ዘመቻ ሰማዕታት በድል እንደቀጠለ ነው !!
በዛሬው ዕለት እሁድ ነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ማጥቃት ሰባተኛ ሀዲስ አለማየሁ ክፍለጦር በሶስት ከተሞች ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ አድርጓል ።
1/ ኮርክ ከተማ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ገብታለች ።
2/ ሉማሜ ከተማ ውስጥ በመግባት አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያለው ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ ተደርጓል ።
3/ አምበር ከተማ በመግባት መብረቃዊ ጥቃት ፈጽሟል ።
4/ የሶስተኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር እና የአራተኛ ጃዊ ክፍለጦር አባላት በጋራ በመሆን ወርቅ ሜዳ ላይ በነበረው ሰራዊት ላይ በፈጸሙት ጥቃት የሻምበል አመራሮችን ጨምሮ በርካታ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ተደምስሷል ።
በአውደ ውጊያው የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና እግረኛ የጠላት ሰራዊት ተማርኳል ።
በዝርዝር ይዘን እንመለሳለን !!
ክብር ለሰማዕታት !!
በዛሬው ዕለት እሁድ ነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ማጥቃት ሰባተኛ ሀዲስ አለማየሁ ክፍለጦር በሶስት ከተሞች ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ አድርጓል ።
1/ ኮርክ ከተማ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ገብታለች ።
2/ ሉማሜ ከተማ ውስጥ በመግባት አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያለው ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ ተደርጓል ።
3/ አምበር ከተማ በመግባት መብረቃዊ ጥቃት ፈጽሟል ።
4/ የሶስተኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር እና የአራተኛ ጃዊ ክፍለጦር አባላት በጋራ በመሆን ወርቅ ሜዳ ላይ በነበረው ሰራዊት ላይ በፈጸሙት ጥቃት የሻምበል አመራሮችን ጨምሮ በርካታ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ተደምስሷል ።
በአውደ ውጊያው የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና እግረኛ የጠላት ሰራዊት ተማርኳል ።
በዝርዝር ይዘን እንመለሳለን !!
ክብር ለሰማዕታት !!
❤3🙏1
ሰበር ዜና
ፋኖን ለማስኮብለል የተላኩት ሽማግሌዎች "ፋኖ እዉነትኛ የፍትህ፣የነፃነት አርበኛነዉ" ሽማግሌዎች አርበኛ አንተነህ ድረስ በሽማግሌዎቹ ተመስክሮለታል
ፋኖን ለማስኮብለል የተላኩት ሽማግሌዎች "ፋኖ እዉነትኛ የፍትህ፣የነፃነት አርበኛነዉ" ሽማግሌዎች አርበኛ አንተነህ ድረስ በሽማግሌዎቹ ተመስክሮለታል
👍2
ሰበር ዜና
ፋኖን ለማስኮብለል የተላኩት ሽማግሌዎች "ፋኖ እዉነትኛ የፍትህ፣የነፃነት አርበኛነዉ" ሽማግሌዎች አርበኛ አንተነህ ድረስ በሽማግሌዎቹ ተመስክሮለታል
ፋኖን ለማስኮብለል የተላኩት ሽማግሌዎች "ፋኖ እዉነትኛ የፍትህ፣የነፃነት አርበኛነዉ" ሽማግሌዎች አርበኛ አንተነህ ድረስ በሽማግሌዎቹ ተመስክሮለታል
🙏2
📌የክቡር ሰማዕቱ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው አንደኛ ዓመት ሙት ዓመት መታሰቢያ!
"ንፁህ ትግል ታግዬ ነው መሞት የምፈልገው" በሚል ንግግሩ ይታወቃል። ክቡር ሰማዕቱ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው።
"የተቆጣ ነብር ቆፍጣና ጦረኛ፣
ሀገሩ ወሎ ነው ጎጃም ድንበርተኛ"
በሚል ባላገር ስንኝ ከቋጠረላቸው ከጀግኖቹና ከደጎቹ ቀየ አማራ ሣይንት ነው ትውልዱና እድገቱ።
ሀገሬው አይደለም የወንድ ጀግና እንደ አራስ ነብር የሚሶረፉ የሴት ጀግኖችንም ማፍራት ያውቅበታል። ለዛም ነው አዝማሪው፦
"በአብራራው አንቀልባ ወንድ ልጅ አዝላለች
የአማራ ሳይንቷ እሷው ትሆናለች" ሲል ስንኝ የቋጨላት።
አከባቢው፦
"ማን ያመጣልኛል?
ከሳይንት ነጭ ጤፍ ከቦረና ስንዴ፡
አሰሱን ገሰሱን አልበላ አለ ሆዴ" የሚል ስንኝ የተቋጠረለትም እንዲሁ በዋዛ አይደለም። ይልቅስ በመንደሩ ጀግናም፣ ጀግና ሆኖ ሐቀኛም፣ አራሽ አንደፋራሽም ስለሚበቅል ነው።ቀጠናው የጤፍ እና ስንዴ አምራቾች ምድር እንዲሁም የአልሞ ተኳሾች እርስተ ጉልት ነው።ይህ አካባቢ ወንድ ልጅ ሲወለድ ተኳሽ እና አራሽ አንደፋራሽ እንዲሆን በማለት ተፈጥሮም የምታሽቃሽጥበት አካባቢ ነው።
አዎ!
