ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
የተማረኩ የደቡብ ወሎ ዞን ሰላም አስከባሪዎች እና ፓራ ኮማንዶዎች ወደ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር የተሀድሶ ማዕከል ገቢ ተደረጉ!!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ወግድ እና ከላላ ወረዳ ውስጥ ባለፉት ቀናት በሰራው ኦፕሬሽን በርካታ ጠላት የተደመሰሰ ሲሆን መንገድ መሪዎቹ የሆኑት የደቡብ ወሎ ዞን ሰላም አስከባሪዎች እና ፓራ ኮማንዶዎች ተማርከዋል:: ፋኖን እናጠፋለን ብለው ከጠላት አብረው ሌት ተቀን ንፁሀን ወገኖቻችንን ሲገድሉ እና ሲያስገድሉ ከርመው በስተመጨረሻ እጃችን ላይ ወድቀዋል:: እነዚህ የደቡብ ወሎ ዞን ሰላም አስከባሪዎች እና ፓራ ኮማንዶዎች አሁን ላይ የተሀድሶ ስልጠና እየተሰጣቸው ሲሆን በስልጠናው መሀል አስተያየታቸውን የለገሱት በጥቅሉ የተናገሩት እስካሁን በሄዱበት መንገድ እና በፈፀሙት ድርጊት እጅጉን እንደተፀፀቱ ነው::

ምርኮኞቹ በንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር የተሀድሶ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና እንዳጠናቀቁ ወደ ማህበረሰቡ ይመለሳሉ ተብሏል:: ፋሽስቱ አብይ አህመድ አማራን በአማራ ለማስመታት የሚያደርገው ጥረት አካል የሆነውን ፕሮጀክት ለማሳካት ደፋ ቀና የምትሉ የፀጥታ ኃይል አባላት በአስቸኳይ ከህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ ሲል ኮሩ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህን ጥሪ ባለመቀበል ከጠላት ጎን የተሰለፉት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል::


መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም
🙏2
ከደሴ በስተምዕራብ ወግድ ወረዳ ውስጥ ንፁሃን አማራዎች በፋሽስቱ አብይ ሰራዊት ተረሸኑ!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር የፋኖ ኃይል በሰነዘረበት ጥቃት ታህሳስ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በርካታ አባላቱን ያጣው የጠላት ኃይል አፀፋዊ ምላሽ በሚመስል መልኩ ንፁሐን ላይ አሰቃቂ እርምጃ ወስዷል::

በዚህ የጠላት የጭካኔ እርምጃ ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ወጣት አስማማዉ (ቀዮ) ተረሽኗል:: ወጣቱ ወግድ ከተማ ውስጥ አሳንቡሳ እና ቦንቦሊኖ በመጥበስ ይተዳደር የነበረ የሁለት ልጆች አባት ነው:: ለአስማማው እና መሰል ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ፈንታ መንግስት ተብየው አካል በየዕለቱ ነፍሳቸውን እየቀጠፈ ነው::

ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ወግዲ ከሀይስኩል አለፍ ብሎ የአምላኬ ካብ የተባለ ስፍራ ላይ አረቡ አህመድ የሚባል ወጣትን የብልጽግና ታጣቂዎች በግፍ እረሽነውታል:: ደረሳውን የረሸኑት የፋኖ መረጃ ነህ ብለው ነው::

ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም እሮቢቴ የሚባል አካባቢ የደቡብ ወሎ ዞን ፓራ ኮማንዶዎች ሌሊት 10 ሰአት ተነስቶ ከመካነሰላም ወደ ወግዲ ይጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ላይ ተኩስ ከፍተው እረዳቱን ሲገድሉት ሹፌሩ ከባድ ቁስለኛ ሆኗል::

ይህም ብቻ አይደለም ከወር በፊት አንድት ለወሊድ ወደ ጤና ተቋም በተሽከርካሪ እየተጓዘች የነበረች እናትን እረሽነዋል::

