🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! የሽልማቱን አይነት እና መጠን ከነገ ወድያ አሳውቃለሁ ። ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! የሽልማቱን አይነት እና መጠን ከነገ ወድያ አሳውቃለሁ ። ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ጥንብ አንሳ
በዘመነ ጥንባት ሰው ከሰው ተሻትቶ በረከሰበቱ
ብዙኃን አሉና ሰውነታቸው ውስጥ ሞተው የሸተቱ
ወይ ልብህን አንፃ ሙታኑን ቀስቅሳ
ወይ ሆድህን ሙላ ሁንና ጥንብአንሳ
@seifetemam #seifetemam
በዘመነ ጥንባት ሰው ከሰው ተሻትቶ በረከሰበቱ
ብዙኃን አሉና ሰውነታቸው ውስጥ ሞተው የሸተቱ
ወይ ልብህን አንፃ ሙታኑን ቀስቅሳ
ወይ ሆድህን ሙላ ሁንና ጥንብአንሳ
@seifetemam #seifetemam
👍1
እሺ እንዴትናችሁልኝ? አዲሱ አመት አያያዙ የተመቻችሁ ይመስላል ። የግጥም ውድድራችን ተጀምሯል እስከ እሁድ አስር ሰዓት ይቆያል ። ግጥማችሁን በ @Seifdman አድርሱኝ ። ከመሳተፍ ማንበብን የምትመርጡ ከሆነ ለ 👍 እንዲሁም ለ 👎 በመምረጥ አሸናፊ ግጥሞችን እንለይ ። በድምጽ የተቀዱም ካሉ እቀበላለሁ ። መልካም ውድድር ።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
40 ልብ
አይ እታባ ...
እንዴት ቀለድሽ ባክሽ
ሆድ ሆዴን ቢበላው ይመጣል ማለትሽ
አልታይህ ቢለኝ የያኔው ተረትሽ
አልጨበጥ ቢለኝ የፊተኛው ተስፋሽ
ይኸው እታባዬ ...... ቧልተኛ ነሽ አልኩሽ
ቁጥር እንደው አያፍር .....
ደንደሱን አስፍቶ ደሞ እያጠበበ፤ ይከንፋል... ይበራል
ሺዘጠኙን በቅጡ ሳንኖር፤ ፪ሺ ሠፍቶ ያተራምሰናል
እሱ ምን አለበት..... እንዳባይ ይነጉዳል...
እኔ አለሁ እዚ በሀሳብ የምርድ
አርባዬን ቀርጥፌ አፋሽ የሆንኩ አመድ
እና እታባዬ.....
የታል ታድያ ያ ልብ የነገርሽኝ ቀድሞ
በ40 ዘመኔ የማገኘው ቆሞ... (አልያም ተጋድሞ)
ከብትንትን ኑሮ የሚገላግለኝ
ከ40 ልብ ህይወት የሚያሰናብተኝ
የታለ እታባ?? ... የታለ??...
አይ እታባ ...
እንዴት ቀለድሽ ባክሽ
ሆድ ሆዴን ቢበላው ይመጣል ማለትሽ
አልታይህ ቢለኝ የያኔው ተረትሽ
አልጨበጥ ቢለኝ የፊተኛው ተስፋሽ
ይኸው እታባዬ ...... ቧልተኛ ነሽ አልኩሽ
ቁጥር እንደው አያፍር .....
ደንደሱን አስፍቶ ደሞ እያጠበበ፤ ይከንፋል... ይበራል
ሺዘጠኙን በቅጡ ሳንኖር፤ ፪ሺ ሠፍቶ ያተራምሰናል
እሱ ምን አለበት..... እንዳባይ ይነጉዳል...
እኔ አለሁ እዚ በሀሳብ የምርድ
አርባዬን ቀርጥፌ አፋሽ የሆንኩ አመድ
እና እታባዬ.....
የታል ታድያ ያ ልብ የነገርሽኝ ቀድሞ
በ40 ዘመኔ የማገኘው ቆሞ... (አልያም ተጋድሞ)
ከብትንትን ኑሮ የሚገላግለኝ
ከ40 ልብ ህይወት የሚያሰናብተኝ
የታለ እታባ?? ... የታለ??...
