የግጥም ጥግ
769 subscribers
56 photos
2 videos
7 files
39 links
ያ ዶሮዬ ጮኈ መንጋቱን ነገረኝ፥
ሲነጋጋ ላርደው ቀጠሮ ነበረኝ።

የተለያዩ ምርጥ ግጥሞችን እዚህ

ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት

@Esamif
@amen1995 መጠየቅና መስጠት ይችላሉ።
Download Telegram

ልዕለ መልካምነትሽ
‎እፁብነትን ከትቦ
‎                ምሉዕ መልክሽን ያወዛ
‎እንደ ፅጌ አበባዋ
‎     የሆንሽ የእንቡጧን ጠረን
‎                    የማትጠገብ መአዛ

‎እኔ ከጎንሽ ያለሁ
‎የውስጤን አውነት አምቄ
‎                  ሳታይኝ ሰርቄ የማይሽ
‎በወንድምነት ሽፋን
‎ከራሴው ሰርቀሽ ያኖርሽኝ
‎                ችዬ እንኳ የማልለይሽ    
‎   
‎የልቤን መንገር ያቃተኝ
‎ብታውቂው የማጣት ስጋት   
‎             ዝም ብል የጭንቄ በደል
‎ብትይዢኝ ለራሴ የምተርፍ         
‎               ከተውሺኝ ዙሪያዬ ገደል

‎ብትፈቅጂ እሺ ብትይኝ
‎አድርጎኝ ብገኝ ዘብ ቋሚ
‎              ለፍቅርሽ ዘለአለም ታጋይ
‎ንግስቴ ሆነሽ ብትከብሪ
‎ፅድቅ ነው ለኔ በረከት
‎                ብኖር ሆኜልሽ አገልጋይ

‎ለደስታሽ ችቦ ለኩሼ
‎ከሀዘንሽ ድባብ ሸሽጌ
ከልዬ ልክ እንደ ጋሻ
‎ሁሉንም ብሆንልሽ ስል
‎አፌ ግን ፈራ መናገር
  የፍቅሩን ማረፊያ ሲሻ

@getmtg
@getmtg
10

ባንታጭም ለ"አብሮ"
‎ ባንሆንም አንድ ላይ
‎መፈፀሙ ላይቀር
‎ የተፃፈው ከላይ

‎ኑሮ መንገዳችን
‎ ቢሆንም ለየቅል
‎ ..... ለዛሬዋ ቀንህ ......
‎"መልካም ልደት" የሚል
‎ አለኝ የምኞት ቃል
‎  
@getmtg
@getmtg
9

ዘመን መጥቶም ቢሄድ
‎ጊዜ 'ማይለያቸው ምርጥ ጓደኛሞች
‎ያንዱ ለአንዱ ብርታት
የክፉም የደጉም ተካፋይ አለሞች

‎በአንድ ጣሪያ ታቅፈው
‎ኑሮ መሰረቱን በህብረት ያቆሙ
‎ትጋት ያፀናቸው
ተደጋግፎ ማለፍ ሰርክ እያጣጣሙ

‎ሲኖሩት ነው እንጂ
‎ቢሰማ ቢነገር ቃል የማይገልፃቸው
‎እስከ ጥግ ድረስ
ጓደኝነት ዋጋው ትርጉሙ የገባቸው

‎ እነሱ እንዲህ ናቸው😊

@getmtg
@getmtg
8

ሆነሽ ሳለ
‎ቆንጂዬ ልጅ
‎      'ምታሳሳ 'ምትወደድ
‎ቢኖርሽም አፍቃሪ ልብ
‎    መልካም ሀሳብ ቀና መንገድ

‎ወትሮ እኔን መንከባከብ
‎               ባይታክትሽ ማስደሰቱ
‎እውነት እውነት እልሻለሁ
‎         ማፍቀር ላልችል ደከምሽ እቱ