በወረዳው ውስጥ ሰኮሩ ቀጠና ሼህ ያሲን የተባሉ ታዋቂ የኃይማኖት አባት እና ሌሎች ደረሳዎች ከዚህ ቀደም በጠላት ተረሽነዋል:: በአበየ ጉርባ ቀጠናም በገዛዛ አቦ መውጫ በኩል አንድ ቄስ እና ሌሎች ንፁሓን በግፍ ተረሽነዋል::

በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት ወንጀል እየፈፀመ ያለው የአብይ አህመድ ፋሽስታዊ መንግሥት በየጊዜው የንፁሓንን ደም እያፈሰሰ መሆኑን አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጭምር ይገነዘብ ዘንድ በሚዲያ፣ ዲፕሎማሲ እና አድቮኬሲው ዘርፍ ሁሉም የአማራ ልጅ እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የሚችሉትን ያደርጉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም
💔1
"አንበሳ ምን ቢርበው ሳር አይግጥም!!"

የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራር የሆነው ሻለቃ ሀብታሙ ደምሴ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ያስተላለፈው መልዕክት!!

የአማራ ህዝብ ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋን ተከትሎ ለህዝባችን የደህንነት ዋስትና ለመሆን ዱር ቤቴ ብለን ጠብመንጃ አንስተን ወደ ጫካ እና በርሃ የገባነው ህዝብን የማዳን አላማን አንግበን መሆኑ ይታወቃል። በበኩላችን የምንሞትለትን አላማ ጠንቅቀን ስለምንረዳ ይህን አላማ ለማሳካት የሚያስችል ፅናት ተላብሰን ትግላችንን ቀጥለናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ቅርብ ወራጆች ደግሞ በየተራ ወደ ጠላት እየገቡ መሆናቸውን ታዝበናል።

ትግል ያለ አላማ እና ፅናት እንደማይሰምር ሁሉ፤ አላማ ቢስ የሆኑ ልፍስፍሶች ወደ ጠላት ሲገቡ ልንረዳው የሚገባ ነገር ቢኖር የትግሉ ሜዳ እየፀዳ መምጣቱን ነው። በትግሉ ሜዳ ላይ በፅናት መቆየት የሚችሉት አላማ ያላቸው ብቻ መሆናቸውን ልንገነዘብ ይገባል። አላማ ከሌላቸው ብዙኃን ይልቅ አላማ ያላቸው ጥቂቶች ለድል ይበቃሉ። የአማራ ህዝብ አሁን ላይ እየሆነ ባለው ነገር ሳይደናገር እና ሳይደናገጥ በእኛ በልጆቹ ሙሉ እምነት እንድኖረው የምናሳስበው የፀና ህዝብ አሸናፊ እንደሚሆን ስለምናውቅ ጭምር ነው። የትግሉ ሂደት መሰናክል የበዛበት መሆኑን አምነን መሰናክሎችን ሁሉ በፅናት ለማለፍ ቆርጠን እንደ ህዝብ መነሳት ይገባናል። ይህ ሊሆን የሚችለው ደግሞ አማራዊ አንድነታችንን ማንበር ስንችል እና የጋራ መግባባት ላይ ስንደርስ ነው።

ባቡሩ ሲጓዝ በየፌርማታው የሚወርዱ ተሳፋሪዎች እንደሚኖሩ ተገማች ነው። ይህን ትግል እንደ ባቡር ቆጥረነው በየፌርማታው የሚወርደው ተሳፋሪ ጉዳይ ሊያሳስበን እንደማይገባ ለማስታወስ እንወዳለን::

በጣም የሚገርመው ነገር ቢኖር ወደ ጠላት የሚገቡ አካላት ለክዳታቸው እንደ ሰበብ የሚቆጥሩት በዋናነት ጌቶቻቸው የሚሰጧቸውን አጀንዳ መሆኑ ነው። ስለዚህ እነሱ ከጅምሩ የጠላት እንጅ የእኛ አልነበሩም ማለት ነው። የጠላትን አጀንዳ ከጠብመንጃ ጋር ተሸክመው ላይ ታች ሲሉ የነበሩ ስለሆኑ እነሱ ቢመጡ ቢሄዱ ምንም ሊደንቀን ሊጨንቀንም አይገባም።