ሣይንትን ለጀግንነት ማን አምቶት?
"ሳይንት አፋፉ ላይ የተሰራ ቤት
ግድግዳው ጠብመንጃ ክዳኑ ጥይት" ይባላል። የሳይንት ሰው ቤቱም፣ የቤቱ ክዳንም፡ ጥይት ስለሆነ የከፋው ቀን፣ ፍትህ ተጓደለ ብሎ ያሰበ ቀን ከቤቱ ግድግዳ የያስቀመጠውን መሣሪያ ፈልፍሎ መዥረጥ ያደርግና ዱር ቤቴ ይላል።
በማይጨው ጦርነት ወቅት፦
"አይኑ መነጽር ጠብመንጃው ሆዳም
ነጭ ሰው ገዳይ ደባልቄ ካዳም"
የተባለለት ስመጥር ዘማች አርበኛ የበቀለውም ከዚሁ ከቦረና ሳይንት አውራጃ ነው።
ድሮስ የአማራ ሣይንት ምድርን ሐቀኛ ጀግኖችን ለማፍራት መች ታምቶ ያውቃል? መጠርጠሩስ?
"የሳይንቶች ዘር የዋጩ ጥሪት፡
ልቡ ድፍን ነው እንደ መድሀኒት" ሲሉ ጎበዞች ያንጎራጎሩት፡
"እወቀረዋለሁ ጥርሴን በጥይት፡
የጀግና ልጅ ሀገር አማራ ሳይንት" ሲሉ ኮረዳዎች የተቀኙት እኮ ለዋዛ አይደለም።
ሀገር ምድሩ ጀግና እና እህል ማብቀል ያውቃል። ወትሮውንስ የአማራ እናት መች ነጥፋ ታውቅና?
"ንፁህ ትግል ታግዬ ነው መሞት የምፈልገው" በሚል ንግግሩ የምናስታውሰው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው የዚሁ አከባቢ ፍሬ ነው።
ይህ የኛ ዘመን አብሪ ኮከብ፣ ይህ የዘመናችን የነፃነት ፋና ወጊ፣ ይህ የዘመናችን እንቁ የጦር ገበሬ፣ ፀረ ባንዳና ፀረ ሆዳም፣ በአማራ ሕዝብ ላይ የወደቀውን የሞት ቀንበርን ለመስበር ለሦስትና አራት ዓመታት በዱር በገደሉ ሲዋደቅ ከርሞ በመጨረሻም በሞቱ ሞትን ገድሎ የክብር ሞት ሸማን ከተጎናፀፈ እንሆ ዛሬ ድፍን እንድ ዓመትን አስቆጥሯል።
ቀኝ አዝማች ይታገሱ በጦር ሜዳ የተዋጋው የብልፅግናው ቡድን ያሰለፈው ወታደርን ብቻ አይደለም። ጎጠኝነትንና አድርባይነትን እንዲሁም ሆዳምነትንም ጭምር እንጂ። ለዚህ ደግሞ ከሕወሓት ወረራ ጀምሮ ተጋድሎ የፈፀመባቸው አውደ ግምባሮች አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ። ገንዘብና ወንበር ሲያይ ሰፍ ያላለ...ሕልውናውን በምስር ወጥ ያልቀየረ...እንቁ ጀግና።
ይህ ተወርዋሪ ምሽግ ደርማሽ ጀግና፡ ክንዱን ከተንተራሰ እንሆ ዛሬ ነሐሴ 25/2017 ዓ/ም ድፍን አንድ ዓመት ሞላው።
በርግጥ ሀገሬው ሰው አማኝና ታማኝም ነው።ይህ ፍጣሮቱም በያዝነው የሕልውና ትግል ብቻ እንኳን ካንዴም ሁለቴ ዋጋ አስከፍሎታል።
አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ የተገደለው፡ ከውጊያ ውሎ ተመልሶ አረፍ እንዳለ አምኖ አቅርቧቸው በነበሩ የሕዝብ አደራን በምስር ወጥ በሸጡ ባንዳዎች ነው።
ሀገሬው የዚህ ብስጭት ሳይወጣለት፡ የአርበኛ ይታገሱ ቀኝ እጅ የነበሩት ሳጅን አደም አሊም እንዲሁ አምነው ባቀረቧቸው ተከድተው ከተሰዉ ወራቶች ተቆጥረዋል።
አሁንም በቀጠናው የሚገኙ ጀግኖችን ለመጠበቅ ጥንቃቄ ይሻል።የአማራ እናት "ጀግና ወላዲቱ" ተብላ ተሞግሳ ሲያበቃ፡ እስከመቼ "የሟቹ እናት" ተብላ ትጠራ?