‎እያሰብኩኝ የሆንሽውን
‎         እየታየኝ ውበት መልክሽ
‎ያለሽን ግልፅ ፅኑ አቋም
‎                  የሚደነቅ ፀባይ ልክሽ

‎እየጣርኩኝ ላለማጣት
‎ ካንቺ ደጃፍ እግሬ እንዳይቀር
‎ላይሆንልኝ ደከምኩ እንጂ
‎    አይቻልም ታግሎ ማፍቀር     

@getmtg
@getmtg         
9

በኑሮ በሕይወት መንገድ
‎       ቢበዛ ህመም እንቅፋት
‎                ቢፈትን ችግር አበሳ
‎ካለው ከነበር በላይ
‎እጥፉን ይሸለመዋል
‎              የሰው ልጅ ወድቆ ሲነሳ

@getmtg
@getmtg
9

neither of us is happy
but neither of us wants to leave
so we keep breaking one another
and calling it love

(Rupi kaur)
@getmtg
@getmtg
👏41😁1
አልፈቀድክም'ንጂ ፈጥረህ ስትለቀን
መኖር ሲሰለቸን ከ'ለታት ባንዱ ቀን
ፈቅደህ ቢሆን ኖሮ...
በራሳችን መንገድ ወዳንተ እንድንመጣ
ባዶ መቅረት ነበር የዚች ምድር ዕጣ

@getmtg
@getmtg
13🔥8🤔2

‎ምንም አትበል
‎ዝምታ ነው እኔና አንተን የሚያግባባን
‎መጣላቱ ይቅር እንጂ
‎                    ባናወራስ ምን አገባን

‎ከአንደበቴ ቃል ሳይወጣ
‎የሆንኩትን ሳልናገር      
‎            ልብህ ቀድሞ ያውቅልኛል
‎እኔም ደግሞ ......
‎ምን እንደሆንክ ለመረዳት
‎ አንዴ አይንህን ማየት ብቻ ይበቃኛል

‎ቃል አንተንፍስ ተው አናውራ
‎ እንዳይብሰን ሁሉም ይቅር
‎ከስሙኝ ባይ ድምፀት ይልቅ
‎             ዝምታ ነው የእኛ ፍቅር

@getmtg
@getmtg
7👏3

ተሸፍነሽ እንኳን
ፊትሽ ተደንቅሮ የደመና እንቅፋት
‎እንደሙሽራ እንስት
‎ አማረባት እንጂ አትባይም ከፋት

@getmtg
@getmtg
8

the night after you left
i woke up so broken
the only place to put the pieces
were the bags under my eyes

(Rupi Kaur)
@getmtg
@getmtg
🔥1

ሙሾ ላመለጠ ወጣትነት
(በዕውቀቱ ሥዩም)

ሳይደምን ይዘንባል
ይዶፋል
ከደጃፌ ግርጌ የሕይወት ጎርፍ ያልፋል

የክንፌ ርጋፊ
አንድ የላባ ነዶ
ያካሌ ቅራፊ
የቀረ ተጎርዶ
ተጠርጎ ሲወሰድ በጥሞና እያየሁ
ይሄው ቁጭ ብያለሁ

ሲጋልብ በፊቴ ይህ የውሀ ሰጋር
ጀንበሬን አየኋት
ተጠርጋ ሰትሄድ ከሰርዲን ጣሳ ጋር

የልጅነት ቅርሴ
ድዴ ያባረራት ያች የወተት ጥርሴ
ካሮጌ ቆርኪ ጋር አብራ ተቀላቅላ
ባረፋ ተከባ በጎርፍ ጀልባ ታዝላ
ስትሄድ እያየሁ
ይሄው ቁጭ ብያለሁ

የመጀመሪያዋ የጉንጬ ላይ ቡግር
የመጨረሻዋ የራሴ ላይ ጠጉር
ከሳር ከትቢያው ጋር እንደተቃቀፉ
በጎርፍ ጀርባ ላይ እየተንሳፈፉ
እንደዋዛ ሲያልፉ
በጥሞና እያየሁ
ይሄው ቁጭ ብያለሁ