ጥርሳችንን ነክሰን በመታገል የሚከፈለውን መስዋዕትነት እየከፈልን ለአማራ ህዝብ የደህንነት ዋስትናዎች ለመሆን እና ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለመታደግ ቆርጠን የተነሳን በመሆናችን እስከመጨረሻዋ የድል ብስራት ከአላማችን ዝንፍ እንደማንል እያረጋገጥኩኝ "አንበሳ ምን ቢርበው ሳር አይግጥም!!" እንድሉ አበው እኛም ምንም አይነት አጀንዳ ቢወረወር ከጠላት ጎን ልንሰለፍ እንደማንችል እሙን ነው።

ሻለቃ ሀብታሙ ደምሴ
የአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራር

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም
3🙏2
ሰበር ዜና!

ተጠናክሮ በቀጠለው ተጋድሎ ዋግሹም ብርጌድ 46 የአገዛዙን ፖሊስና ሚሊሻ በመደምሰስና 58 የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የላስታ ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ ኮር አካል የሆነው ዋግሹም ብርጌድ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ድሃና ወረዳ 010 ቀበሌ አባም አቦ ቀጠና ጥር 03/2018 ዓ/ም ከጧቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት ባደረጉት ከባድ ትንቅንቅ የብልፅግና ዙፋን አስጠባቂ የሆኑትን የድሃና ወረዳ ፖሊስና ሚሊሻ አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ታላቅ ጀብዱ ፈፅመዋል።

መነሻውን ከድሃና ወረዳ አምደወርቅ ከተማ ወደ 010 ቀበሌ አባም አቦ ቀጠና በመንቀሳቀስ ዋግሹም ብርጌድ ፋኖዎችን አፍናለሁ በሚል የተንቀሳቀሰው የወረዳው ፖሊስና ሚሊሻ አባላት መረጃው ቀድሞ የደረሰው የብርጌዱ ወታደራዊ መረጃ ክፍል ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ሊያፍን የመጣውን የጠላት ኃይል በተቃራኒው ከበባ ውስጥ በማስገባት አንድም ኃይል ሳይቀር እንዲደመሰስ፣እንዲቆስልና እንዲማረክ ተደርጓል።

በዚህ አውደ ውጊያ 46ቱ ሲደመሰስ፣29ኙን በማቁሰል ሁለት አመራሮችን ጨምሮ 24ቱ ሊማረኩ ችለዋል። በተያያዘም 32 ክላሽንኮፍና 16 የቃታ መሳሪያ በድምሩ 48 የነፍስ ወከፍ መሳሪያ፣2860 ተተኳሽ፣56 የወገብ ትጥቅ ተማርኳል። ከምርኮኞቹ መካከልም የድሃና ወረዳ ፖሊስ ምርመራ ሂደት ኃላፊ ኢንስፔክተር ሸጋ አያናውና የድሃና ወረዳ ሚሊሻ ፅህፈት ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ምስጋናው ይገኙበታል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መምህር ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 4/2018 ዓ.ም
4🙏1
ሰበር ዜና

ከ5 በላይ አጎራባች የወረዳ ህዝብ በሚሳተፍበት የወልድያ ከተማ ታላቅ የገበያ ቀን የአገዛዙ ሃይል የከባድ መሳሪያ ድብደባ እየፈፀመ ነው::

በዛሬው እለተ ማክሰኞ በወልድያ ከተማ የገበያ ቀን ቢሆንም ከኢንዱስትሪ መንደር/ማር ማቀነባበሪያው ከማለዳው ጀምሮ ከባድ መሳሪያ በመተኮስ ከጉባላፍቶ እና ራያ ቆቦ ወረዳ የውርድንብር ድብደባ እየፈፀመ ነው::

የፈሪ ነገር ሆኖበት የፋኖን ጦር ፊትለፊት መጋፈጥ ሲያቅተው በሩቁ በሚያስወነጭፈው የከባድ መሳሪያ ቅንቡላ ንፁሃን ላይ ሰባዊና ቁሳዊ ጉዳት እያደረሰ ነው::