በርግጥ አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው አንድ ሆኖ በክብር ወድቆ፡ ሺህ ሆኖ በቅሏል። በሱ ስም እየፎከሩ ምሽግ የሚሰብሩ ጀግኖች እልፍ ናቸው።
ምድር ቃጢ በሆነችበት ውጊያ መኃል
"ዘራፍ ...የይቴ ወንድም፡
እንበለው እንጂ መሸሽ አይወድም"
እያሉ እየፎገሉ ከምሽግ ምሽግ የሚወረወሩ ጀግኖችን ያየ ሰው በርግጥ አርበኛ ይታገሱ አልሞተም አለ ብሎ ቢከራከር አይፈረድበትም። ትክክል ነው እልፍ አዕላፍ ጀግኖችን አፍርቷል።
ክቡር ሰማዕቱ አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው ነፍስህ በሰላም ትረፍ!
ስለ ህፃን አይሻ ሰይድና ስለ ሕዝቧ የተከፈለ ወጣትነት!
ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
ዘገባው የመረብ ሚዲያ ነው!
"ንፁህ ትግል ታግዬ ነው መሞት የምፈልገው" በሚል ንግግሩ ይታወቃል። ክቡር ሰማዕቱ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው።
"የተቆጣ ነብር ቆፍጣና ጦረኛ፣
ሀገሩ ወሎ ነው ጎጃም ድንበርተኛ"
በሚል ባላገር ስንኝ ከቋጠረላቸው ከጀግኖቹና ከደጎቹ ቀየ አማራ ሣይንት ነው ትውልዱና እድገቱ።
ሀገሬው አይደለም የወንድ ጀግና እንደ አራስ ነብር የሚሶረፉ የሴት ጀግኖችንም ማፍራት ያውቅበታል። ለዛም ነው አዝማሪው፦
"በአብራራው አንቀልባ ወንድ ልጅ አዝላለች
የአማራ ሳይንቷ እሷው ትሆናለች" ሲል ስንኝ የቋጨላት።
አከባቢው፦
"ማን ያመጣልኛል?
ከሳይንት ነጭ ጤፍ ከቦረና ስንዴ፡
አሰሱን ገሰሱን አልበላ አለ ሆዴ" የሚል ስንኝ የተቋጠረለትም እንዲሁ በዋዛ አይደለም። ይልቅስ በመንደሩ ጀግናም፣ ጀግና ሆኖ ሐቀኛም፣ አራሽ አንደፋራሽም ስለሚበቅል ነው።ቀጠናው የጤፍ እና ስንዴ አምራቾች ምድር እንዲሁም የአልሞ ተኳሾች እርስተ ጉልት ነው።ይህ አካባቢ ወንድ ልጅ ሲወለድ ተኳሽ እና አራሽ አንደፋራሽ እንዲሆን በማለት ተፈጥሮም የምታሽቃሽጥበት አካባቢ ነው።
አዎ!
ሣይንትን ለጀግንነት ማን አምቶት?
"ሳይንት አፋፉ ላይ የተሰራ ቤት
ግድግዳው ጠብመንጃ ክዳኑ ጥይት" ይባላል። የሳይንት ሰው ቤቱም፣ የቤቱ ክዳንም፡ ጥይት ስለሆነ የከፋው ቀን፣ ፍትህ ተጓደለ ብሎ ያሰበ ቀን ከቤቱ ግድግዳ የያስቀመጠውን መሣሪያ ፈልፍሎ መዥረጥ ያደርግና ዱር ቤቴ ይላል።
በማይጨው ጦርነት ወቅት፦
"አይኑ መነጽር ጠብመንጃው ሆዳም
ነጭ ሰው ገዳይ ደባልቄ ካዳም"
የተባለለት ስመጥር ዘማች አርበኛ የበቀለውም ከዚሁ ከቦረና ሳይንት አውራጃ ነው።
ድሮስ የአማራ ሣይንት ምድርን ሐቀኛ ጀግኖችን ለማፍራት መች ታምቶ ያውቃል? መጠርጠሩስ?
"የሳይንቶች ዘር የዋጩ ጥሪት፡
ልቡ ድፍን ነው እንደ መድሀኒት" ሲሉ ጎበዞች ያንጎራጎሩት፡
"እወቀረዋለሁ ጥርሴን በጥይት፡
የጀግና ልጅ ሀገር አማራ ሳይንት" ሲሉ ኮረዳዎች የተቀኙት እኮ ለዋዛ አይደለም።
ሀገር ምድሩ ጀግና እና እህል ማብቀል ያውቃል። ወትሮውንስ የአማራ እናት መች ነጥፋ ታውቅና?