@getmtg
@getmtg
👏32

ተበዳይ ሰው መስሎ
...... መሄድ ለፈለገ .....
‎አንል "ለምን ቀረች?" አንል "ለምን ሸሸኝ?"
‎ከምኞትም በላይ .....
መረገጫ ጨርቁን እንጥፈን ነው የምንሸኝ

@getmtg
@getmtg
👏63🔥1
የምንወደዉና ብዙ የለፋንለት የ ህይወታችን ምዕራፍ "ነበር" ይሆናል ብሎ ማሰብ🥺
6
Forwarded from 🚶‍♂️📚לֵוִי
በYouTube መተናል🎉🎊!


#ሳይኮሎጂያዊ..
#ፍልስፍናዊ..  እና
#ሐይማኖታዊ.. እሳቤዎችን በሰፊው የምንዳስስበትን..
እንዲሁም፦ በአጫጭር ድርሰቶቼ ውስጥ የተገለፁትን ገፀባሕርያት ከሳይኮሎጂ አንፃር የምንገመግብበትን የYouTube channel subscribe በማድረግ እናስመርቀው 🙏

500 Subscribers ስንደርስ video መጫን እንጀምራለን!🎉🎊

https://youtube.com/watch?v=UYS5BsR-0g0&si=GVthq0_J5oHs-gA1
ብቻዬን ትተሺኝ
ላትመለሽ ነገር መች በቃኝ መናፈቅ
ልማዴ አድርጌው ማይመጣ መጠበቅ
እጠብቅሻለሁ እንዴት ልግለፅልሽ
ትናፍቂኛለሽ እንደምን ልበልሽ
የራበው አስቀዳሽ ትግስት የነፈገው
ከካህኑ ምላስ ዕትው የምትል ቃል እንደሚፈልገው
በዛሬ ቀመር ውስጥ ከሰው አንቺን ባጣ
ትናፍቂኛለሽ እንደ ትላንትና ደግሞ'ንደማይመጣ
ትናፍቂኛለሽ...
ኩልል እንደምትል የውሀ ጠብታ
ሀሩር ያነደደው ዘማች እንደሚሻት የ ዓይኑ ውልብታ
ትናፍቂኛለሽ...
አርባ ቀን አርባ ሌት እንደፆመ መናኝ
ቀን እንደረዘመው ካምላኩ እስኪገናኝ
እጠብቅሻለሁ
ነፍስና ስጋዬን ፈጥሮት ለኩነኔ
ዘመኑ ሲታደስ እያረጀሁ እኔ
ልክ'ንደ መስከረም
ከነሀሴ ዝናብ አበባ እንዳገኘ
የኔም ጥበቃዬ ባንቺ ከተዳኘ
ብቻ ምን ልበልሽ እጠብቅሻለሁ
ያለፈው ዘመኔ...
ስቴጅ ያፈረስሽው እንደ ጥንት መንደር
ዛሬ መመለስሽ ላያስክሰው ነገር

@getmtg
@getmtg
👍65

ልብስ ሰፊዋ
(በሕይወት እምሻው)

በከተማው አደባባይ እምብርት ላይ የተሰቀለው ባንዲራ ብዙ ክረምትና በጋ ስለተፈራረቀበት ተጎሳቁሏል፡፡ በክረምት ዝናብ ረጥቧል፡ በበጋ አቧራ አድፏል፡ በሃሩር ንዳድ ገርጥቷል፡፡ በነፋስ ሳቢያ ተቀዷል፡፡ ግን ማንም ልብ ያለው፡ ማንም ደንታ የሰጠው አልነበረም፡፡

