ገጸ ሰብእ
427 subscribers
105 photos
1 file
232 links
ከትናንት ብንዘገይም ከነገ እንቀድማለን!
https://t.me/getseseb
Download Telegram
ትናንት አልፎ ዛሬ ተሰጥቶናል። ነገ ግን ትናንትን ባሳለፈን ዛሬን በሰጠን በአምላካችን እጅ ላይ ናት። ስለዚህ ልንሰራ የምንችለው ዛሬን ነው። የዛሬ ስራችን ግን በአምላካችን ቸርነት ለሚሰጠን ነገ ትልቅ ጥቅም ነው።
ዛሬ የንስሐ ቀን ተሰጥቶናል፤ በመንፈሳዊ ሕይወታችንም በሥጋዊ ሕይወታችንም የሰራናቸውን ስህተቶችና ያልሰራናቸውን መልካም ነገሮች የምናድስበት።
ትናንት ያበላሸነውን አእምሯችንን፤ ያላጠራነውን አመለካከታችንን፤ ያላነጻነውን ሀሳባችንን ዛሬ እናክመውና ነገን በተስፋ እንጠባበቅ።

ከትናንት ብንዘገይም ከነገ እንቀድማለን!

ሳሙኤል በላቸው | ዲያቆን
@getseseb
#share
6🔥1
"ተስፋ አትቁረጪ፡፡ ኦሎምፒያስ ሆይ ! እውነተኛውና እጅግ ክፉው ነገር አንድ ብቻ ነው፤ እውነተኛ ፈተና አንድና አንድ ብቻ ነው፤ እርሱም ኃጢአት ነው፡፡ እንዲህ ብዬ አሰምቼ መንገሬንም መቼም መች አላቋርጥም፡፡

ሌሎች ነገሮች ግን - ለምሳሌ ሴራዎች፣ ጥላቻዎች፣ ማጭበርበሮች፣ ሐሜቶች፣ ስድቦች፣ ወቀሳዎች፣ የራስ ያልኾነን ነገር የእኔ ነው ብሎ መያዝ፣ ስደት፣ ስል የኾነ የጠላት ጎራዴ፣ የጉድጓድ ውስጥ የኾኑ አደጋዎች፣ ከዓለም ኹሉ የሚመጣ ውጊያ፣ እንዲሁም አንቺ ልትጠሪው የምትችዪ ሌላም ኹሉ ነገር - እዚህ ግባ የሚባሉ አይደሉም፡፡

የእነዚህ ነገሮች ክብደታቸው ምንም ይኹን ምን ሐላፊያን ናቸው፤ የሚጠፉ ናቸው፤ ሟች ሰውነታችንን ሊጎዱ ቢችሉም እንኳን መንፈሳዊው ማንንታችንን ግን ምንም ሊያደርጉ የማይችሉ ናቸው፡፡

ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስም ከዚህ ዓለም ሕይወት ጋር ተያይዘው የሚገኙ ደስታዎችም ኾኑ ኀዘኖች ምናምንቴነትን ሊናገር ወድዶ እውነቱን በአንዲት አረፍተ ነገር ገልጦታል፤ እንዲህ ሲል፡-“የሚታዩ ነገሮች ጊዜያዊ ናቸውና” /2ኛ ቆሮ.4፥18/፡፡

ታዲያ እንደ ፈሳሽ ውኃ የሚያልፉ ጊዜያዊ ነገሮችን የምትፈሪው ስለ ምንድን ነው?

ወደ ኦሎምፒያስ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
7👍1😢1
Forwarded from 🎚የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አባላት መወያያ🎚
"እነሆ የአብነት ጊዜ ደረሰ"
ልዩ የትምህርት ዕድል ለወጣቶች
ይደውሉ ይመዝገቡ
096567318ዐ / 0939019363
👍42
Forwarded from Yordanos
የእምነት ሕይወት
በገበያ ላይ

የብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ የምንጊዜም ወርቃማ
ብሒሎች

፩. የንስሀ አባት ማለት እርሱን ስትመለከት እግዚአብሔርን እና ትዕዛዛቱን የምታስታውስበት ሰው ማለት ነው፡፡

፪. ኃጢአት ከበጎ ነገር በተቃራኒ መስራት ብቻ አይደለም። በጎውን አውቆ አለመስራትም ኃጢአት ነው።

፫. ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃሜውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ፡፡

