ከፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ራሳቸውን ነፃ አውጥተው ፋኖን የሚቀላቀሉ የፋሽስቱ ሰራዊቶች ቁጥር በእጥፍ እየጨመረ ነው።
ከፋሽስቱ ሰራዊት እየፈረሱ ፋኖን የሚቀላቀሉ ሰራዊቶች የ12ኛ እና የ93ኛ ክፍለ ጦር የሆኑት ሰራዊቶች የብልፅግናን ጭቆና ከትከሻቸው ላይ አራግፈው በመጣል ወደ አማራ ፋኖ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮርን የሚቀላቀሉ የፋሽስቱ ሰራዊቶች ከቀን ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ መጥቷል። በጥቅምት ወራት የመባቻ ማግስት እስከ ህዳር አራት የፋሽስቱን ስርዓት እየከዱ የደጀን ክፍለጦርን የተቀላቀሉ ሀይሎች ስድስት ደርሰዋል። ራሳቸውን ከሞትና ከጥፋት በመታደግ የፋሽስቱን ስርዓት አገልጋይነትን በመጠየፍ የብልፅግናን ቤት ንቀው ወደ ህዝብ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
የስርዓቱን አስከፊነትና ጨፍጫፊነት የመሰከሩ ሲሆን" ከአሁን በኋላ የፋሽስቱን ወበር ለማስጠበቅ የሜንገብረው የህይዎት ዋጋ የለም።" ሲሉ ገልፀዋል። አስቀጥለውም በፋሽስቱ ስርዓት ውስጥ ተጨቁነውና ተደፍጥጠው ያሉ ወታደሮች ባገኙት አጋጣሚ ፋኖን ይቀላቀሉ እራሳቸውን ነፃ ያውጡ" ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 4/2018 ዓ.ም
ከፋሽስቱ ሰራዊት እየፈረሱ ፋኖን የሚቀላቀሉ ሰራዊቶች የ12ኛ እና የ93ኛ ክፍለ ጦር የሆኑት ሰራዊቶች የብልፅግናን ጭቆና ከትከሻቸው ላይ አራግፈው በመጣል ወደ አማራ ፋኖ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮርን የሚቀላቀሉ የፋሽስቱ ሰራዊቶች ከቀን ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ መጥቷል። በጥቅምት ወራት የመባቻ ማግስት እስከ ህዳር አራት የፋሽስቱን ስርዓት እየከዱ የደጀን ክፍለጦርን የተቀላቀሉ ሀይሎች ስድስት ደርሰዋል። ራሳቸውን ከሞትና ከጥፋት በመታደግ የፋሽስቱን ስርዓት አገልጋይነትን በመጠየፍ የብልፅግናን ቤት ንቀው ወደ ህዝብ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
የስርዓቱን አስከፊነትና ጨፍጫፊነት የመሰከሩ ሲሆን" ከአሁን በኋላ የፋሽስቱን ወበር ለማስጠበቅ የሜንገብረው የህይዎት ዋጋ የለም።" ሲሉ ገልፀዋል። አስቀጥለውም በፋሽስቱ ስርዓት ውስጥ ተጨቁነውና ተደፍጥጠው ያሉ ወታደሮች ባገኙት አጋጣሚ ፋኖን ይቀላቀሉ እራሳቸውን ነፃ ያውጡ" ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 4/2018 ዓ.ም
❤2👍1
🔶 ዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር አርሴማ ላይ በጠላት ኃይል ላይ ጥቃት ፈጸመ።
በትላንትናው እለት ህዳር 4/2018 ዓ.ም ዳግማዊ ቴዎድሮስ፭ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ቃኘው ብርጌድ ፤ ታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ጅብ አስራ ማርያም ብርጌድ እና ጥቁር አንበሳ ክ/ጦር ቃኘው ሻለቃ በመቀናጀት ምንዝሮ ልዩ ስሙ አርሴማ ከተባለው ቦታ ላይ በብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ላይ ጥቃት አድርሰዋል።
በጥቃቱ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የገባው ሰራዊቱ ቁስለኛውንና አስከሬኑን በመተው ወደ ጠዳ ከተማ ፈርጥጦ ገብቷል።
በዚህም የተነሳ ቁስለኛውንና አስከሬኑን ለማንሳት ተጨማሪ የጠላት ኃይል ከጠዳ ከተማ ተነስቶ ውጊያው ከተካሄደበት ቦታ በመድረስ በወገን ሃይል ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ነበልባሎቹ ፋኖዎች የለመደውን የሽንፈት ካባ አከናንበውታል።
በውጊያው ከተገኙ ድሎች መካከል
** 06 የሞተ
** 08 ክፋኛ የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን።
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ
ህዳር 05/2018 ዓ.ም
በትላንትናው እለት ህዳር 4/2018 ዓ.ም ዳግማዊ ቴዎድሮስ፭ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ቃኘው ብርጌድ ፤ ታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ጅብ አስራ ማርያም ብርጌድ እና ጥቁር አንበሳ ክ/ጦር ቃኘው ሻለቃ በመቀናጀት ምንዝሮ ልዩ ስሙ አርሴማ ከተባለው ቦታ ላይ በብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ላይ ጥቃት አድርሰዋል።
በጥቃቱ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የገባው ሰራዊቱ ቁስለኛውንና አስከሬኑን በመተው ወደ ጠዳ ከተማ ፈርጥጦ ገብቷል።
በዚህም የተነሳ ቁስለኛውንና አስከሬኑን ለማንሳት ተጨማሪ የጠላት ኃይል ከጠዳ ከተማ ተነስቶ ውጊያው ከተካሄደበት ቦታ በመድረስ በወገን ሃይል ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ነበልባሎቹ ፋኖዎች የለመደውን የሽንፈት ካባ አከናንበውታል።