"ንፁህ ትግል ታግዬ ነው መሞት የምፈልገው" በሚል ንግግሩ የምናስታውሰው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው የዚሁ አከባቢ ፍሬ ነው።
ይህ የኛ ዘመን አብሪ ኮከብ፣ ይህ የዘመናችን የነፃነት ፋና ወጊ፣ ይህ የዘመናችን እንቁ የጦር ገበሬ፣ ፀረ ባንዳና ፀረ ሆዳም፣ በአማራ ሕዝብ ላይ የወደቀውን የሞት ቀንበርን ለመስበር ለሦስትና አራት ዓመታት በዱር በገደሉ ሲዋደቅ ከርሞ በመጨረሻም በሞቱ ሞትን ገድሎ የክብር ሞት ሸማን ከተጎናፀፈ እንሆ ዛሬ ድፍን እንድ ዓመትን አስቆጥሯል።
ቀኝ አዝማች ይታገሱ በጦር ሜዳ የተዋጋው የብልፅግናው ቡድን ያሰለፈው ወታደርን ብቻ አይደለም። ጎጠኝነትንና አድርባይነትን እንዲሁም ሆዳምነትንም ጭምር እንጂ። ለዚህ ደግሞ ከሕወሓት ወረራ ጀምሮ ተጋድሎ የፈፀመባቸው አውደ ግምባሮች አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ። ገንዘብና ወንበር ሲያይ ሰፍ ያላለ...ሕልውናውን በምስር ወጥ ያልቀየረ...እንቁ ጀግና።
ይህ ተወርዋሪ ምሽግ ደርማሽ ጀግና፡ ክንዱን ከተንተራሰ እንሆ ዛሬ ነሐሴ 25/2017 ዓ/ም ድፍን አንድ ዓመት ሞላው።
በርግጥ ሀገሬው ሰው አማኝና ታማኝም ነው።ይህ ፍጣሮቱም በያዝነው የሕልውና ትግል ብቻ እንኳን ካንዴም ሁለቴ ዋጋ አስከፍሎታል።
አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ የተገደለው፡ ከውጊያ ውሎ ተመልሶ አረፍ እንዳለ አምኖ አቅርቧቸው በነበሩ የሕዝብ አደራን በምስር ወጥ በሸጡ ባንዳዎች ነው።
ሀገሬው የዚህ ብስጭት ሳይወጣለት፡ የአርበኛ ይታገሱ ቀኝ እጅ የነበሩት ሳጅን አደም አሊም እንዲሁ አምነው ባቀረቧቸው ተከድተው ከተሰዉ ወራቶች ተቆጥረዋል።
አሁንም በቀጠናው የሚገኙ ጀግኖችን ለመጠበቅ ጥንቃቄ ይሻል።የአማራ እናት "ጀግና ወላዲቱ" ተብላ ተሞግሳ ሲያበቃ፡ እስከመቼ "የሟቹ እናት" ተብላ ትጠራ?
በርግጥ አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው አንድ ሆኖ በክብር ወድቆ፡ ሺህ ሆኖ በቅሏል። በሱ ስም እየፎከሩ ምሽግ የሚሰብሩ ጀግኖች እልፍ ናቸው።
ምድር ቃጢ በሆነችበት ውጊያ መኃል
"ዘራፍ ...የይቴ ወንድም፡
እንበለው እንጂ መሸሽ አይወድም"
እያሉ እየፎገሉ ከምሽግ ምሽግ የሚወረወሩ ጀግኖችን ያየ ሰው በርግጥ አርበኛ ይታገሱ አልሞተም አለ ብሎ ቢከራከር አይፈረድበትም። ትክክል ነው እልፍ አዕላፍ ጀግኖችን አፍርቷል።
ክቡር ሰማዕቱ አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው ነፍስህ በሰላም ትረፍ!
ስለ ህፃን አይሻ ሰይድና ስለ ሕዝቧ የተከፈለ ወጣትነት!
ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
ዘገባው የመረብ ሚዲያ ነው!
🙏4
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ፤
"እኔ ብሞት ደሜን የምትመልሱት ገዳዬን ገድላችሁ ሳይሆን የአማራ ህዝብን ነፃ አውጥታችሁ ነው" በማለት በህይወት ሳለ በተደጋጋሚ ሲናገር የነበረው የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋውን ህልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ እለት አስመልክቶ የተላለፈ ድርጅታዊ መልዕክት:-
የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር አማራ ሣይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አዛዥ እንዲሁም የመሀል ሳይንቱ አትሮንስ ብርጌድ አዛዥ የነበረውና ቀደም ብሎም ከምስራቅ አማራ ፋኖ (2013 ዓ.ም) ጀምሮ በትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም ሆኖ ጀብዱ የፈፀመው የቦሩ ሜዳው ውጊያ ፊታውራሪ እና ፅኑው ታጋይ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በድህረ ሰሜኑ ጦርነት ወቅት የያኔው ምስራቅ አማራ ፋኖ የሰጠውን ግዳጅ ተቀብሎ ወደ ትውልድ አካባቢው መሀል ሳይንት ወረዳ በማቅናት ወጣቶችን በማንቃት እና በመመልመል እንዲሁም በፋኖነት በማደራጀት ጉልህ ሚና ተጫውቶ በወርሀ መጋቢት 2015 ዓ.ም ይፋዊ የህልውና ፍልሚያ ስንጀምር እሱም ባለበት ግንባር ኃይሉን ሸክፎ ቀጥታ ወደ ትግሉ በአዲስ መልኩ መግባቱ ይታወሳል::