፬. ሊቅ በሊቅነቱ ቢያስተምርህ ሊቅ ትሆናለህ ሊቅ በሕይወቱ ቢያስተምርህ ግን ክርስቲያን ትሆናለህ።

፭. አንተ ሐሳብህን ልትመራው እንጂ፤ ሐሳብህ አንተን እንዲመራህ ቦታ አትስጠው፥ እውነተኛ ክርስቲያን ስሜቱ የሚመራዉ ሳይሆን ስሜቱን የሚመራ ነዉ።

፮. ያልገደለ እጅ ግን ያላዳነ፣ ያልሰረቀ አጅ ግን ያልመፀወተ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የለውም። እውነተኛው መልካምነት ክፋ አለማድረግ ብቻ ሳይሆን መልካም ማድረግም ነው። የሚጎዳንን መተው ብቻ ሳይሆን ስለ ሌሎች ጥቅም መድከምም ነው።

፯. በዚህ ዓለም እንግዳ መሆንህንና ወደ ሰማያዊው ቤትህ እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ። ያን ጊዜ በዚህ ዓለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ።

ከመጽሐፉ የተወሰደ
አዘጋጅ:- ዲ/ን ዮርዳኖስ ፍሬው
አሳታሚና አከፋፋይ:- ሀሁ መጻሕፍት መደብር
ስልክ:- 0911006705
🙏3
እጮኛሞች "በሐዘንም በደስታም አንለያይም!" ማለት ወጋቸው ነው። እናትም ልጇን ስትልክ "ጎሽ የኔ ልጅ እንዳትፈራ!" ብላ ለልጇ ድፍረትንና ተስፋን መስጠት ልማዷ ነው።
ኹሉም በያለበት የደኅንነት ቃል ይገባል። ግን በሐዘን የተለያዩ እጮኛሞችም፤ ልጇን ልካ መኪና ሲበላባት ያልሰማች እናትም እናውቃለን። በመከራህ ቀን የወዳጆችህ የ"እረዳሃለሁ"፣ የ"ከጎንህ ነኝ" ቃል ሊታጠፍ ይችላል።
የማይታበል ቃል ግን እዚህ አለ፤ የማይጠፋ ኪዳን ግን በዚህ አለ " በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ።"
(መዝሙረ ዳዊት 50:15)

ዲያቆን ሳሙኤል በላቸው

https://t.me/deaconsamuelbelachew
👍5🥰1
ሰው ወደ ናፍቆቱ ይሳባል። ሰው ለናፍቆቱ ዋጋ ይከፍላል። ሰው ከናፍቆቱ ጋር ጊዜ ያጠፋል።
እንዲያስታውሷችሁ የምትፈልጓቸው ሰዎች እያስታወሷችሁ ካልኾነ ከእናንተ አንድ ነገር ጎድሎ ይኾናል።
እንዲወዷችሁ የምትፈልጓቸው ሰዎች እየወደዷችሁ ካልኾነ አንድ ነገር ጎድሎአችሁ ይኾናል።
እርሱም
በሕይወታችሁ ሰዎች ከእናንተ የሚናፍቁት የሚስማማቸው ምን ነገር አላችሁ? እናንተን እንዲያስታውሱ እንዲወዱ  የሚያደርጋቸው መልካም ነገር ምንድን ነው?
ይህን ጥያቄ መመለስ ካልቻልን ከሰዎች ጋር አብሮ መቀጠል በጣም ከባድ ይኾናል።
ነገር ግን መልካም ነገር ኖሮአችሁ አላስታውስ ካልዋችሁ በቃ ተዉአቸው ወይ እናንተ ለእነርሱ ወይ እነርሱ ለእናንተ የተገቡ አይደሉም ማለት ነው። ወደሚገቧችሁና ወደምትገቧቸው ሂዱ።
ጌታችን ኢየሱስም ያደረገው ይህንን ነው።
በዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 1:11 እንዲህ ተጽፏል "የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤"

ዲ/ን ሳሙኤል በላቸው

#share
https://t.me/deaconsamuelbelachew
8👍2
ዘወትር እሑድ በአካል በገዳማችን በመገኘት ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት ይማሩ !