በውጊያው ከተገኙ ድሎች መካከል
** 06 የሞተ
** 08 ክፋኛ የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን።
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ
ህዳር 05/2018 ዓ.ም
❤2🙏1
እነሆ የዕድሜ ልክ የፅናት አባት አርበኛ መሳፍንት ተስፉን መልዕክት በወርድ ለፈለጋችሁ።
ከአርበኛ መሳፍንት የተላለፈ ወቅታዊ መልዕከት
**********
ህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም
የምወዳችሁ፣ የማከብራችሁ፣ እንድያ ህይወቴን ለመስጠት የተዘጋጀሁላችሁ የመኖሬ ሚስጥር የሆናችሁ የአማራ ህዝብ እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በሙሉ የከበረ ሰላምታዬ ይድረሳችሁ፡፡
ከእኔ አብራክ የተወለዱ ልጆቼ፣ የአማራ ህዝብ የመንፈስ ልጆች አርበኛ ጌትነት እና አርበኛ ገብረ መሰዋት የተሰማችሁ ሀዘን ከፍተኛ እንደሆነ በተለያየ መንገድ ደርሶኛል፡፡
በእርግጥ ሀዘኑን የጀግና አባት፤ ለሀገር የቆሙ እልፍ ጣይ አባት፣ ሁሌ በበርሀ እና ስደት ሆና ያሳደገ አባት ሆናችሁ ስታስቡት እጅግ መሪር ነው፤ ግን ደሞ ጣፋጭ መሪር ነው:: ሁኔታውን መሪሪ የሚያደርገው ስለማራነት እና ለሐገር በሚደረግ የህይወት መሰዋዕትነት ውስጥ ከአብራክህ የወጡ ጀግና ልጆችህን በእርጅና ዘመንህ እያጣህ ስትሄድ ነው፡፡ ይህ እራስን ለትግል አቅርቦ እንደመሰዋት አይደለም ይህ በጦር ሜዳ ተፋልሞ እንደ መቁሰል አይደለም፤ ይህ መሸነፍ እና እንደ ማሸነፍ አይደለም እጅግ ጥልቅ ጀግንነት የሚጠይቅ እንጂ፡፡ ሆኖም ግን እኔ አባታችሁ ይህን መሪር ሀቅ ወደ ጣፋጨነት የምቀደረው ከአባቶቼ በወረስኩት ለህዝብ ለነፃነት፤ ለእምነት፣ ለሀገር መኖር እጅግ በጣም ጥልቅ ጀግንነት እና ቆራጥነት የሚጠይቅ መሰዋዕትነት እንደሆነ ስለማምን ነው።
የተከበራችሁ ወገኖቼ ሀዘን ገብቶታል ብላችሁ እንዳታስቡ ምክንያቱም በልጆቼ መሰዋት ውስጥ፣ ሁሌ የሚታዩኝ የአማራን ህዝብ ወደ ክብሩ ሲመለስ ነው፣ ሀገሬ ኢትዮጵያ ከባንዳዎች እጅ ወጥታ የቀደመው ክብሯ ተመልሶ በአለም ፊት ከፍ ብላ መታየቷ ነው፣ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚያምነው እምነቱ በነፃነት አምልኮ የሚመኛትን መንግስተ ሰማያታት እወርሳለሁ ብሎ በሙልዑነት በሀገሩ ሲኖር ማየት ነው።
በአሁኑ ሰዓት ለአማራ ህዝብ እና ለሀገር የሚደረግ መሰዋዕትነት ተራ መሰዋዕትነት አይደለም ሰው በጠፋበት ዘመን ፤ እናቶች በሚቃትቱበት ዘመን፤ ሴት ልጆች ድረሱልኝ በሚሉበት ዘመን፤ አዛውንት የሚያደርጉት አጥተው በሚያስቅሱበት ዘመን፤ ክርስቲያኖች ሰው አውጣልን እያሉ በሚማፀኑበት ዘመን የሚከፈል እንቁ መሰዋዕትነት ነው፡፡ መለኪያም የለውም፡
የምወዳችሁ የአማራ ህዝብ ሆይ በልጆቼ መቃብር ላይ ቆሜ ይህንን የአባትነት ጥሪ እና መልዕክት እንድትቀበሉኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡
1. በትንንሽ እውነቶች ትልልቅ እውነቶችን አትሽጡ ወይም አትግደሉ ፡- ይህ ማለት- ማንኛውም ሰው የሚያነሳው እውነት ይኖረዋል፤ ለምሳሴ እራስን መለወጥ፣ ለቤተሰብ ቋሚ ገቢ እንዲኖር ማድረግ፣ የግል ክብሩን መጠበቅ፣ የራሱን የትግል ስልት መቀየስ፣ የሚባሉ እውነቶች አሉት። መገንዘብ የሚገባን ግን እነዚህ እውነቶች የሚኖሩነት ሀገር እና ህዝብ ሲኖር ብቻ ነው፡፡ ስለሀገር፣ ስለህዝብ፤ ስለ እምነት መኖር ከላይ ከተቀመጡት እውነቶች ጋር ሲነፃፀር ትንንሽ እውነት ናቸው፡፡ አሁን እየሆነ ያለው ግን በእነዚህ ትንንሽ አውነተሰ ትልልቅ እውነትን መግደል ነው፡፡ ይህ የአማራንት መገለጫ አይደለም:: የአባቶቻንም አደራ እንዲህ እንደ እንሰሳ እንድንኖር አይደለም:: ልጄ ጌትነት የተሰዋው እሱ ለትልቁ እውነት ሲኖር ለትንንሽ ነገር የሚኖሩ የባንዳዎች አስተሳሰብ ውጤት ነው::
2. የአማራ ህዝብ መዳኛ የሆነውን ትጥቃችሁን (አንድነትን) በወሬ፤ በሴረኛ፤ በስሜታዊነት፤ ባለማወቅ፤ በስርዐት አልበኝነት እና በራስ ወዳድነት አትናዱት፦ አማራ ትልቅ ህዝብ ነው። ትልቅነቱ የመነጨው በአማኝነቱ በታማኝነቱ ነገርን ከስሩ በማየቱ/ማስተዋሉ/፤ በማገናዘቡ እና ትልቁን እውነት ይዞ በአንድነት ጥላትን በማሸነፉ እንጂ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ብቻ አይደለም፡፡
3. የተግባር ሰው ሁኑ፤ በጣም ቀላሉን መንገድ አትምረጡ - በጣም ቀላሉ መንገድ መናገር እና መተቸት ነው፡፡ ይህ ለአማራነት አይመጥንም። አማራነት ለሚያውቁት እውነት “በመመነን" ወይም በመኖር ነው የሚገለፀው፡፡ የወንድምህን ሌብነት ጨዋ በመሆን አሳየው፣ እንዳይሰርቅ ሥርዐት በመዘርጋት አግዘው፣ በመምከር አስተምረው እንጂ እንደ ሰይጣን ቆሻሻ ቃላቶችን በመጠቀም አይሁን፡፡ ተግባርህ እንጂ ስድብህ እንዳላስተማረ አይተኸዋል፡፡
4. የተሰዉ ልጆቼን፣ በዱር በገድል ስለእናንተ የተሰዉ እህት ወንድሞቻችሁን እና በትግል ላይ ያሉ አርበኞችን የምትወዷቸው ከሆን የሚከተሉት ጥያቄዎችን በውስጣቸሁ ሁል ጊዜ አንሱ፡፡
የእኔ ልጅ ጌትነትና ሌሎች ፋኖዎች ስለወገናቸው ቃል እንደገቡት እናንተ የሚጨፈጨፈው አማራ እንዲድን ምን ቃል ገባችሁ?