ውዴ
ዝምታሽ ቢጨንቀኝ ቴክስትሽ ቢርቀኝ
ስልኬ ያለልማዱ ብሬን ቢምርልኝ
አፌን አሞጥሙጬ ልነግርሽ ቆረጥኩኝ
እቱ የኔ አበባ....
ዝምታሽ ከባድ ነው ሆድን ያሸብራል
ቀልብንም አርቆ አንጀት ያላውሣል.....
ብዬ እንዳልልሽ.... ብዬ እንዳልልሽ
ቃላት አይገዙ በቂ ስንኝ የለኝ
እኔም ካንቺ የባስኩ ስንኞች የከዱኝ
ብቻ....
ጀማሪ መሆኔ እንዳይነቃብኝ
ኝ ኝ ኝ ..... እያልኩኝ
መግጠሙ ደብሮኝ
የሆዴን ሣልሸና ልተኛ ወሠንኩኝ።
(እባክሽ አደራ እንዳትስቂብኝ.ኝ ኝ ኝ..)
ኖታ
ዝምታሽ ቢጨንቀኝ ቴክስትሽ ቢርቀኝ
ስልኬ ያለልማዱ ብሬን ቢምርልኝ
አፌን አሞጥሙጬ ልነግርሽ ቆረጥኩኝ
እቱ የኔ አበባ....
ዝምታሽ ከባድ ነው ሆድን ያሸብራል
ቀልብንም አርቆ አንጀት ያላውሣል.....
ብዬ እንዳልልሽ.... ብዬ እንዳልልሽ
ቃላት አይገዙ በቂ ስንኝ የለኝ
እኔም ካንቺ የባስኩ ስንኞች የከዱኝ
ብቻ....
ጀማሪ መሆኔ እንዳይነቃብኝ
ኝ ኝ ኝ ..... እያልኩኝ
መግጠሙ ደብሮኝ
የሆዴን ሣልሸና ልተኛ ወሠንኩኝ።
(እባክሽ አደራ እንዳትስቂብኝ.ኝ ኝ ኝ..)
ኖታ
እዬዬ
ከውዶቹ መሃል አንድ ሰው አነሰኝ
ሀዘን ሆዴ ገብቶ እያንሰፈሰፈኝ
ጠቆረብኝ ውስጤ ልቤም ጨላለመ
ያሸከምኩት ተስፋ በአፈር አከተመ
እዬዬ ለራሴ እዬዬ ለሃገሬ
ታናሼ ሲቀድመኝ እኔ ተገትሬ
እዬዬ ለቋሚ ውዱን ለሸኘ ሰው
ከተመረጠማ የአብስራ ድንቅ ነው
ሰይፈ
ከውዶቹ መሃል አንድ ሰው አነሰኝ
ሀዘን ሆዴ ገብቶ እያንሰፈሰፈኝ
ጠቆረብኝ ውስጤ ልቤም ጨላለመ
ያሸከምኩት ተስፋ በአፈር አከተመ
እዬዬ ለራሴ እዬዬ ለሃገሬ
ታናሼ ሲቀድመኝ እኔ ተገትሬ
እዬዬ ለቋሚ ውዱን ለሸኘ ሰው
ከተመረጠማ የአብስራ ድንቅ ነው
ሰይፈ
ግዝት
አድምጡኝ እንጂ አትስሙኝ
በክፋት ጥላቻ በህይወት ገላችሁ
ከነመፈጠሬም በቁሜ ረስታችሁ
የአፈሬን ሳጥን በቅርቡ አይታችሁ
እንዳታለቅሱልኝ ...
ኻላ እንዳላዝንባችሁ
አትክልት አይደለሁ እንባችሁ አይረባኝ
ከሞት አለምልሞ ህይወት አይዘራብኝ
እንዲያው ከንቱ ድካም እንዳይሆንባችሁ
መኖሬን ከድታችሁ ሞቴን ካመናችሁ
ያኔ... በበድኔ ዙሪያ እንዳላይ ከባችሁ
በቁሜ እያለሁ ይኸው ገዘትኳችሁ።
እንዳታለቅሱልኝ...!!!