ዝርዝር መረጃ ከእዙ እንደደረሰን የምናደርሳችሁ ይሆናል::
💔1
ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ዛሬ ጥር 5/2018 ዓ.ም ደቡብ ወሎ ዞን ውጫሌ ከተማ ደረሳዎችን ጨምሮ ወጣቶችን በሃይል እያፈሰ ወደ ጦር ማሰልጠኛ እያጋዘ ይገኛል::

ተከታዩ ቪዲዮ በዉጫሌ ንፁሃንን በተለይ ደግሞ 'የሙስሊሙን ማህበረሰብ ፋኖ ጠል ነው' የሚል ስሁት ትርክቱን ለማሳየት በመምረጥ ወደማሰልጠኛ እየወሰዷቸው ነው:: የፍኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው የ እምነት ልዩነትን በማስፋት ግጭት ለመቀስቀስ እየጣረ የሚገኘው ስርአቱ የመዘዘው የመጨረሻ ካርዱ ቀድሞ የተነቃበት በመሆኑ ችግሩ አልተፈጠረም::

በተለይ የ እምነት ልዩነት ውበት እንጅ ችግር ያልሆነበት የወሎ ማህበረሰብ አገዛዙ እየሄደበት ያለውን የግጭት ቅስቀሳ አጀንዳ እየተጠየፈ ከህልውና ትግሉ ጎን እየቆመ ነው::
💔1
ከእያንዳንዱ ሚዲያዎች በስተጀርባ ረጃጅም የሴራ ፖለቲካ እጆች እንዳሉ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን...?

አሁን ላይ የአማራ ፋኖን ትግል ደጋፊ፣ዘጋቢና አጋዥ መስለው የተቋቋሙ ሚዲያዎች መስራቾቻቸውን፣የቦርድ አባሎቻቸውንና ስራ አስኪያጆቻቸውን ታውቋቸው ይሁን? በዋናነት የሳተላይትና ዩ ቱብ ቤዝድ (satellite&youtube based) ሚዲያዎች፣አልፎ አልፎ ከማኀበራዊ ትስስር አውታሮች ደግሞ ፌስቡክና ቲክታክ (facebook& tiktok) ላይ ውለው የሚያድሩትን ግለሰቦችና ቡድኖች ከጀርባ ያላቸውን ፍላጎት የአማራ ህዝብ ይረዳው ይሆን?

በተለይ በአማራ ህዝብ የሕልውና ትግል ስም የሳተላይትና ዩቱብ ሚዲያ ከፍተው እርስ በእርስ ሲያጋድሉ የሚውሉትን የሚዲያ ባለቤቶች፣የቦርድ አባላት፣ዋናና ምክትል ስራ አስኪያጆች ማንነት፣ምንነት፣ፖለቲካዊ ፍላጎት፣የት አገራት እንደሚኖሩ፣የቤተሰብ ሁናቴ፣የግል ስራ፣ሐይማኖት፣ለአገዛዙ ያላቸው አጠቃላይ ሁኔታ፣የፋኖን ትግል የሚያዩበት መነፀር፣ የግል ስብዕናቸውና የጀርባ ታሪካቸው ወዘተ... ይታዎቅ ይሁን?? አይመስለኝም።

ምድር ላይ የሚታገሉ ሃቀኛ የፋኖ አመራሮችን፣ፋኖዎችን፣ ትግሉን የሚያግዙ አካላትን፣ተቋማትን፣ድርጅቶችንና በአጠቃላይ የትግሉ አስኳል የሆኑ አካላትን መሬት ላይ በስመ ፋኖ አገዛዙ ካሰማሯቸው የይስሙላ ታጣቂዎችና የፋኖ አመራሮች "ነን" ባዮች ጋራ ተናበው እንዴት እንደሚያጠቁ ተገልጦላችሁ ይሆን??