የእኔ ልጅ ጌትነት እና ስለ አማራ የተሰዉ ፋኖዎች የገቡትን ቃል በማክበር አንድኛ ሂወታቸውን እንደሰጡ እናንተስ ምናችሁን መሰዋዕት አደረጋችሁ?
ወንድሞቻችሁ በየበረሀው እየተሰዉ እኛ አንድ ሆነን እንዳንታገል የሚያደርገን ሀደል ከአማራ ህዝብ በልጦ ነው? አማራ ችግር የመፍታት ጥበብ አጥቶ ነው? አማሪ በድርጅት እና በአሰራር ሥርአት ብቻ ማሸነፍ እንደሚችል ጠፍቶት ነው? ወይስ በሴት ልጆቹ ጡት መቆረጥ ተደስቶ ነው? እነዚህን ጥያቄዎች መልሳችሁ አንድ ሀየሰል የገነባችሁ እለት የልጆቼን ደም እንደመለሳችሁልኝ አቆጥረዋለሁ።
የተከበራችሁ ወገኖቼ እኔ እድሜ ልኬን ስታገል ኖሬ የቀረኝ እድሜ አጭር ነው። በህይወት እስካለሁ ድረስ ለህዝቤ እራሴን መሰዋዕት አድርጌ አቀርባለሁ። ለመላው አማራ እና ኢትዮጵያውያን የማስተላልፈው ትልቅ መልዕክት ይህ በፈጣሪ አምሳል የተፈጠረን ሰው እየነቀሰ ሰው የሚተከል፣ እምነት የሌለው፣ ሀገር የሚጠላ፤ የሰው ህመም የማያመው፣ በሰው ልጅ ሞት የሚሳለቅ፣ ገድሎ በእሬሳ ላይ የሚቀልድ ስርአት እስካልተወገደ ድረስ የቅደም ተከተል ጉዳይ እንጂ ማንም እንደማይተርፍ ላረጋገጥላችሁ እወዳለሁ::
በመሆኑም የአማራ ልጆች የሆናችሁ እና ለገል ጥቅማችሁ ስትሉ ከመንግስት ጋር ሆናችሁ ወገናችሁን የምትገድሉ አማሮች ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢል አማራ ማሸነፉ ስለማይቀር፤ የእኛ ህይወት ህያው ሆና በወርቅ መዝገብ ሲመዘገብ እናንተ በምትሞቱለት ጥላታችሁ ተገድላችሁ የውሻ ሞት ሞታችሁ ልጆቻችሁም የባንዳ ልጆች ተብለው ሲወገዙ እንዳይኖሩ ከወንድሞቻችሁ ጋር ይቅር ተባባሉ እና በአንድ ተሰለፉ። የውስጥ ባንዳዎች መርሳት የሌለባችሁ ጀግናን ስትሰዉ ህያው ታደርጉታላችሁ እንጂ አትገድሉትም፣ ይልቁንም እናንተ የውሻ ሞት ስለምትሞቱ ጀግናን ጠብቁትና እራሳችሁን ከአደጋ ጠብቁ:
በመጨረሻን የአማራ ብርቅዬ ልጆች የሆናችሁ ነፍጥ አንስታችሁ በተለያዩ መስመር የምትታገሉ ፋኖዎች የአማራ ህዝብ እጣ ፈንታ በእጃችሁ ነው። የአማራ ህዝብ ከጎናችሁ በመሆን አለምን ያስደመመ ንቅናቄ ከተደረገበት ከሁለት አመታት በኋላ ያለው የአማራ ስቃይ የታሪካችሁ አካል ነው የሚሆነው:: አደናቅፎ የጣላችሁን መንገድ አትከተሉ። ስለሆነም በአጭር ጊዜ ውስጥ አንድ ሆናችሁ እንድትታገሉ በተሰዉት ሁለት ልጆቼ ለአማራ ሲሉ በተሰዉ መላው የአማራ ፋኖ ታጋዮች እና በመላው የአማራ ሥም ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡
አርበኛ መሣፍንት ተስፉ
ከአርበኛ መሳፍንት የተላለፈ ወቅታዊ መልዕከት
**********
ህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም
የምወዳችሁ፣ የማከብራችሁ፣ እንድያ ህይወቴን ለመስጠት የተዘጋጀሁላችሁ የመኖሬ ሚስጥር የሆናችሁ የአማራ ህዝብ እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በሙሉ የከበረ ሰላምታዬ ይድረሳችሁ፡፡
ከእኔ አብራክ የተወለዱ ልጆቼ፣ የአማራ ህዝብ የመንፈስ ልጆች አርበኛ ጌትነት እና አርበኛ ገብረ መሰዋት የተሰማችሁ ሀዘን ከፍተኛ እንደሆነ በተለያየ መንገድ ደርሶኛል፡፡
በእርግጥ ሀዘኑን የጀግና አባት፤ ለሀገር የቆሙ እልፍ ጣይ አባት፣ ሁሌ በበርሀ እና ስደት ሆና ያሳደገ አባት ሆናችሁ ስታስቡት እጅግ መሪር ነው፤ ግን ደሞ ጣፋጭ መሪር ነው:: ሁኔታውን መሪሪ የሚያደርገው ስለማራነት እና ለሐገር በሚደረግ የህይወት መሰዋዕትነት ውስጥ ከአብራክህ የወጡ ጀግና ልጆችህን በእርጅና ዘመንህ እያጣህ ስትሄድ ነው፡፡ ይህ እራስን ለትግል አቅርቦ እንደመሰዋት አይደለም ይህ በጦር ሜዳ ተፋልሞ እንደ መቁሰል አይደለም፤ ይህ መሸነፍ እና እንደ ማሸነፍ አይደለም እጅግ ጥልቅ ጀግንነት የሚጠይቅ እንጂ፡፡ ሆኖም ግን እኔ አባታችሁ ይህን መሪር ሀቅ ወደ ጣፋጨነት የምቀደረው ከአባቶቼ በወረስኩት ለህዝብ ለነፃነት፤ ለእምነት፣ ለሀገር መኖር እጅግ በጣም ጥልቅ ጀግንነት እና ቆራጥነት የሚጠይቅ መሰዋዕትነት እንደሆነ ስለማምን ነው።