ኖታ
አድምጡኝ እንጂ አትስሙኝ
በክፋት ጥላቻ በህይወት ገላችሁ
ከነመፈጠሬም በቁሜ ረስታችሁ
የአፈሬን ሳጥን በቅርቡ አይታችሁ
እንዳታለቅሱልኝ ...
ኻላ እንዳላዝንባችሁ
አትክልት አይደለሁ እንባችሁ አይረባኝ
ከሞት አለምልሞ ህይወት አይዘራብኝ
እንዲያው ከንቱ ድካም እንዳይሆንባችሁ
መኖሬን ከድታችሁ ሞቴን ካመናችሁ
ያኔ... በበድኔ ዙሪያ እንዳላይ ከባችሁ
በቁሜ እያለሁ ይኸው ገዘትኳችሁ።
እንዳታለቅሱልኝ...!!!
ኖታ
ሁለት አለሜ
መጀመሪያ ሳይሽ ልቤ ምቱ ጠፋው
ግጥሜ ተበላሸ
ቀለሙ እየሸሸ
መጀመሪያ ሳውቅሽ ሰው አለኝ የሚለው
ቃልሽ ልቤን ወጋ
እንዴት ካንቺ ላውጋ
ክንፍ ያለኝ ይመስልጊዜን መራመጃ
ነገን ካንቺ ከረምኩ የዛሬዬን እንጃ
ጸዳልሽን አየሁ ከጎኔ ሲበራ
የቆዘመ ገጼን በሙቀት ሲጣራ
ደሞም ደስስ እያለ መልሶ ሲያስፈራ
እኔና አንቺ ብቻ ካለንበት ቦታ
ከቦን ያለም ሃዘን ከቦን ያለም ሆታ
ቅጽበታት ደምረን ስናረገው አፍታ
ዱካክ እንዳጠረው እንቅልፍ አልባ ጊዜ
ባንኖ መታ ልቤ ባንቺው ስልት አባዜ
ሁለት አለም ኖረኝ
አንደኛው የንቃት ሌላው የትካዜ
ሰይፈ ተማም 2010
መጀመሪያ ሳይሽ ልቤ ምቱ ጠፋው
ግጥሜ ተበላሸ
ቀለሙ እየሸሸ
መጀመሪያ ሳውቅሽ ሰው አለኝ የሚለው
ቃልሽ ልቤን ወጋ
እንዴት ካንቺ ላውጋ
ክንፍ ያለኝ ይመስልጊዜን መራመጃ
ነገን ካንቺ ከረምኩ የዛሬዬን እንጃ
ጸዳልሽን አየሁ ከጎኔ ሲበራ
የቆዘመ ገጼን በሙቀት ሲጣራ
ደሞም ደስስ እያለ መልሶ ሲያስፈራ
እኔና አንቺ ብቻ ካለንበት ቦታ
ከቦን ያለም ሃዘን ከቦን ያለም ሆታ
ቅጽበታት ደምረን ስናረገው አፍታ
ዱካክ እንዳጠረው እንቅልፍ አልባ ጊዜ
ባንኖ መታ ልቤ ባንቺው ስልት አባዜ
ሁለት አለም ኖረኝ
አንደኛው የንቃት ሌላው የትካዜ
ሰይፈ ተማም 2010
ለመስራት
ለመጨረስስ አልሰራም ለመስራት ልጨርስ እንጂ
ተጨርሶ ሲመረቅ እንደሚታደስ መንገድ
ስካሩ ጠፋ ሲባል መልሶ 'ሚንገዳገድ
እንኳን ተሻለህ ሲሉት እንደሚያቃስት ህመመኛ
ለመጨረስስ አንስራ ለመስራት እንጨርስ እኛ
ሰይፈ ተማም 2010
ለመጨረስስ አልሰራም ለመስራት ልጨርስ እንጂ
ተጨርሶ ሲመረቅ እንደሚታደስ መንገድ
ስካሩ ጠፋ ሲባል መልሶ 'ሚንገዳገድ
እንኳን ተሻለህ ሲሉት እንደሚያቃስት ህመመኛ
ለመጨረስስ አንስራ ለመስራት እንጨርስ እኛ
ሰይፈ ተማም 2010
ከመሬት ነኝ
መሬት አይደል መነሻዬ
መሬት ያጣሁ መሬት ሁኜ
መነሳትን ተጠይፌ
የወደቅኩኝ ተንሳፍፌ
እኔም ራሴ መሬት
ለመብቀያ ያበቀለኝ
ከመሬት ነኝ?