ፖለቲከኞቹ "በትላልቅ ጉዳዮች" ተጠምደዋል፡፡

ወታደሮቹ የሀገሪቱን ድንበር ከጠላት እየጠበቁ ነው፡፡

የመንፈስ አባቶች ነፍሳትን ከሲኦል በማዳን፡ ሕዝቡ ደግሞ ኑሮውን በማሸነፍ ሩጫ ተጠምደዋል፡፡

ከአደባባዩ በስተግራ በኩል ጥግ ላይ ምስኪን ልብስ ሰፊ ግን በባንዲራው ጉዳይ ተብከንክናለች፡፡

አንድ ቀን ከሰዐት በኋላ በአጠገቧ በጥድፊያ የሚያልፈውን ቁመተ ሎጋ ሰው አስቆመችና ባንዲራውን እንዲያወርድላት ጠየቀችው፡፡

"ለምን?" ብሎ ጠየቃት፡፡

"ለምን ...? እያየኸው .... እጅግ ቆሽሿል፡ ቀለሞቹ መለየት እስኪያቅት ገርጥቷል፡፡ በዚያ ላይ ተቀዷል፡፡ ቀለሞቹን መመለስ ባልችል እንኳን፡ ቢያንስ አጥቤ ልስፋው ብዬ እኮ ነው ... ልብስ ሰፊ እኮ ነኝ" ብላ መለሰችለት፡፡

ሰውዬው ሣቀና እንዲህ አላት፡

"ምንሸ ተነካና? ባንዲራ አይደል ... ምን አገባሽ ... የድሃ ቅንጡ ነሽ ባክሽ ... እስቲ መጀመሪያ የተቀደደ ልብስ ስፊና የራስሽን ቀዳዳ ድፈኚ ... የደላሽ!"

ጭንቅላቷን ባለመስማማት ነቀነቀች፡፡

"ግን እኮ ተቀዷል ... " ከማለቷ በቆመችበት ጥሏት ሄደ፡፡

ጥቂት ካሰበች በኋላ

ሁለት የጎዳና ጎረምሶችን ብር አስጨብጣና ምሰሶውን እንዲወጡ አድርጋ፡ ባንዲራውን አስወረደች፡፡

አጠበችው፡ ሰፋችው፡፡ ልጆቹ መልሰው እንዲሰቅሉላት ካደረገች በኋላ ሲውለበለብ እየተመለከተች ፈገግ ብላ፡ "ጎበዞች! እንደ ቀድሞ ግርማ ሞገሱ ባያስደነግጥም ከቀዳዳ እና ከቆሻሻው ይሄ ይሻላል" አለች፡፡

በነጋታው ከዚህ በፊት ዐይታቸው የማታውቅ ሰዎች አዲስ ባንዲራ ይዘው መጡ፡፡ አጥባና ሰፍታ የሰቀለችውን ባንዲራ አውርደው ጣሉና በአዲሱ ተኩት፡፡

አንዱን ፈራ ተባ እያለች ተጠጋችውና፡ "ምነው እስከዛሬ ሳታዩት ገና እስተካክዬው ስሰቅለው ልትተኩት መጣችሁ?" ስትል ጠየቀችው፡፡

ሰውዬው ዞርም ብሎ ሳያያት፡

"ለዐይን ይቀፋል፡፡ እንዲህ እንደነገሩ የተጣፈ ባንዲራ በዋና አደባባያችን ላይ ተሰቅሎ ማየት በጣም ይቀፋል" ብሎ መለሰላት፡፡

(ዥዋ ዥዌ)

@getmtg
@getmtg
😁43

you have so much
but are always hungry for more
stop looking up at everything you don't have
and look around at everything you do

- where the satisfaction lives

(Rupi kaur)

@getmtg
@getmtg
👍41

"መቼስ ለትዝታ ሩቅ የሚባል _ላለመድረስ ከፈለጉም ቅርብ የሚባል ቦታ የለም፡፡"

(ከዕለታት ግማሽ ቀን)

@getmtg
@getmtg
👍43👏1