የተከበራችሁ ወገኖቼ ሀዘን ገብቶታል ብላችሁ እንዳታስቡ ምክንያቱም በልጆቼ መሰዋት ውስጥ፣ ሁሌ የሚታዩኝ የአማራን ህዝብ ወደ ክብሩ ሲመለስ ነው፣ ሀገሬ ኢትዮጵያ ከባንዳዎች እጅ ወጥታ የቀደመው ክብሯ ተመልሶ በአለም ፊት ከፍ ብላ መታየቷ ነው፣ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚያምነው እምነቱ በነፃነት አምልኮ የሚመኛትን መንግስተ ሰማያታት እወርሳለሁ ብሎ በሙልዑነት በሀገሩ ሲኖር ማየት ነው።
በአሁኑ ሰዓት ለአማራ ህዝብ እና ለሀገር የሚደረግ መሰዋዕትነት ተራ መሰዋዕትነት አይደለም ሰው በጠፋበት ዘመን ፤ እናቶች በሚቃትቱበት ዘመን፤ ሴት ልጆች ድረሱልኝ በሚሉበት ዘመን፤ አዛውንት የሚያደርጉት አጥተው በሚያስቅሱበት ዘመን፤ ክርስቲያኖች ሰው አውጣልን እያሉ በሚማፀኑበት ዘመን የሚከፈል እንቁ መሰዋዕትነት ነው፡፡ መለኪያም የለውም፡
የምወዳችሁ የአማራ ህዝብ ሆይ በልጆቼ መቃብር ላይ ቆሜ ይህንን የአባትነት ጥሪ እና መልዕክት እንድትቀበሉኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡
1. በትንንሽ እውነቶች ትልልቅ እውነቶችን አትሽጡ ወይም አትግደሉ ፡- ይህ ማለት- ማንኛውም ሰው የሚያነሳው እውነት ይኖረዋል፤ ለምሳሴ እራስን መለወጥ፣ ለቤተሰብ ቋሚ ገቢ እንዲኖር ማድረግ፣ የግል ክብሩን መጠበቅ፣ የራሱን የትግል ስልት መቀየስ፣ የሚባሉ እውነቶች አሉት። መገንዘብ የሚገባን ግን እነዚህ እውነቶች የሚኖሩነት ሀገር እና ህዝብ ሲኖር ብቻ ነው፡፡ ስለሀገር፣ ስለህዝብ፤ ስለ እምነት መኖር ከላይ ከተቀመጡት እውነቶች ጋር ሲነፃፀር ትንንሽ እውነት ናቸው፡፡ አሁን እየሆነ ያለው ግን በእነዚህ ትንንሽ አውነተሰ ትልልቅ እውነትን መግደል ነው፡፡ ይህ የአማራንት መገለጫ አይደለም:: የአባቶቻንም አደራ እንዲህ እንደ እንሰሳ እንድንኖር አይደለም:: ልጄ ጌትነት የተሰዋው እሱ ለትልቁ እውነት ሲኖር ለትንንሽ ነገር የሚኖሩ የባንዳዎች አስተሳሰብ ውጤት ነው::
2. የአማራ ህዝብ መዳኛ የሆነውን ትጥቃችሁን (አንድነትን) በወሬ፤ በሴረኛ፤ በስሜታዊነት፤ ባለማወቅ፤ በስርዐት አልበኝነት እና በራስ ወዳድነት አትናዱት፦ አማራ ትልቅ ህዝብ ነው። ትልቅነቱ የመነጨው በአማኝነቱ በታማኝነቱ ነገርን ከስሩ በማየቱ/ማስተዋሉ/፤ በማገናዘቡ እና ትልቁን እውነት ይዞ በአንድነት ጥላትን በማሸነፉ እንጂ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ብቻ አይደለም፡፡
3. የተግባር ሰው ሁኑ፤ በጣም ቀላሉን መንገድ አትምረጡ - በጣም ቀላሉ መንገድ መናገር እና መተቸት ነው፡፡ ይህ ለአማራነት አይመጥንም። አማራነት ለሚያውቁት እውነት “በመመነን" ወይም በመኖር ነው የሚገለፀው፡፡ የወንድምህን ሌብነት ጨዋ በመሆን አሳየው፣ እንዳይሰርቅ ሥርዐት በመዘርጋት አግዘው፣ በመምከር አስተምረው እንጂ እንደ ሰይጣን ቆሻሻ ቃላቶችን በመጠቀም አይሁን፡፡ ተግባርህ እንጂ ስድብህ እንዳላስተማረ አይተኸዋል፡፡
4. የተሰዉ ልጆቼን፣ በዱር በገድል ስለእናንተ የተሰዉ እህት ወንድሞቻችሁን እና በትግል ላይ ያሉ አርበኞችን የምትወዷቸው ከሆን የሚከተሉት ጥያቄዎችን በውስጣቸሁ ሁል ጊዜ አንሱ፡፡
የእኔ ልጅ ጌትነትና ሌሎች ፋኖዎች ስለወገናቸው ቃል እንደገቡት እናንተ የሚጨፈጨፈው አማራ እንዲድን ምን ቃል ገባችሁ?
የእኔ ልጅ ጌትነት እና ስለ አማራ የተሰዉ ፋኖዎች የገቡትን ቃል በማክበር አንድኛ ሂወታቸውን እንደሰጡ እናንተስ ምናችሁን መሰዋዕት አደረጋችሁ?