ከአንድ ዓመት ተኩል ቀደም ብሎ በቀድሞ አጠራሩ የ "አማራ ፋኖ በጎጃም" (አፋጎ) ከእኔ ጋራ ግጭት ውስጥ እንዲገባ፣ አስቀድመው፣ በእኔ ላይ ከፍተኛ የጥላቻ ቅስቀሳ፣በሬ ወለድ ስም ማጥፋት(defamation)፣ የስብዕና ግድያ (character assassination)፣መልካም ስምና ዝናዬን (Good name and reputation) በማጥፋት በገዛ ጦራችን ከበባ እንዲፈፀምብን ከፍ ሲል ደግሞ የህይወት መሰዋዕትነት በማስከፈል ጎጃም ላይ ታሪካዊ ስህተት እንዲሰራ ሲቀሰቀሱ የነበሩ ሚዲያዎችና ቧልተኞቻቸው ዛሬ ላይ የት እንዳሉ ታውቁ ይሆን?እነ ማ እንደሆኑ ልብ ብላችሁ ይሆን?

ያኔ በእኛ ላይ ከውስጥም ከውጭም ሲዘምቱ የነበሩት ራሳቸውን ፍፁም የትግሉ አራማጅ፣ተቆርቋሪ፣አዳኝ፣መሪና አለኝታ አስመስለው ነበረ። በአንፃሩ እኛን ደግሞ የትግሉ ስጋቶች አድርገው በመቀስቀስ እንድንወገር ሲያቧልቱ ነበረ። በጣም አስቂኙ ጉዳይ ግን እነዚህ በውስጥም በውጭም በሚዲያ፣ በጋዜጠኛ፣በቃል አቀባይና በፖለቲከኛ ስም በእኛ ላይ በሀሰት ሲዘምቱ የነበሩት አገዛዙን በዋናነት የብአዴንን መዋቅር አንገት ለአንገት ተናንቀን ካፈረስነው በኋላ እጃቸውን እየጎተትን ከባርነትም ከፍራቻም ነፃ ያወጣናቸው አንጊዎች መሆናቸው ነው።ዛሬ ደግሞ መፅናት አቅቷቸው እየተንጠባጠቡ ወትሮም ከባርነት ተጎትተው ወደ ወጡበት ስፍራ እየተመለሱ ነው።  በዚህ አጋጣሚ እጅግ በጣም ጥቂት በሐቅ የሚታገሉና የሚያታግሉ ሚዲያዎችና በለሙያዎቻቸውን አልዘነጋንም።

ለማንኛውም እኛ ሐቀኞች ከነ ሐቃችን እስከ ቀራኒዮ የሕልውና አደጋ ውስጥ ለገባው ህዝባችን ያለማዎላዎል ፀንተን እንታገላለን።

በጋዜጠኛ፣በፋኖ፣በአርበኛ፣በካፒቴን ..ወዘተ...ስሞች እየዘለሉ ለአገዛዙ ቢገብሩ እንዳይደንቃችሁ። የፀኑ፣የሚፀኑና የሚያፀኑ ዝም ያሉ ጀግና ታጋይ ልጆች ስላሏችሁ።

በቀጣይ የሚዲያና የጋዜጠኛ ሚና በትግሉ ምን መሆን አለበት? ምንድን ነውስ? ዛሬ ላይ እዚህም አዛም የምናያቸው ጋዜጠኞች ወይስ ደላሎች የሚሉትን እናነሳለን።

እንፅና!!!

@ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናው - የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ የሚድያ እና ዝግጅት መምሪያ ኃላፊ
3
የምኒልክ ዕዝን ክንድ መቋቋም ያቃተው ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ከተግባር ይልቅ "ውሸት"ን ትልቅ የአውደ ውጊያ ግንባር ካደረገው አመታቶች የተቆጠሩ ሲሆን ዛሬም አጠናክሮ ቀጥሎበት በምታዩት መልኩ በአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ስም የሃሰት መግለጫ እያወጣ ይገኛል::

እኛም እንላለን እናንተም በውሸታችሁ ቀጥሉ እኛም በሐቀኛ ተግባራችን! በያዝናቸው አመርቂ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ድሎቻችን ታጅበን ለመጨረሻው ግብ ድልና ነፃነታችን እየታገልን እንገኛለን::

ግፈኞች ሆይ ጦራችሁም ወሬያችሁም አይፈታንም:: አላማችንን ላፍታም ቢሆን አያደናቅፈውም!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 5/2018 ዓ.ም