ከምሬት ነኝ?
ከምር የት ነኝ?
ቁንጥር አፈር ዘግኖ በእጁ ካበጃጀኝ
ቁንጽል አንቀጽ ጠቅሶ በእጁ 'ሚያስፈጀኝ
መሆኔ አይደለም ወይ ከመሬትም መሬት
ሲረማመዱብኝ እንቁዬን ደብቄ በቀን እኩለ ሌት
ሲዘንብ እምቦካ የቋጠርኩኝ አለት
ሲያርሱ 'ምበረበር
ሲበትኑ 'ምዘር
የማያዳብረኝ የሰጡኝ ምርጥ ዘር
አለቴን ገድዬ 'ማረገው አፈር
ጨረቃን ጋርጄ ፀሃይ የምሰፍር
ፀሃይ በዛ ብዬ ደሞ ምንጨረጨር
ህዋ ላይ ተጥዬ የማርፍበት የናፈቀኝ
አዎ መሬት ያጣሁ መሬት ነኝ
ቀማሽ ምላስ ሰጥቶ ጣ'ም 'ሚያስቆጥረኝ
ጣፋጭ ስኳር ነስቶ በጨዉ ሲያስመርረኝ
መሆኔ አይደለም ወይ ከምሬትም ምሬት
ወዳጄ ስሞታ ወዳጄ ጣ'ም ሃሞት
የማያጣኝ ከቤት
የማያጣኝ ከሬት
ብሶት የወለደው ብሶ ያንገሸገሸኝ
ጣ'ም ያጣሁ ምሬት ነኝ
አገር ማለት መሬት
አገር ማለት ምሬት
አገር ማለት እኔ
ተምታቶብኝ ድንገት
መሬት ምሬት ምርየት
መሬቱ ሰው አለው
አለው የሰው ኩሩ
'ራሱን እማይነጥል
ከዱሩ ከአፈሩ
ሲጠብቃት ኖሮ
ከሷው ነው አዳሩ
ይኸም ሰው ጨፍግጓል
መረሮታል ጠአሙ
መጣፈጥ ጠፍቶታል
መልኩም ሆነ ስሙ
ለአንድ ቡሃቃ ሊጥ
20 ሺ እያሰሙ
ከምር ወደየት ነው
ከየት ወየት መንገድ
(ከሰከሩም እንኳን)
አይቶ ገምቶ ነው
ኋላ መንገዳገድ
ወይ የሚያቅፉ መስሎ
ትከሻ መላመድ
ወይ እራስን መብላት
ከመሬት መዋደድ
የምን ቆሞ መሄድ
የምን ሄዶ መቆም
በራስ ቤት መታሰር
ቂም ይዞ እንደመፆም
ለመዋደድ ነቅቶ
በፍቅር ነው መሾም
እንዳሹት ከምታሽ
እንደ ደማከሴ
የት እንዳለሁ ሳላውቅ
አድር ይሆን ፈውሼ?
ያለት ስንጣሪ
ከምድር የቀረፀኝ
ቅምሻ ፍርፋሪ
ኮምጥጦ አገረሸኝ
አይኔን አስጨፈነኝ
ኸረ ከምር የት ነኝ?