ወንድሞቻችሁ በየበረሀው እየተሰዉ እኛ አንድ ሆነን እንዳንታገል የሚያደርገን ሀደል ከአማራ ህዝብ በልጦ ነው? አማራ ችግር የመፍታት ጥበብ አጥቶ ነው? አማሪ በድርጅት እና በአሰራር ሥርአት ብቻ ማሸነፍ እንደሚችል ጠፍቶት ነው? ወይስ በሴት ልጆቹ ጡት መቆረጥ ተደስቶ ነው? እነዚህን ጥያቄዎች መልሳችሁ አንድ ሀየሰል የገነባችሁ እለት የልጆቼን ደም እንደመለሳችሁልኝ አቆጥረዋለሁ።
የተከበራችሁ ወገኖቼ እኔ እድሜ ልኬን ስታገል ኖሬ የቀረኝ እድሜ አጭር ነው። በህይወት እስካለሁ ድረስ ለህዝቤ እራሴን መሰዋዕት አድርጌ አቀርባለሁ። ለመላው አማራ እና ኢትዮጵያውያን የማስተላልፈው ትልቅ መልዕክት ይህ በፈጣሪ አምሳል የተፈጠረን ሰው እየነቀሰ ሰው የሚተከል፣ እምነት የሌለው፣ ሀገር የሚጠላ፤ የሰው ህመም የማያመው፣ በሰው ልጅ ሞት የሚሳለቅ፣ ገድሎ በእሬሳ ላይ የሚቀልድ ስርአት እስካልተወገደ ድረስ የቅደም ተከተል ጉዳይ እንጂ ማንም እንደማይተርፍ ላረጋገጥላችሁ እወዳለሁ::
በመሆኑም የአማራ ልጆች የሆናችሁ እና ለገል ጥቅማችሁ ስትሉ ከመንግስት ጋር ሆናችሁ ወገናችሁን የምትገድሉ አማሮች ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢል አማራ ማሸነፉ ስለማይቀር፤ የእኛ ህይወት ህያው ሆና በወርቅ መዝገብ ሲመዘገብ እናንተ በምትሞቱለት ጥላታችሁ ተገድላችሁ የውሻ ሞት ሞታችሁ ልጆቻችሁም የባንዳ ልጆች ተብለው ሲወገዙ እንዳይኖሩ ከወንድሞቻችሁ ጋር ይቅር ተባባሉ እና በአንድ ተሰለፉ። የውስጥ ባንዳዎች መርሳት የሌለባችሁ ጀግናን ስትሰዉ ህያው ታደርጉታላችሁ እንጂ አትገድሉትም፣ ይልቁንም እናንተ የውሻ ሞት ስለምትሞቱ ጀግናን ጠብቁትና እራሳችሁን ከአደጋ ጠብቁ:
በመጨረሻን የአማራ ብርቅዬ ልጆች የሆናችሁ ነፍጥ አንስታችሁ በተለያዩ መስመር የምትታገሉ ፋኖዎች የአማራ ህዝብ እጣ ፈንታ በእጃችሁ ነው። የአማራ ህዝብ ከጎናችሁ በመሆን አለምን ያስደመመ ንቅናቄ ከተደረገበት ከሁለት አመታት በኋላ ያለው የአማራ ስቃይ የታሪካችሁ አካል ነው የሚሆነው:: አደናቅፎ የጣላችሁን መንገድ አትከተሉ። ስለሆነም በአጭር ጊዜ ውስጥ አንድ ሆናችሁ እንድትታገሉ በተሰዉት ሁለት ልጆቼ ለአማራ ሲሉ በተሰዉ መላው የአማራ ፋኖ ታጋዮች እና በመላው የአማራ ሥም ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡
አርበኛ መሣፍንት ተስፉ
🙏3❤1
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር!
ሻለቃ መሪው በፋኖዎች በቁጥጥር ስር ዋለ!
ህዳር 05/2018ዓ.ም
በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር ተከዜ ክፍለ ጦር መረጃን በማነፍነፍ የ61ኛ ክፍለ ጦር የ2ኛ ሻለቃ ምክትል መሪ የሆነው መቶ አለቃ በእውቀቱ ምስጋናው ከድልብ ወደ ግዳን ወረዳ ሙጃ ማርያም ከተማ በሚወስደው መንገድ ዴንሳ ከተማ ላይ በተከዜ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ህዳር 04/2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል።
ይህ ግለሰብ ላስታ ወረዳ ኩልመስክ ከተማ ላይ ከዚህ በፊት ስምንት ንፁሃንን የረሸነና ያስረሸነ፣የብዙ ወጣቶችን አካል ያጎደለ፣የአባውራ ሴቶችን የደፈረ፣ህዝባዊ መድረክ ላይ በይፋ ኩልመስክ ከተማን ጥቁር አለብሳታለሁ እያለ ማህበረሰቡ ላይ ግልፅ የስነ ልቦና ጫና ያደርስ የነበረ፣ከነጋዴው ብሎም ከማህበረሰቡ ሙስና የሚቀበልና የግል ጥቅሙን የሚያግበሰብስና ፍፁም ስነ ምግባር የጎደለው ጥቁር አማራ ነበር።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተከዜ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፋኖ ኢንጅነር አማረ ካሳ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 05/ 2018 ዓ.ም
ሻለቃ መሪው በፋኖዎች በቁጥጥር ስር ዋለ!
ህዳር 05/2018ዓ.ም
በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር ተከዜ ክፍለ ጦር መረጃን በማነፍነፍ የ61ኛ ክፍለ ጦር የ2ኛ ሻለቃ ምክትል መሪ የሆነው መቶ አለቃ በእውቀቱ ምስጋናው ከድልብ ወደ ግዳን ወረዳ ሙጃ ማርያም ከተማ በሚወስደው መንገድ ዴንሳ ከተማ ላይ በተከዜ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ህዳር 04/2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል።
ይህ ግለሰብ ላስታ ወረዳ ኩልመስክ ከተማ ላይ ከዚህ በፊት ስምንት ንፁሃንን የረሸነና ያስረሸነ፣የብዙ ወጣቶችን አካል ያጎደለ፣የአባውራ ሴቶችን የደፈረ፣ህዝባዊ መድረክ ላይ በይፋ ኩልመስክ ከተማን ጥቁር አለብሳታለሁ እያለ ማህበረሰቡ ላይ ግልፅ የስነ ልቦና ጫና ያደርስ የነበረ፣ከነጋዴው ብሎም ከማህበረሰቡ ሙስና የሚቀበልና የግል ጥቅሙን የሚያግበሰብስና ፍፁም ስነ ምግባር የጎደለው ጥቁር አማራ ነበር።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተከዜ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፋኖ ኢንጅነር አማረ ካሳ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 05/ 2018 ዓ.ም
👍3
የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜደር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ድልን ተቀዳጀ።
በዛሬዉ እለት ህዳር 05/2018 ዓ.ም ሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክ/ጦር አርበኛ ገብረመስቀል ደርብ ብርጌድ ጋፋት ሻለቃ ኮከብ ሻለቃ እና ታቦር ሻለቃ በመቀናጀት ከደብረታቦር ወደ እብናት ሲጎዝ በነበረ የስርአቱን ቅጥረኛ ከ12፡00 ሰአት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6 ፡40 ሰአት ልዩ ቦታዉ ቡሮ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ ደፈጣ በመጣል የጠላት ሀይልን በሚገባ አስተናግደዉታል።
ከደብረታቦር 18 መኪና ጠላትና እሬሽን የጫነ ሲሆን ከእብናት የወረደው አመራር ከ10 መኪና በለይ ታጅቦ ሲመጣ አናብስቶቹ ምን ዉስጥ ገባዉ ብሎ ሲርበተበትና ነብሱን ለማትረፍ ሲፍጨረጨር ዉሏል።
በአዉደ ዉጊያዉም የተገኙ ድሎች፦ የሞተ 14 : ቁስለኛ ከ20 በላይ አድርጎ በሁለት መኪና ጭኖ ሙትና ቁስለኘውን ወደ ደብረታቦር ተመልሷል።
