓለም ሌላ ላላይ
ላንቺ እየዘመርኩ ሆንኩኝ ማኅሌታይ።
....
እተረከዝሽ ስር ላንቺ ስል ወረድሁ/ኝ
ትተሺኝ ብትበርሪ መልአክ ነች አልሁ/ኝ
ማን ያውቃል እውነትን ፤ እውነትም ማን ያውቃል?
ማን ነው የሚጸና ከሃቅ እና ከቃል??
ማን ያውቃል?
እጄን ይዘሽ ከእጅሽ ሆኜ በመሃሉ
ከብደሽ ላይኔ ሌላው አንሶ ቀልሎ ሁሉ
በሳቀብን ስናሽካካ የረታንን ስንጥለው
ባረፍድ እንኳ እንዳይስቁ አጣት ብለው
ታቅፈኝ ይሆን ፤አውቃት ይሆን፤ አያት ይሆን?
ቀን መቃዠት አንቺን ማለም ሌሊት ሲሆን
ማን ያውቃል ?
መገጣጠም እንጂ አሁን አለ "እውነት"?
የቱ ነው ሃቅ ሚሆን ከህልም እና ቅዠት?
የቱ ነው የሚያም
ከእውነት ማጣት እና የውሸት ከማግኘት?
ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል
ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል?
ማን ያውቃል?
በ ቶማስ አድማሱ @Mmiinnuu
. . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . .
ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል
ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል?
ለመውለድ ያቀደ ገና ከመውደዱ የምሩን ይሞታል?
ማን ያውቃል?
ባይኔ መኃሉ ላይ ካይኔ ጥቁሩ ላይ
ብሌኔን ታቅፈሽ በዓለም ሌላ ላላይ
ላንቺ እየዘመርኩ ሆንኩኝ ማኅሌታይ።
....
እተረከዝሽ ስር ላንቺ ስል ወረድሁ/ኝ
ትተሺኝ ብትበርሪ መልአክ ነች አልሁ/ኝ
ማን ያውቃል እውነትን ፤ እውነትም ማን ያውቃል?
ማን ነው የሚጸና ከሃቅ እና ከቃል??
ማን ያውቃል?
እጄን ይዘሽ ከእጅሽ ሆኜ በመሃሉ
ከብደሽ ላይኔ ሌላው አንሶ ቀልሎ ሁሉ
በሳቀብን ስናሽካካ የረታንን ስንጥለው
ባረፍድ እንኳ እንዳይስቁ አጣት ብለው
ታቅፈኝ ይሆን ፤አውቃት ይሆን፤ አያት ይሆን?
ቀን መቃዠት አንቺን ማለም ሌሊት ሲሆን
ማን ያውቃል ?
መገጣጠም እንጂ አሁን አለ "እውነት"?
የቱ ነው ሃቅ ሚሆን ከህልም እና ቅዠት?
የቱ ነው የሚያም
ከእውነት ማጣት እና የውሸት ከማግኘት?
ከደስታና ከሐዘን የቱ ይሰነብታል
ለአ'ንዲት ቅጽፈት ሳቅ ዓይን እንባ ያግታል?
ማን ያውቃል?
Forwarded from Poetic Saturdays
ተዘዋውሯል!
በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት የሀገራዊ የግጥም ውድድራችንን ወደ መጋቢት 11 አዘዋውረነዋል።
ያኔ እንገናኝ!
POSTPONED! Due to scheduling concerns, we have decided to postpone the National Poetry Slam to March 20th! See you there!
በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት የሀገራዊ የግጥም ውድድራችንን ወደ መጋቢት 11 አዘዋውረነዋል።
ያኔ እንገናኝ!
POSTPONED! Due to scheduling concerns, we have decided to postpone the National Poetry Slam to March 20th! See you there!