የህልውና ትግሉ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ወራት በፅናት እና በጀግንነት በውጊያ ሜዳው ላይ ታይቶ አምና ልክ በዛሬው እለት ማለትም ነሀሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በባንዳ በተተኮሰ ጥይት በድንገት ያጣነው የትግል ጓዳችን እና ወንድማችን ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በትግሉ ሂደት የሚከፈለው መስዋዕትነት በጠላት በተተኮሰ ብቻ ሳይሆን በወገን ጥይት ጭምር ሊሆን እንደሚችልና በሁለቱም አቅጣጫ ለሚተኮስ ጥይት ዝግጁ መሆን እንደሚገባ አስተማሪ ሆኖ አልፏል:: በወገን ባለጋራ እጅ መሞት የትግሉ ሜዳ እንድጠራ በር የመክፈት መስዋዕትነት ሲሆን ጀብዱ ፈጽሞ ጥሎ እንደ መውደቅ ማለትም ልክ በጠላት እጅ እንደመሞት ያለ ክቡር መስዋዕትነት ነው::
ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በጆፌ ኢትዮጵያኒስቱ ኃይል ሳይታለል በአማራ ብሔርተኝነት እና በእውነት ፍፁም አልደራደርም ብሎ አሰላለፉን አሳምሮ ለወሎ ቤተ አማራ ፋኖ አንድነት የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ የከፈለ አርበኛ ብቻ ሳይሆን ንፁህ ትግልን ታግሎ በማለፍ ሌሎች ንፁህ ታጋዮችን ማፍራት የቻለ የህልውን ትግሉ ደማቅ ምልክትም ነው:: የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ሰራዊት እና አመራሮች ለፋኖአዊ አንድነት እና ለአማራዊ እሴት ያላቸውን ትልቅ ቦታ አስረጅ የሆነው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ንፅህና እና እውነት የታጋዩ እና የትግላችን መሰረት መሆኑን ማሳያነቱ አያጠራጥርም::
ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በምዕራብ ወሎ ግንባር መሀል ሳይንት ወረዳ ውስጥ በተለምዶ አህዮ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ ሰኞ ገበያ የተባለ ስፍራ ላይ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በመምራት ላይ ሳለ አንድ ቅጥረኛ ባንዳ ግለሰብ በተኮሰው አውቶማቲክ ጥይት ተመትቶ ቢሰዋም ባንዳው ላይ የመሀል ሳይንቱ አትሮንስ ብርጌድ አባል የሆነ ጀግና ጓድ በጀት ፍጥነት እርምጃ መውሰዱን እንዲሁም በማግስቱ የቀብር ስነ-ስርዓቱ ከመፈፀሙ የተወሰኑ ሰዓታት ቀደም ብሎ የክፍለ ጦሩ አካል የሆነው ታቦር ተራራ ብርጌድ ሰራዊት ከመሀል ሳይንት ወረዳ ቀጥሎ የሚገኘው አማራ ሳይንት ወረዳ ውስጥ ፓትሮል በማቃጠል ከአንድ ቲም ያላነሰ ጠላትን በመደምሰስ 3 ክላሽ እና 1 ብሬን ከነ ሽልንሼሉ መማረኩ አይረሳም:: በእለቱ እለት እና በማግስቱ ደሙ የተመለሰለት ጓዳችን እና የትግል ወንድማችን ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በህይወት ሳለም ሲናገር የነበረው "እኔ ብሞት ደሜን የምትመልሱት ገዳዬን ገድላችሁ ሳይሆን የአማራ ህዝብን ነፃ አውጥታችሁ ነው" በማለት ነበር:: በዚህም መሰረት ለነፃነት እና ለህልውና የሚደረገው ትንቅንቅ እና የሚከፈለው መስዋእትነት ቀጥሎ ሰራዊታችን በየእለቱ ጀብዱ እየፈፀመ መሆኑን ያስታውሷል::
"ገንዘብ ስታዩ አትደንግጡ" የሚለውን የዋርካው ምሬ ወዳጆ ወርቃማ ምክር በመተግበር ለገንዘብ ባለመደንገጥ በእውቀት እና በታማኝነት እንዲሁም በጀግንነት ታግሎ በንፅህና ያለፈው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው "ሲርባቸው ይመጣሉ" ያሉን ወገኖችን ጭምር አሳፍሮ የመለሰ የሀቅ እና የእውነት ታጋይ በመሆኑ ሁሌም ስሙ ሲዘከር በአርአያነትም በየመድረኩ በክብር ሲጠራ ይኖራል::
ለቀጠናዊ መናበብ እና ለአማራዊ አንድነት ልዩ ቦታ በመስጠት አንድ የፋኖ ድርጅት እንድፈጠር ለማድረግ ደፋ ቀና ሲል የነበረ መሆኑም አይረሴ ነው::
ከምስራቅ ጎጃም እና ደቡብ ጎንደር ፋኖወች ጋር ቀጠናዊ ትስስር በመፍጠር ለአማራዊ አንድነት መደላድል ሲፈጠር የነበረው ይህ ጀግና ያፈራው ሰራዊት በምዕራብ ወሎ ግንባር ከመሀል ሳይንት ተነስቶ ወግዲ እና መካነሰላም እንዲሁም ከላላ እና መቅደላ ብሎም ተንታ እና ሌሎች አጎራባች ወረዳወች ድረስ ታሪክ ሰርቷል፤ እየሰራም ነው::
የአንድነት ሀዋርያው፣ በእውነት እና እውነት ይታወቅ የነበረው...ጎጥ እና ጥቅም የማይበግረው ከገንዘብ ይልቅ ህዝብን አስቀዳሚው ንፁሁ ታጋይ ቢሞትም ስሙ አልተቀበረም፤ ትግሉም ተቀጣጥሏል እንጅ አልቀዘቀዘም::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ነሀሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