በዚህም የተነሳ ቁስለኛውንና አስከሬኑን ለማንሳት ተጨማሪ የጠላት ኃይል ከደብረታቦር ከተማ ተነስቶ ውጊያው ከተካሄደበት ቦታ በመድረስ በወገን ሃይል ላይ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ነበልባሎቹ ፋኖዎች የለመደውን የሽንፈት ካባ አከናንበዉታል ሲል የብርጌዱ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አርበኛ በላይነዉ ልብሱ ተናግራል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን።
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ
ህዳር 05/2018 ዓ.ም
በዛሬዉ እለት ህዳር 05/2018 ዓ.ም ሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክ/ጦር አርበኛ ገብረመስቀል ደርብ ብርጌድ ጋፋት ሻለቃ ኮከብ ሻለቃ እና ታቦር ሻለቃ በመቀናጀት ከደብረታቦር ወደ እብናት ሲጎዝ በነበረ የስርአቱን ቅጥረኛ ከ12፡00 ሰአት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6 ፡40 ሰአት ልዩ ቦታዉ ቡሮ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ ደፈጣ በመጣል የጠላት ሀይልን በሚገባ አስተናግደዉታል።
ከደብረታቦር 18 መኪና ጠላትና እሬሽን የጫነ ሲሆን ከእብናት የወረደው አመራር ከ10 መኪና በለይ ታጅቦ ሲመጣ አናብስቶቹ ምን ዉስጥ ገባዉ ብሎ ሲርበተበትና ነብሱን ለማትረፍ ሲፍጨረጨር ዉሏል።
በአዉደ ዉጊያዉም የተገኙ ድሎች፦ የሞተ 14 : ቁስለኛ ከ20 በላይ አድርጎ በሁለት መኪና ጭኖ ሙትና ቁስለኘውን ወደ ደብረታቦር ተመልሷል።
በዚህም የተነሳ ቁስለኛውንና አስከሬኑን ለማንሳት ተጨማሪ የጠላት ኃይል ከደብረታቦር ከተማ ተነስቶ ውጊያው ከተካሄደበት ቦታ በመድረስ በወገን ሃይል ላይ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ነበልባሎቹ ፋኖዎች የለመደውን የሽንፈት ካባ አከናንበዉታል ሲል የብርጌዱ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አርበኛ በላይነዉ ልብሱ ተናግራል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን።
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ
ህዳር 05/2018 ዓ.ም
👍3❤1🙏1
የአለም አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በአርሲ ስለተገደሉ አርቶዶክሳዊያን የተሰማውን ሀዘን ገልጧል፡፡
ንጹሐንን በጭካኔ የሚገድሉትን አውግዞ ገዳዮችን ወደ ፍትሕ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍ የገለፀው ካውንስሉ
ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስም የሐዘን ደብዳቤም መጻፉ ታውቋል፡፡
(አውሎግሶን አንድነት ፣ ሕዳር 4/2018)
ንጹሐንን በጭካኔ የሚገድሉትን አውግዞ ገዳዮችን ወደ ፍትሕ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍ የገለፀው ካውንስሉ
ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስም የሐዘን ደብዳቤም መጻፉ ታውቋል፡፡
(አውሎግሶን አንድነት ፣ ሕዳር 4/2018)
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር!
የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት ንፁሃንና እንስሳትን በከባድ መሳሪያ ጨፈጨፈ !
ህዳር 05/2018ዓ.ም
የአገዛዙ ብልፅግና ወንበር አስጠባቂ ጨፍጫፊ ሰራዊት በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ 04 ቀበሌ ሳርዝና ልዩ ስሟ ወምበርኮ ማርያም ከምትባል ደብር እህል በመዉቃት ላይ ያሉ ንፁሃንን ላሊበላ ከተማ ልዩ ስሙ ሁለት ቁጥር ከሚባለው ቦታ በመሆን በዘፈቀደ ሞርተር 120 ወደ ንፁሃን በመተኮስ የአንድ ቤተሰብ ልጆች
1. ህፃን ወርቅየ ጌታቸው ዕድሜ=15 ወዲያውኑ አውድማው ላይ ሲሞት
2. ህፃን ደባሽ ጌታቸው ዕድሜ=8 ቀኝ እጁ የተቆረጠ እንዲሁም
3. የልጆቹ አባት አቶ ጌታቸው መለሰ ዕድሜ=46 በከባድ ሁኔታ የቆሰለ
4. ሰባት ከብቶች ወዲያውኑ ሲሞቱ
5. አውድማው ላይና በዙሪያው የነበረ ሦስት ክምር እህል ከ30 ኩንታል በላይ የሚገመት እህል ወድሟል።
የብልፅግና ወራሪ ሰራዊት ግብረ ሰዶም የሚፈፅም፣ህፃናትን የሚያርድ፣ንፁሃንን የሚረሽን በመድፍ አረር የሚቆላ፣አራጅ፣ደፋሪ ፀረ አማራ በመሆኑ በህዝባዊ ማዕበልና እምቢተኝነት ለአንዴና ለመጨረሻ ተባብረን እናስወግደው ሲሉ የጄኔራል ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ሃምሳ አለቃ ጌታየ ተፈሪ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ጄ/ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ አርበኛ ፋኖ ሽፈራው አለልኝ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 05/ 2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት ንፁሃንና እንስሳትን በከባድ መሳሪያ ጨፈጨፈ !
ህዳር 05/2018ዓ.ም
የአገዛዙ ብልፅግና ወንበር አስጠባቂ ጨፍጫፊ ሰራዊት በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ 04 ቀበሌ ሳርዝና ልዩ ስሟ ወምበርኮ ማርያም ከምትባል ደብር እህል በመዉቃት ላይ ያሉ ንፁሃንን ላሊበላ ከተማ ልዩ ስሙ ሁለት ቁጥር ከሚባለው ቦታ በመሆን በዘፈቀደ ሞርተር 120 ወደ ንፁሃን በመተኮስ የአንድ ቤተሰብ ልጆች
1. ህፃን ወርቅየ ጌታቸው ዕድሜ=15 ወዲያውኑ አውድማው ላይ ሲሞት
2. ህፃን ደባሽ ጌታቸው ዕድሜ=8 ቀኝ እጁ የተቆረጠ እንዲሁም
3. የልጆቹ አባት አቶ ጌታቸው መለሰ ዕድሜ=46 በከባድ ሁኔታ የቆሰለ
4. ሰባት ከብቶች ወዲያውኑ ሲሞቱ
5. አውድማው ላይና በዙሪያው የነበረ ሦስት ክምር እህል ከ30 ኩንታል በላይ የሚገመት እህል ወድሟል።
የብልፅግና ወራሪ ሰራዊት ግብረ ሰዶም የሚፈፅም፣ህፃናትን የሚያርድ፣ንፁሃንን የሚረሽን በመድፍ አረር የሚቆላ፣አራጅ፣ደፋሪ ፀረ አማራ በመሆኑ በህዝባዊ ማዕበልና እምቢተኝነት ለአንዴና ለመጨረሻ ተባብረን እናስወግደው ሲሉ የጄኔራል ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ሃምሳ አለቃ ጌታየ ተፈሪ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ጄ/ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ አርበኛ ፋኖ ሽፈራው አለልኝ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 05/ 2018 ዓ.ም
❤4💔2
የወንበዴ ስርዓት : የብልፅግና የደናቁርት አመራር : የደቦ ፍርድ ውጤት!
