፡
ቀጨኔ አድባርሽ ማነው
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
"ጋራው ሚካኤል ባይሰማን
ጋሽ ቸሬ ባለውቃቢው
የኛን ልመና አይዘነጋም
በጨለማ ሹክ ያሉት ፀሎት
እስኪፈታ ጀንበር አትነጋም"
ብለውኝ ለሊቱን ሙሉ
ካደምኩት ተሰዋ እንቅልፌ
ሲነጋስ_!?
ትዝታዋ እንጂ የለችም እሷ ከቅፌ፤
እግዚአብሔር አብ ከተራራው ጫፍ
ሞገሱን ይዞ ተቀምጧል
ፀበሉን እያፈለቀ
የስንቱን የንባ ሀዘን ውጧል!
ታዲያሳ እግዚሐርዬ
የኔ እና የሷን ነገር ምነው!
በቶሎ ያልፈጠምክልኝ
ጠንቋይ ቤት ሂዷል ብለህ ነው!?
ከእንጦጦ ዳገት እስከ ሾላ ጫፍ
እሷው ነች በሩቁ ተለጥፋልኝ
እንግዲህ ማምጣት ካቃተህ
በል ቶሎ አይኔን አጥፋልኝ
ማዞሪያን ስዞረው ውዬ
በቅርበት እሷን ካላየው
አይን አለኝ ማለት ምንድር ነው!?
"ሸክላ ሰሪ ናት" ቢሉኝ
አፈር ሆኜ ምነው ብታፍሰኝ
በማርያም ወንዝ ውሃ አልቆጥቁጣኝ
ክንዷ ላይ ብታንተርሰኝ
ሸማዬን ላንተ አላነጥፍም
ከንግዲስ ግጥም አልጥፍም
/አምጣልኝ አልኩህ አምጣልኝ/
እምቢየው እሷ ከሌለች
ብቻዬን አልባረክም
እንግዲህስ አምላክ ነህ ብዬም
ለክብርህ ዣንጥላ አልልክም
ብትፈልግ ሲኦል ወርውረኝ
አድርገኝ ለሚፋጅ ቅጣት
አይበልጥም እሷን ከማጣት።
@getmtg
@getmtg
ቀጨኔ አድባርሽ ማነው
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
"ጋራው ሚካኤል ባይሰማን
ጋሽ ቸሬ ባለውቃቢው
የኛን ልመና አይዘነጋም
በጨለማ ሹክ ያሉት ፀሎት
እስኪፈታ ጀንበር አትነጋም"
ብለውኝ ለሊቱን ሙሉ
ካደምኩት ተሰዋ እንቅልፌ
ሲነጋስ_!?
ትዝታዋ እንጂ የለችም እሷ ከቅፌ፤
እግዚአብሔር አብ ከተራራው ጫፍ
ሞገሱን ይዞ ተቀምጧል
ፀበሉን እያፈለቀ
የስንቱን የንባ ሀዘን ውጧል!
ታዲያሳ እግዚሐርዬ
የኔ እና የሷን ነገር ምነው!
በቶሎ ያልፈጠምክልኝ
ጠንቋይ ቤት ሂዷል ብለህ ነው!?
ከእንጦጦ ዳገት እስከ ሾላ ጫፍ
እሷው ነች በሩቁ ተለጥፋልኝ
እንግዲህ ማምጣት ካቃተህ
በል ቶሎ አይኔን አጥፋልኝ
ማዞሪያን ስዞረው ውዬ
በቅርበት እሷን ካላየው
አይን አለኝ ማለት ምንድር ነው!?
"ሸክላ ሰሪ ናት" ቢሉኝ
አፈር ሆኜ ምነው ብታፍሰኝ
በማርያም ወንዝ ውሃ አልቆጥቁጣኝ
ክንዷ ላይ ብታንተርሰኝ
ሸማዬን ላንተ አላነጥፍም
ከንግዲስ ግጥም አልጥፍም
/አምጣልኝ አልኩህ አምጣልኝ/
እምቢየው እሷ ከሌለች
ብቻዬን አልባረክም
እንግዲህስ አምላክ ነህ ብዬም
ለክብርህ ዣንጥላ አልልክም
ብትፈልግ ሲኦል ወርውረኝ
አድርገኝ ለሚፋጅ ቅጣት
አይበልጥም እሷን ከማጣት።
@getmtg
@getmtg
❤3
ባለቅኔ ነበርኩ
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።
ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?
ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥
ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?
እውነት!
ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።
ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ
ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።
(Red-8)
፡
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።
ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?
ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥
ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?
እውነት!
ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።
ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ
ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።
(Red-8)
፡
👍5❤1👏1
፡
ደስታ ቢራቢሮ
(በእውቀቱ ስዩም)
ደስታ ቢራቢሮ
እኔ ጀብደኛ አዳኝ
ስትከንፊ ስከተል የእድሜ መንገድ ከዳኝ
ሳሎኔ ዱር ሆኖ
በግንድ በቅርንጫፍ በሣር ተሸፍኖ
ከኮርኒሴ በታች ወፍራም ጭጋግ ሰፍኖ
እኔም እድሜ ልኬን የማያድግ ሕፃን
እድገቱ
ቁመቱ
ባስማት የተገታ
ነጋ ጠባ ዝላይ ሁለዜ ጨዋታ
በሄደበት ለማጅ
ነፋስን በመንፊት ውሀን በጨርቅ አጥማጅ
ዓመት ታመት ጮርቃ
ለሹመት የማይታጭ ለዋስ የማይበቃ
ሆኘ ቀረሁ በቃ?