"እኔ ብሞት ደሜን የምትመልሱት ገዳዬን ገድላችሁ ሳይሆን የአማራ ህዝብን ነፃ አውጥታችሁ ነው" በማለት በህይወት ሳለ በተደጋጋሚ ሲናገር የነበረው የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋውን ህልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ እለት አስመልክቶ የተላለፈ ድርጅታዊ መልዕክት:-
የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር አማራ ሣይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አዛዥ እንዲሁም የመሀል ሳይንቱ አትሮንስ ብርጌድ አዛዥ የነበረውና ቀደም ብሎም ከምስራቅ አማራ ፋኖ (2013 ዓ.ም) ጀምሮ በትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም ሆኖ ጀብዱ የፈፀመው የቦሩ ሜዳው ውጊያ ፊታውራሪ እና ፅኑው ታጋይ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በድህረ ሰሜኑ ጦርነት ወቅት የያኔው ምስራቅ አማራ ፋኖ የሰጠውን ግዳጅ ተቀብሎ ወደ ትውልድ አካባቢው መሀል ሳይንት ወረዳ በማቅናት ወጣቶችን በማንቃት እና በመመልመል እንዲሁም በፋኖነት በማደራጀት ጉልህ ሚና ተጫውቶ በወርሀ መጋቢት 2015 ዓ.ም ይፋዊ የህልውና ፍልሚያ ስንጀምር እሱም ባለበት ግንባር ኃይሉን ሸክፎ ቀጥታ ወደ ትግሉ በአዲስ መልኩ መግባቱ ይታወሳል::
የህልውና ትግሉ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ወራት በፅናት እና በጀግንነት በውጊያ ሜዳው ላይ ታይቶ አምና ልክ በዛሬው እለት ማለትም ነሀሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በባንዳ በተተኮሰ ጥይት በድንገት ያጣነው የትግል ጓዳችን እና ወንድማችን ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በትግሉ ሂደት የሚከፈለው መስዋዕትነት በጠላት በተተኮሰ ብቻ ሳይሆን በወገን ጥይት ጭምር ሊሆን እንደሚችልና በሁለቱም አቅጣጫ ለሚተኮስ ጥይት ዝግጁ መሆን እንደሚገባ አስተማሪ ሆኖ አልፏል:: በወገን ባለጋራ እጅ መሞት የትግሉ ሜዳ እንድጠራ በር የመክፈት መስዋዕትነት ሲሆን ጀብዱ ፈጽሞ ጥሎ እንደ መውደቅ ማለትም ልክ በጠላት እጅ እንደመሞት ያለ ክቡር መስዋዕትነት ነው::
ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በጆፌ ኢትዮጵያኒስቱ ኃይል ሳይታለል በአማራ ብሔርተኝነት እና በእውነት ፍፁም አልደራደርም ብሎ አሰላለፉን አሳምሮ ለወሎ ቤተ አማራ ፋኖ አንድነት የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ የከፈለ አርበኛ ብቻ ሳይሆን ንፁህ ትግልን ታግሎ በማለፍ ሌሎች ንፁህ ታጋዮችን ማፍራት የቻለ የህልውን ትግሉ ደማቅ ምልክትም ነው:: የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ሰራዊት እና አመራሮች ለፋኖአዊ አንድነት እና ለአማራዊ እሴት ያላቸውን ትልቅ ቦታ አስረጅ የሆነው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ንፅህና እና እውነት የታጋዩ እና የትግላችን መሰረት መሆኑን ማሳያነቱ አያጠራጥርም::
ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በምዕራብ ወሎ ግንባር መሀል ሳይንት ወረዳ ውስጥ በተለምዶ አህዮ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ ሰኞ ገበያ የተባለ ስፍራ ላይ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በመምራት ላይ ሳለ አንድ ቅጥረኛ ባንዳ ግለሰብ በተኮሰው አውቶማቲክ ጥይት ተመትቶ ቢሰዋም ባንዳው ላይ የመሀል ሳይንቱ አትሮንስ ብርጌድ አባል የሆነ ጀግና ጓድ በጀት ፍጥነት እርምጃ መውሰዱን እንዲሁም በማግስቱ የቀብር ስነ-ስርዓቱ ከመፈፀሙ የተወሰኑ ሰዓታት ቀደም ብሎ የክፍለ ጦሩ አካል የሆነው ታቦር ተራራ ብርጌድ ሰራዊት ከመሀል ሳይንት ወረዳ ቀጥሎ የሚገኘው አማራ ሳይንት ወረዳ ውስጥ ፓትሮል በማቃጠል ከአንድ ቲም ያላነሰ ጠላትን በመደምሰስ 3 ክላሽ እና 1 ብሬን ከነ ሽልንሼሉ መማረኩ አይረሳም:: በእለቱ እለት እና በማግስቱ ደሙ የተመለሰለት ጓዳችን እና የትግል ወንድማችን ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው በህይወት ሳለም ሲናገር የነበረው "እኔ ብሞት ደሜን የምትመልሱት ገዳዬን ገድላችሁ ሳይሆን የአማራ ህዝብን ነፃ አውጥታችሁ ነው" በማለት ነበር:: በዚህም መሰረት ለነፃነት እና ለህልውና የሚደረገው ትንቅንቅ እና የሚከፈለው መስዋእትነት ቀጥሎ ሰራዊታችን በየእለቱ ጀብዱ እየፈፀመ መሆኑን ያስታውሷል::