ይህ ሰው ጨካኝ ሆኖ የሰው ነፍስ አላጠፋም። በውንብድና ተግባር ተሰማርቶ አልያም ዘርፎ አይደለም፣ የሰው ሚስትም አልቀማም። እኔ እንደሰማሁት ከሆነም ልጁ በጨዋነቱ የሚወቀስም አልነበረም። የአከባቢው ሰዎችም እንዲሁ ነው የሚሉት። ምስኪን ነው።
ይህን የጭካኔ ጥግ፣ የግፍ ግፍ የፈፀሙበት ጉልበተኞች በወቅቱ በተፈጠረ ፀብም አልነበረም። በዚህ ልክ ማሰብ እንዲሳናቸው ያደረጋቸው የቆየ ነገር፣ ያደረ እና የከራረመ ቂም ይዘው መሆኑ ነው። የሰማሁት ይህንኑ ነው። የተባልኩትም እንዲሁ።
በ2009 ዓም ላይ ቤቴን አቃጥለሃል፣ ንብረቴን አውድመሃል ነው መነሻቸው። ይህን ብለው ቂማቸውን በግፍ ማወራረድ የፈለጉት ግለሰብ አቶ ብርሃኑ በቀለ የሚሰኙ እና በዲላ ዙሪ የአንዲዳ ቀበሌ ነዋሪም ናቸው።
ነሃሴ 24 2016 ዓ/ም አቶ ብርሃኑ በቀለ ተባባሪ ጓደኞቹን ይዞ ወጣት ደሳለኝ ማርያምን ወዳለበት መኖሪያ ቤት በማቅናት ያገኙታል። ይዘውትም ተረባርበውበት አዋክበውና አንገላተው ልብሱን ቀዳደው አውልቀው፣ እጆቹን በገመድ ጠፈሩት። እርቃኑን እንደሆነም ወደ ገበያ ለሽያጭ እንደሚነዱት ከ*ብ**ት እየጎተቱት፣ በአለንጋም እየገረፉት፣ በካሜራዎቻቸው እየቀረፁት እና ፎቶ እያነሱት፣ በሰው እያሳቁበት፣ እየተዘባበቱበት፣ ከኦቲልቾ እስከ አንዲዳ ድረስ ህዝብ እየተመለከታቸው፣ አንድም ተዉ፣ በህግ አምላክ፣ እባካችሁን እረፉ. . የሚላቸው ሳይኖር ህጉም፣ እግዜሩም፣ ሰዉም፣ ባህልም የሚጠየፈውን የነውር እና የጭካኔ ጥግ የሆነ ድርጊታቸውን በአደባባይ እየፈፀሙ፣ እንዲሁ ደጋግመው እየገረፉት፣ ባሰሩት ገመድ እየጎተቱት ለአንዲዳ ፖሊስ አስረክበውታል።
በወቅቱ የነበረው ፖሊስም ደሳለኝን እርቃኑን በገመድ ታስሮ ሲያየው ጥቂት እንኳን አልደነገጠም። "አስገቡት !!" ነበር ያለው። አዎን አስገቡት ከማለት ውጪ ለምን እንዲህ አደረጋችሁ ብሎ እንኳን አልጠየቃቸውም። ወጣቱ ምስኪን ደሳለኝም አንድ የሚረዳው፣ አንድ እንኳን የሚሟገትለት፣ አይዞህ የሚለው ሳይኖር ይህን ሁሉ ግፍ ተቀበለ። ምሬትን አጣጥሞ ቀመሰ። ጭካኔን እስከ ጥጉ ድረስ ያውም ሲፈፀምበት አየ። ሀፍረተ ስጋውን በእራፊ ጨርቅ እንኳ አልሸፈኑትም ነበር።
ከዚህ ሁሉ ስቃይ እና እስር በኋላም እንዲህ ሆነ።
ፖሊስ ነፃ ነህ ብሎት ካሰናበተው ቀን በኋላ ይህ ምስኪን ወጣት ደሳለኝ ማርያም የገባበት አልታወቀም።
ወላጅ አባቱ አቶ ማርያም ጎበና ከኦሮሚያ ክልል ሻኪሶ ወረዳ ሆነው፣ ለዲላ ከተማ አስተዳደር እና ለሚመለከተው ሁሉ ብለው በፃፉት ደብዳቤ
"ልጄን አጣሁት። ስራ ይሆናል ብለን ብንጠባበቀው ድምፁ ጠፋብን። ኋላ ላይም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እርቃኑን በገመድ አስረው ሲያሰቃዩት የሚያሳይ ፎቶ ተለቆ ያዩ ሰዎች ነገሩን። ለዲላ ከተማ ፖሊስ ባመለክት ከሶስት ወር ያለፈ ክስ አንቀበልም አሉኝ። ቢያንስ የልጄን መኖርም መሞትም ባውቅ ብዬ አልሆነልኝም። ፖሊስ እንኳን ለፍትህ ደጁን ዘጋብኝ" የሚል ይዘት ያለው ነው።
እንግዲህ ይህ የሆነው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን በዲላ ከተማ አስተዳደር ስር ነው። እንደሰማሁት ከሆነም የዲላ ከተማ ፖሊስ አዛዥ፣ ጉዳዩን ይዘውት የነበሩት መርማሪ ፖሊሶች በጉርሻ ተደልለው ነገሩ ተድበስብሶ እንዲቀር አድርገውታል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን፣ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ እና የዲላ ከተማ ፖሊስ ስለዚህ በሰው ልጅ ላይ ስለተፈፀመ ግፍ በቂ እና የተጣራ መረጃ እንዲሰጥ እናድርግ።
ይሄን ሁሉ ግፍ የፈፀሙት ጉልበተኞች እና ተባባሪ የህግ አካላቶች እንዲጠየቁ ማድረግ አለብን።
ምን የሚባል ኋላ ቀርነት፣ ምን የሚባል ጭካኔ፣ ምን የሚባል ከሰውነት መሸሽ እንደሆነም ይንገሩን። በየጊዜው የምንሰማው ዜና ሁሉ እውነት መንግስት ያለበት ሀገር ላይ ነን ?! ከማስባልም እያለፈ ነው።
እባካችሁ ይህን አፀያፊ ነውር መስማት ያለበት ሁሉ ጋር እንዲደርስ ሼር አድርጉት።
Cc Minase Wako Gudeta