ደስታ ቢራቢሮ
በጣቶቸ ማሀል ቀለምሽ ተነነ
ተከትዬሽ ስከንፍ ላባዬ በነነ
ክንፌ ተመለጠ
ጥላሽን ሳሳድድ ዘመኔ አመለጠ፡፡
@getmtg
@getmtg
ደስታ ቢራቢሮ
(በእውቀቱ ስዩም)
ደስታ ቢራቢሮ
እኔ ጀብደኛ አዳኝ
ስትከንፊ ስከተል የእድሜ መንገድ ከዳኝ
ሳሎኔ ዱር ሆኖ
በግንድ በቅርንጫፍ በሣር ተሸፍኖ
ከኮርኒሴ በታች ወፍራም ጭጋግ ሰፍኖ
እኔም እድሜ ልኬን የማያድግ ሕፃን
እድገቱ
ቁመቱ
ባስማት የተገታ
ነጋ ጠባ ዝላይ ሁለዜ ጨዋታ
በሄደበት ለማጅ
ነፋስን በመንፊት ውሀን በጨርቅ አጥማጅ
ዓመት ታመት ጮርቃ
ለሹመት የማይታጭ ለዋስ የማይበቃ
ሆኘ ቀረሁ በቃ?
ደስታ ቢራቢሮ
በጣቶቸ ማሀል ቀለምሽ ተነነ
ተከትዬሽ ስከንፍ ላባዬ በነነ
ክንፌ ተመለጠ
ጥላሽን ሳሳድድ ዘመኔ አመለጠ፡፡
@getmtg
@getmtg
👍2👏2❤1
፡
ልዕለ መልካምነትሽ
እፁብነትን ከትቦ
ምሉዕ መልክሽን ያወዛ
እንደ ፅጌ አበባዋ
የሆንሽ የእንቡጧን ጠረን
የማትጠገብ መአዛ
እኔ ከጎንሽ ያለሁ
የውስጤን አውነት አምቄ
ሳታይኝ ሰርቄ የማይሽ
በወንድምነት ሽፋን
ከራሴው ሰርቀሽ ያኖርሽኝ
ችዬ እንኳ የማልለይሽ
የልቤን መንገር ያቃተኝ
ብታውቂው የማጣት ስጋት
ዝም ብል የጭንቄ በደል
ብትይዢኝ ለራሴ የምተርፍ
ከተውሺኝ ዙሪያዬ ገደል
ብትፈቅጂ እሺ ብትይኝ
አድርጎኝ ብገኝ ዘብ ቋሚ
ለፍቅርሽ ዘለአለም ታጋይ
ንግስቴ ሆነሽ ብትከብሪ
ፅድቅ ነው ለኔ በረከት
ብኖር ሆኜልሽ አገልጋይ
ለደስታሽ ችቦ ለኩሼ
ከሀዘንሽ ድባብ ሸሽጌ
ከልዬ ልክ እንደ ጋሻ
ሁሉንም ብሆንልሽ ስል
አፌ ግን ፈራ መናገር
የፍቅሩን ማረፊያ ሲሻ
@getmtg
@getmtg
ልዕለ መልካምነትሽ
እፁብነትን ከትቦ
ምሉዕ መልክሽን ያወዛ
እንደ ፅጌ አበባዋ
የሆንሽ የእንቡጧን ጠረን
የማትጠገብ መአዛ
እኔ ከጎንሽ ያለሁ
የውስጤን አውነት አምቄ
ሳታይኝ ሰርቄ የማይሽ
በወንድምነት ሽፋን
ከራሴው ሰርቀሽ ያኖርሽኝ
ችዬ እንኳ የማልለይሽ
የልቤን መንገር ያቃተኝ
ብታውቂው የማጣት ስጋት
ዝም ብል የጭንቄ በደል
ብትይዢኝ ለራሴ የምተርፍ
ከተውሺኝ ዙሪያዬ ገደል
ብትፈቅጂ እሺ ብትይኝ
አድርጎኝ ብገኝ ዘብ ቋሚ
ለፍቅርሽ ዘለአለም ታጋይ
ንግስቴ ሆነሽ ብትከብሪ
ፅድቅ ነው ለኔ በረከት
ብኖር ሆኜልሽ አገልጋይ
ለደስታሽ ችቦ ለኩሼ
ከሀዘንሽ ድባብ ሸሽጌ
ከልዬ ልክ እንደ ጋሻ
ሁሉንም ብሆንልሽ ስል
አፌ ግን ፈራ መናገር
የፍቅሩን ማረፊያ ሲሻ
@getmtg
@getmtg
❤10