"ገንዘብ ስታዩ አትደንግጡ" የሚለውን የዋርካው ምሬ ወዳጆ ወርቃማ ምክር በመተግበር ለገንዘብ ባለመደንገጥ በእውቀት እና በታማኝነት እንዲሁም በጀግንነት ታግሎ በንፅህና ያለፈው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው "ሲርባቸው ይመጣሉ" ያሉን ወገኖችን ጭምር አሳፍሮ የመለሰ የሀቅ እና የእውነት ታጋይ በመሆኑ ሁሌም ስሙ ሲዘከር በአርአያነትም በየመድረኩ በክብር ሲጠራ ይኖራል::
ለቀጠናዊ መናበብ እና ለአማራዊ አንድነት ልዩ ቦታ በመስጠት አንድ የፋኖ ድርጅት እንድፈጠር ለማድረግ ደፋ ቀና ሲል የነበረ መሆኑም አይረሴ ነው::
ከምስራቅ ጎጃም እና ደቡብ ጎንደር ፋኖወች ጋር ቀጠናዊ ትስስር በመፍጠር ለአማራዊ አንድነት መደላድል ሲፈጠር የነበረው ይህ ጀግና ያፈራው ሰራዊት በምዕራብ ወሎ ግንባር ከመሀል ሳይንት ተነስቶ ወግዲ እና መካነሰላም እንዲሁም ከላላ እና መቅደላ ብሎም ተንታ እና ሌሎች አጎራባች ወረዳወች ድረስ ታሪክ ሰርቷል፤ እየሰራም ነው::
የአንድነት ሀዋርያው፣ በእውነት እና እውነት ይታወቅ የነበረው...ጎጥ እና ጥቅም የማይበግረው ከገንዘብ ይልቅ ህዝብን አስቀዳሚው ንፁሁ ታጋይ ቢሞትም ስሙ አልተቀበረም፤ ትግሉም ተቀጣጥሏል እንጅ አልቀዘቀዘም::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ነሀሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
👍4❤2
እየጨመረ የመጣው ቀጠናዊና የውስጥ ስጋት፤ የአማራ ፋኖ አንድነት አስፈላጊነት በሻለቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ
እየጨመረ የመጣው ቀጠናዊና የውስጥ ስጋት፤ የአማራ ፋኖ አንድነት አስፈላጊነት በሻለቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ
🙏2
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት የኦርቶዶክሳውያን ግድያ መቀጠሉን ምእመናን ተናገሩ።
የ75 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው ካህን ማንነታቸዉ ባልታወቁ ታጣቂ ኃይሎች ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት በመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት
ቀሲስ ንጉሴ ወልደ መድኅን ማንነታቸዉ ባልታወቁ ታጣቂ ኃይሎች ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ሌሊት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ምእመናን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገልጸዋል።።
የ75 ዓመት አረጋዊው ካህን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከልጅነት እስከተገደሉበት ቀን ድረስ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ከዲቁና እስከ ቅስና አገልግለዋል።
በአገልግሎት ዘመናቸውም ዳሪሙ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተባበር አሠርተው ለአገልግሎት ማብቃታቸው ተጠቅሷል።
የቀሲስ ንጉሴ ወልደ መድኅን ሥርዓተ ቀብር ነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
በምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሮቤ ወረዳ እየተባባሰ የመጣዉን የኦርዶክሳዉያን መከራ እና ሞት የሚመለከተው አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸዉ በተደጋጋሚ ጊዜ የአካባቢው ምእመናን ጥሪ ቢያቀርቡም አሁንም ድረስ የኦርቶዶክሳውያን ግድያና መከራ እንዳላበቃ ከምእመናኑ አንደበት ተገልጿል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።
የ75 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው ካህን ማንነታቸዉ ባልታወቁ ታጣቂ ኃይሎች ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት በመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት
ቀሲስ ንጉሴ ወልደ መድኅን ማንነታቸዉ ባልታወቁ ታጣቂ ኃይሎች ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ሌሊት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ምእመናን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገልጸዋል።።
የ75 ዓመት አረጋዊው ካህን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከልጅነት እስከተገደሉበት ቀን ድረስ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ከዲቁና እስከ ቅስና አገልግለዋል።
በአገልግሎት ዘመናቸውም ዳሪሙ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተባበር አሠርተው ለአገልግሎት ማብቃታቸው ተጠቅሷል።
የቀሲስ ንጉሴ ወልደ መድኅን ሥርዓተ ቀብር ነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
በምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሮቤ ወረዳ እየተባባሰ የመጣዉን የኦርዶክሳዉያን መከራ እና ሞት የሚመለከተው አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸዉ በተደጋጋሚ ጊዜ የአካባቢው ምእመናን ጥሪ ቢያቀርቡም አሁንም ድረስ የኦርቶዶክሳውያን ግድያና መከራ እንዳላበቃ ከምእመናኑ አንደበት ተገልጿል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።
❤5
ሰበር ዜና
ፋኖ በምህረት ገብቷል በሚል ድስኩር ፈንጠዝያ ላይ የዋለው የአገዛዙ ጥምር ሃይልን የጎንደሬ በጋሻው ከፍለ ጦር ቴውድሮስ ብርጌድ አባላት ደስታውን ወደ ለቅሶ ቀይሮለታል።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዛሬ ነሀሴ 25 /2017 ዓ/ም ከጠዳ ዩኒቨርስቲ ምረት የገቡ ፋኖዎች ተሀድሶ በሚል ድስኩር ከህዝብ በዘረፋት ሀብትና ንብረት የአገዛዙ አመራሮችና ወንበር አስጠባቂ ሀይሎች በድግስ ፈንጠዝያ ውለው ከቀኑ 11 ሰዓት ወደ ማክሰኝት ከተማ ሲያመሩ የቴውድሮስ ብርጌድ አባላት ምንዝሮ ቀበሌ ላይ ደፈጣ በመያዝ ጥጋባቸውን ወደ ለቅሶ ቀይረውታል።
የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ቴውድሮስ ብርጌድ ጀግኖች ዛሬ የአገዛዙን ጥምር ሀይል የቁርጥና ቢራ ጥጋባቸውን እንደ ጎማ በማፈንዳት አስተንፍሰው ከስምንት ኪሎ ሜትር በላይ አስፈርጥጠው ሰባቱን ወደሞ*ት ሸኝ*ተው 12ቱን ከባድና ቀላል ቁስለኛ አድርገው የሀዘን ማቅ ውስጥ ጥሏቸዋል።
በውጊያው ጠዳ ዩንቨርስቲ ለአቀባበል የመጡ አመራሮችና የአገዛዙ ባለስልጣናትም በፍራቻና በድንጋጤ ዩኒቨርስቲውን ለቀው ወደ ጎንደር ከተማ ፈርጦጠው ሂደዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር : የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ህ/ግን /ኃላፊ አርበኛ ታድሎ ደሴ (ካስትሮ )
ፋኖ በምህረት ገብቷል በሚል ድስኩር ፈንጠዝያ ላይ የዋለው የአገዛዙ ጥምር ሃይልን የጎንደሬ በጋሻው ከፍለ ጦር ቴውድሮስ ብርጌድ አባላት ደስታውን ወደ ለቅሶ ቀይሮለታል።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዛሬ ነሀሴ 25 /2017 ዓ/ም ከጠዳ ዩኒቨርስቲ ምረት የገቡ ፋኖዎች ተሀድሶ በሚል ድስኩር ከህዝብ በዘረፋት ሀብትና ንብረት የአገዛዙ አመራሮችና ወንበር አስጠባቂ ሀይሎች በድግስ ፈንጠዝያ ውለው ከቀኑ 11 ሰዓት ወደ ማክሰኝት ከተማ ሲያመሩ የቴውድሮስ ብርጌድ አባላት ምንዝሮ ቀበሌ ላይ ደፈጣ በመያዝ ጥጋባቸውን ወደ ለቅሶ ቀይረውታል።
የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ቴውድሮስ ብርጌድ ጀግኖች ዛሬ የአገዛዙን ጥምር ሀይል የቁርጥና ቢራ ጥጋባቸውን እንደ ጎማ በማፈንዳት አስተንፍሰው ከስምንት ኪሎ ሜትር በላይ አስፈርጥጠው ሰባቱን ወደሞ*ት ሸኝ*ተው 12ቱን ከባድና ቀላል ቁስለኛ አድርገው የሀዘን ማቅ ውስጥ ጥሏቸዋል።
በውጊያው ጠዳ ዩንቨርስቲ ለአቀባበል የመጡ አመራሮችና የአገዛዙ ባለስልጣናትም በፍራቻና በድንጋጤ ዩኒቨርስቲውን ለቀው ወደ ጎንደር ከተማ ፈርጦጠው ሂደዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር : የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ህ/ግን /ኃላፊ አርበኛ ታድሎ ደሴ (ካስትሮ )
❤3🙏2