ይህ ሰው ጨካኝ ሆኖ የሰው ነፍስ አላጠፋም። በውንብድና ተግባር ተሰማርቶ አልያም ዘርፎ አይደለም፣ የሰው ሚስትም አልቀማም። እኔ እንደሰማሁት ከሆነም ልጁ በጨዋነቱ የሚወቀስም አልነበረም። የአከባቢው ሰዎችም እንዲሁ ነው የሚሉት። ምስኪን ነው።
ይህን የጭካኔ ጥግ፣ የግፍ ግፍ የፈፀሙበት ጉልበተኞች በወቅቱ በተፈጠረ ፀብም አልነበረም። በዚህ ልክ ማሰብ እንዲሳናቸው ያደረጋቸው የቆየ ነገር፣ ያደረ እና የከራረመ ቂም ይዘው መሆኑ ነው። የሰማሁት ይህንኑ ነው። የተባልኩትም እንዲሁ።
በ2009 ዓም ላይ ቤቴን አቃጥለሃል፣ ንብረቴን አውድመሃል ነው መነሻቸው። ይህን ብለው ቂማቸውን በግፍ ማወራረድ የፈለጉት ግለሰብ አቶ ብርሃኑ በቀለ የሚሰኙ እና በዲላ ዙሪ የአንዲዳ ቀበሌ ነዋሪም ናቸው።
ነሃሴ 24 2016 ዓ/ም አቶ ብርሃኑ በቀለ ተባባሪ ጓደኞቹን ይዞ ወጣት ደሳለኝ ማርያምን ወዳለበት መኖሪያ ቤት በማቅናት ያገኙታል። ይዘውትም ተረባርበውበት አዋክበውና አንገላተው ልብሱን ቀዳደው አውልቀው፣ እጆቹን በገመድ ጠፈሩት። እርቃኑን እንደሆነም ወደ ገበያ ለሽያጭ እንደሚነዱት ከ*ብ**ት እየጎተቱት፣ በአለንጋም እየገረፉት፣ በካሜራዎቻቸው እየቀረፁት እና ፎቶ እያነሱት፣ በሰው እያሳቁበት፣ እየተዘባበቱበት፣ ከኦቲልቾ እስከ አንዲዳ ድረስ ህዝብ እየተመለከታቸው፣ አንድም ተዉ፣ በህግ አምላክ፣ እባካችሁን እረፉ. . የሚላቸው ሳይኖር ህጉም፣ እግዜሩም፣ ሰዉም፣ ባህልም የሚጠየፈውን የነውር እና የጭካኔ ጥግ የሆነ ድርጊታቸውን በአደባባይ እየፈፀሙ፣ እንዲሁ ደጋግመው እየገረፉት፣ ባሰሩት ገመድ እየጎተቱት ለአንዲዳ ፖሊስ አስረክበውታል።
በወቅቱ የነበረው ፖሊስም ደሳለኝን እርቃኑን በገመድ ታስሮ ሲያየው ጥቂት እንኳን አልደነገጠም። "አስገቡት !!" ነበር ያለው። አዎን አስገቡት ከማለት ውጪ ለምን እንዲህ አደረጋችሁ ብሎ እንኳን አልጠየቃቸውም። ወጣቱ ምስኪን ደሳለኝም አንድ የሚረዳው፣ አንድ እንኳን የሚሟገትለት፣ አይዞህ የሚለው ሳይኖር ይህን ሁሉ ግፍ ተቀበለ። ምሬትን አጣጥሞ ቀመሰ። ጭካኔን እስከ ጥጉ ድረስ ያውም ሲፈፀምበት አየ። ሀፍረተ ስጋውን በእራፊ ጨርቅ እንኳ አልሸፈኑትም ነበር።
ከዚህ ሁሉ ስቃይ እና እስር በኋላም እንዲህ ሆነ።
ፖሊስ ነፃ ነህ ብሎት ካሰናበተው ቀን በኋላ ይህ ምስኪን ወጣት ደሳለኝ ማርያም የገባበት አልታወቀም።
ወላጅ አባቱ አቶ ማርያም ጎበና ከኦሮሚያ ክልል ሻኪሶ ወረዳ ሆነው፣ ለዲላ ከተማ አስተዳደር እና ለሚመለከተው ሁሉ ብለው በፃፉት ደብዳቤ
"ልጄን አጣሁት። ስራ ይሆናል ብለን ብንጠባበቀው ድምፁ ጠፋብን። ኋላ ላይም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እርቃኑን በገመድ አስረው ሲያሰቃዩት የሚያሳይ ፎቶ ተለቆ ያዩ ሰዎች ነገሩን። ለዲላ ከተማ ፖሊስ ባመለክት ከሶስት ወር ያለፈ ክስ አንቀበልም አሉኝ። ቢያንስ የልጄን መኖርም መሞትም ባውቅ ብዬ አልሆነልኝም። ፖሊስ እንኳን ለፍትህ ደጁን ዘጋብኝ" የሚል ይዘት ያለው ነው።
እንግዲህ ይህ የሆነው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን በዲላ ከተማ አስተዳደር ስር ነው። እንደሰማሁት ከሆነም የዲላ ከተማ ፖሊስ አዛዥ፣ ጉዳዩን ይዘውት የነበሩት መርማሪ ፖሊሶች በጉርሻ ተደልለው ነገሩ ተድበስብሶ እንዲቀር አድርገውታል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን፣ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ እና የዲላ ከተማ ፖሊስ ስለዚህ በሰው ልጅ ላይ ስለተፈፀመ ግፍ በቂ እና የተጣራ መረጃ እንዲሰጥ እናድርግ።
ይሄን ሁሉ ግፍ የፈፀሙት ጉልበተኞች እና ተባባሪ የህግ አካላቶች እንዲጠየቁ ማድረግ አለብን።
ምን የሚባል ኋላ ቀርነት፣ ምን የሚባል ጭካኔ፣ ምን የሚባል ከሰውነት መሸሽ እንደሆነም ይንገሩን። በየጊዜው የምንሰማው ዜና ሁሉ እውነት መንግስት ያለበት ሀገር ላይ ነን ?! ከማስባልም እያለፈ ነው።
እባካችሁ ይህን አፀያፊ ነውር መስማት ያለበት ሁሉ ጋር እንዲደርስ ሼር አድርጉት።
Cc Minase Wako Gudeta
❤5