ታውሮ ሚመራው
መንገዴን ነጠቀኝ
እኔጠፋሁ ልበል
ካለሁስ ወዴት ነኝ
አገር ማለት መሬት
አገር ማለት ምሬት
አገር ማለት እኔ
ተምታቶብኝ ድንገት
... ሆኜ ካለሁበት
ሰይፈ ተማም 2010
መሬት አይደል መነሻዬ
መሬት ያጣሁ መሬት ሁኜ
መነሳትን ተጠይፌ
የወደቅኩኝ ተንሳፍፌ
እኔም ራሴ መሬት
ለመብቀያ ያበቀለኝ
ከመሬት ነኝ?
ከምሬት ነኝ?
ከምር የት ነኝ?
ቁንጥር አፈር ዘግኖ በእጁ ካበጃጀኝ
ቁንጽል አንቀጽ ጠቅሶ በእጁ 'ሚያስፈጀኝ
መሆኔ አይደለም ወይ ከመሬትም መሬት
ሲረማመዱብኝ እንቁዬን ደብቄ በቀን እኩለ ሌት
ሲዘንብ እምቦካ የቋጠርኩኝ አለት
ሲያርሱ 'ምበረበር
ሲበትኑ 'ምዘር
የማያዳብረኝ የሰጡኝ ምርጥ ዘር
አለቴን ገድዬ 'ማረገው አፈር
ጨረቃን ጋርጄ ፀሃይ የምሰፍር
ፀሃይ በዛ ብዬ ደሞ ምንጨረጨር
ህዋ ላይ ተጥዬ የማርፍበት የናፈቀኝ
አዎ መሬት ያጣሁ መሬት ነኝ
ቀማሽ ምላስ ሰጥቶ ጣ'ም 'ሚያስቆጥረኝ
ጣፋጭ ስኳር ነስቶ በጨዉ ሲያስመርረኝ
መሆኔ አይደለም ወይ ከምሬትም ምሬት
ወዳጄ ስሞታ ወዳጄ ጣ'ም ሃሞት
የማያጣኝ ከቤት
የማያጣኝ ከሬት
ብሶት የወለደው ብሶ ያንገሸገሸኝ
ጣ'ም ያጣሁ ምሬት ነኝ
አገር ማለት መሬት
አገር ማለት ምሬት
አገር ማለት እኔ
ተምታቶብኝ ድንገት
መሬት ምሬት ምርየት
መሬቱ ሰው አለው
አለው የሰው ኩሩ
'ራሱን እማይነጥል
ከዱሩ ከአፈሩ
ሲጠብቃት ኖሮ
ከሷው ነው አዳሩ
ይኸም ሰው ጨፍግጓል
መረሮታል ጠአሙ
መጣፈጥ ጠፍቶታል
መልኩም ሆነ ስሙ
ለአንድ ቡሃቃ ሊጥ
20 ሺ እያሰሙ
ከምር ወደየት ነው
ከየት ወየት መንገድ
(ከሰከሩም እንኳን)
አይቶ ገምቶ ነው
ኋላ መንገዳገድ
ወይ የሚያቅፉ መስሎ
ትከሻ መላመድ
ወይ እራስን መብላት
ከመሬት መዋደድ
የምን ቆሞ መሄድ
የምን ሄዶ መቆም
በራስ ቤት መታሰር
ቂም ይዞ እንደመፆም
ለመዋደድ ነቅቶ
በፍቅር ነው መሾም
እንዳሹት ከምታሽ
እንደ ደማከሴ
የት እንዳለሁ ሳላውቅ
አድር ይሆን ፈውሼ?
ያለት ስንጣሪ
ከምድር የቀረፀኝ
ቅምሻ ፍርፋሪ
ኮምጥጦ አገረሸኝ
አይኔን አስጨፈነኝ
ኸረ ከምር የት ነኝ?
ታውሮ ሚመራው
መንገዴን ነጠቀኝ
እኔጠፋሁ ልበል
ካለሁስ ወዴት ነኝ
አገር ማለት መሬት
አገር ማለት ምሬት
አገር ማለት እኔ
ተምታቶብኝ ድንገት
... ሆኜ ካለሁበት
ሰይፈ ተማም 2010
👍1